Friday 31 December 2021

ኢየሱስን ብቻ!

ብቻ! የማያሳይ ከወዳጅ አግዝፎ

ብቻ! ማያጎላ ከአዝማድ አልቆ

Wednesday 1 December 2021

ስህተትን ማን ያስተውላታል? (መዝ. 19፥12)

Please read in PDF

ኀጢአት አማኞች እንዳያስተውሉት ስለሚፈልግ፣ በጽድቅ መዝገብ ውስጥ ራሱን መደበቅ ይወዳል። አብዛኛኞቹ አማኞች ግን የተገለጠ ኀጢአትን አይተው ሲሸሹ፣ ራሱን ሊገልጥ የማይወደውንና ስውሩን ኀጢአትን ግን ሲዘፈቁበት አልያም “ኀጢአት አይደለም” ብለው ሲሞግቱ እንሰማቸዋለን። ከዚህ የተነሣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ተሐድሶ እንዲመጣ የሚሹ አካላት፣ ዘወትር ሊያመለክቱ ከሚገባቸው ተግባራት አንዱ፣ ራሱን ሸሻጊውን፣ “እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ባለ ነገር በነውር ሊይዝ” (ኤፌ. 5፥27) ከሚተጋው ኀጢአት መጠበቅና ማስጠንቀቅ፤ ዘወትር አማኞች እንዳይረሱ ማሳሰብ ነው።

Thursday 18 November 2021

“ወደ ኦርቶዶክስ አልተመለሱም፤ በዚህ መንገድም አይመለሱም!”

 Please read in PDF

ወደ ኦርቶዶክስ ተመልሰናል ባዮችና የኦርቶዶክስ “ቀናተኛው ማኅበረ ቅዱሳን”

የቀናተኞቹ ውይይት ዕጣሬ

በባለፈው ወር ”ወደ ኦርቶዶክስ ተመልሰናል“ ያሉ ወገኖች ብዙ ነጋሪት አስጐስመዋል፤ ከበሮ አስመትተዋል፤ እንቢልታ አስነፍተዋል። ነገር ግን ያስነፉትን እንቢልታ፤ ያስመቱትን ከበሮ፤ ያስጐሰሙትን ነጋሪት ያህል፣ ተቀባይነትን ሳይኾን “ማኅበረ ቅዱሳን የተባለ ‘ኦርቶዶክሳዊ’ ቀናተኛን” በሚገባ አስቀሰቀሰባቸው እንጂ አልጠቀማቸውም። “ተመላሾቹ”፣ እንዲመለሱ መንገድ ያደላደለላቸው ሰው፣ “የማኅበራዊ ሚዲያ አቅም እንዲጠቀሙ በብዙ እንደ መከራቸው ይታመናል፤” ግን ውጤቱን አለመመዘናቸውና በተቀደደ ቦይ መፍሰሳቸው ሊመጣ ያለውን ናዳ አለማስተዋላቸው ወለል አድርጎ ያሳያል።





Thursday 11 November 2021

በደስታ ካልተገዛህለት!

 Please read in PDF

ቅጥር እንዳትቀጥር፣ እንዳታበጅ መስመር

ሚዛን ቱንቢው ይቅር፣ ብላ ጠጣ ጨፍር

በቅንብብ አትኑር፣ ባ’ጥር አትከበብ

Wednesday 3 November 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፲፭)

Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

ከዚህ በታች ያሉት ዐሳቦች፣ ስለ መንፈስ ቅዱስ ጥምቀት መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምራቸው ታላላቅ እውነቶች ናቸው። የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት፦

1.  የመንፈስ ቅዱስን ጥምቀት ከመዳናችን ፈጽሞ ነጥለን ልናየው አንችልም። በቅዱስ ጳውሎስ ትምህርት እንዳስተዋልነው፣ ከክርስቶስ ጋር የአካል አንድነት የሚኖረን በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት አማካይነት ብቻ ነው። በመንፈስ ቅዱስ የሚጠመቀው አማኝ፣ ሕያውና ቅድስት የኾነችውን የቤተ ክርስቲያን አንድነት የሚካፈልና አማኞችን ወደዚህ ፍጹም አንድነት ለመጨመር የሚከናወን ታላቅ መንፈሳዊ ሥራ ነው።



Friday 29 October 2021

በገንዘብ ብዛት አትችሏትም!

Please read IN PDF

ቤተክርስቲያን የክርስቶስ አካል ናት፤ እርሱ ብቻ ደግሞ ራስዋ ነው። የሚያምርና የተንቆጠቆጠ ካቴድራል አልያም ጽርሐ ወንጌል ላይኖራት ይችላል። አማኞቿ ጥልቅ ድኾች፣ ደምግባት አልባ፣ ያልተማሩ ገበሬዎች አልያም ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች ቢኾኑም፤ በክርስቶስ ፊት እኩልና አንድ፤ ኹሉም ለክርስቶስ በኵራት ናቸው። በጌታ ቤት ታላቅና ታናሽ የለምና!

በአንድ ቀን የወደቀ የለም!

Please read in PDF

ስሕተትን ማን ያስተውላታል? ከተሰወረ ኃጢአት አንጻኝ። (መዝ. 19፥12)

ሔዋን ከእባብ ጋር በማይጠቅምና በማያንጽ ወሬ መዘግየቷ ዋጋ አስከፍሎአታል (ዘፍ. 3፥1-6)፤ የመጀመሪያው የእስራኤል ንጉሥ የነበረው ሳዖል ውድቀቱ የጀመረው፣ ትንሽ ከምትመስል ነገር ግን አደገኛ ከኾነ ክፉ የባልንጀርነት ቡድን ውስጥ መሳተፉ ነው (1ሳሙ. 14፥2-3)፤ ጅማሮው መልካም የነበረው ያ ንጉሥ በፍጻሜው፣ ጠንቋይ እንደ ፈለገ፣ ለእግዚአብሔር እንዳልታዘዘ ክፉ ሞት ሞተ፡፡ ሳምሶንን የሚያህል ብርቱ አገልጋይ፣ የመውደቁና የመንኮታኮቱ ጅማሮ፣ ሶምሶንም ወደ ተምና ወረደ፥ በተምናም ከፍልስጥኤማውያን ልጆች አንዲት ሴት አየ። (መሣ. 13፥1) ከምትል ቀላል ሐረግ ነው፡፡

Wednesday 20 October 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፲፬)

 Please read in PDF

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት

የ“መድሎተ ጽድቅ” ጸሐፊ፣ ስለ ነገረ ድኅነት ያን ያህል ሰፊ ጽሑፍ ሲጽፍ፣ አንድም ቦታ ከውኃ ጥምቀት በስተቀር ስለ መንፈስ ቅዱስ ጥምቀት አለመጻፉ፣ ምን ያህል ከመንፈስ ቅዱስ እውነት፣ ከኢየሱስ ትምህርትና ሕይወት መራቁን፣ የቅዱሳት መጻሕፍትን ኃይል ባለማወቅ እንዴት እንደ ሳተ እንመለከታለን።



መጽሐፍ ቅዱስ ግን፣ በግልጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ ጥምቀት በሚገባ ያስተምራል፤ ደግሞም ከነገረ ድኅነት ጋር ተያያዥና ቊልፍ ትምህርት መኾኑን በሚገባ እናስተውላለን። የሚከተሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች መመልከት እውነታውን እንድናስተውል ይረዳናል።

Thursday 14 October 2021

“ለምን ሄዱ?” አንልም!

 Please read in PDF

(ይህ ጽሑፍ፣ በእውነተኛ ልብ ወንጌልን በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ውስጥ ለማድረስና ለሚሽነሪ አገልግሎት በሕይወታቸው ተወራርደው የሚያገለግሉ ታማኝ አገልጋዮችን አይመለከትም!)

ለምን አንልም?

ክርስቶስ ኢየሱስ፣ ከውስጥ በሚነሳ አሸናፊነትና “ዘገምተኛ” በኾነ ጽኑ የፍቅር መንገድ የሚያሸንፍ እንጂ፣ በግድና በኃይል ማንንም መያዝና አብሮት እንዲኖር አይፈልግም። ጽድቅን ወዳዱ ጌታ፣ ጽድቅን ያደርግ ዘንድ የምድርን የታችኛው ክፍል በትእግሥት ዝግታ ረግጦ መራመዱ ይህን እውነታ በአድናቆት ያሳየናል! ከዚህ በተቃራኒ ግን “ሰሞነኞቹ”፣ እንደ 1980ዎቹ ትውልዶች፣ “‘እስክንድያ እናቴ’ ኦርቶዶክስ ሃይማኖቴ” ብለው መሄዳቸውን ስናይ ምን እንላለን? ምንም!

Wednesday 6 October 2021

አትደነቁ!

Please read in PDF

“ወዳጆች ሆይ፥ በእናንተ መካከል እንደ እሳት ሊፈትናችሁ ስለሚሆነው መከራ ድንቅ ነገር እንደ መጣባችሁ አትደነቁ፤” (1ጴጥ. 4፥12)

ቅዱስ ጴጥሮስ በአማኞች መካከል እንደ እሳት የሚፈትን ፈተናና መከራ ሊነሣ እንደሚችል በግልጥ ያስተምረናል። የፈተናው መነሻ ደግሞ እዚያው መካከላችን መኾኑንም ጭምር፤ አዎን! ከኢየሱስ ጎን ይሁዳ፣ ከጳውሎስ ጎን ዴማስ፣ ከዮሐንስ ጎን ዲዮጥራጢስ፣ ከኤልሳዕ ጎን ግያዝ … መኖራቸው እንግዳና ልዩ ነገር አይደለም። ዛሬ ላይም እንዲህ ያሉ ወገኖች መነሳታቸው ፈጽሞ አይደንቅም፤ አይገርምም። ገንዘብን ለማካበት መጐምጀት፣ ተሰሎንቄን አይቶ ከቅድስና መልፈስፈስ፣ በወንድሞች ላይ የጐበዝ አለቃ ለመኾን መቋመጥ … ያኔም ነበረ፤ አኹንም መኖሩ አይደንቅም፤ አይገርምምም!

Tuesday 5 October 2021

“ኑ! አለቃ ሹመን እንመለስ” ለምትሉ!

 Please read in PDF

ከሰሞኑ ጯኺ መፈክሮች ውስጥ፣ “ወደ ተቋማዊው ኦርቶዶክስ (institutional Orthodox) እንመለስ” የሚለው አንዱ ነው። የሚመለሱበት የአብዛኛዎቹ ምክንያታቸው ደግሞ፣ “‘ተሐድሶ’ ወደ ወንጌላውያን አፍላሽ ኾኖአል እንጂ፣ በራሱ መቆም ያልቻለ ነው፤ ስለዚህም ወደ ተቋማዊው ኦርቶዶክስ ተመልሰን አስቀድመን ከጴንጤነት እንዳን፤ ቀጥለን ደግሞ በኦርቶክሳዊ መንገድ ‘ክርስትናን’ እንስበክ” የሚል ነው። እኒህ ሰዎች፣ አኹን ላይ፣ ወደ ተቋማዊው ኦርቶዶክስ መመለስን ቀለል አድርገው ሲናገሩ፣ በወንጌላውያን “pulpit” ላይ የማርያምን ምልጃ ብንሰብክ፣ ከልካይ የለንም ባይ ፍጹም ተላላዎች ይመስላሉ!

Monday 4 October 2021

የአፈግፋጊዎቹ ሰበብ!

 Please read in PDF

አንድ የምዕራብ ቤተ ክርስቲያን አባባል አለ፤ “በምድር ላይ ፍጽምት ቤተ ክርስቲያን የለችም፤ ምናልባት ካለች፣ አንተ የገባህባት ቀን ፍጽምናዋን ታጣለች” ይላል። ሙሉ ለሙሉ ባልተዋጀው ዓለም ስንመላለስ ፈተናና ውጊያ፤ መሰናክልና ወጥመድ፣ መከራና ተግዳሮት አለብን፤ ጌታችን ኢየሱስ ራሱ፣ “እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤” (ማቴ. 10፥16) ብሎ ተናገረን እንጂ፣ ወደ ሰላማውያንና ፍጹማን አማኞች ወይም ማኅበረ ሰቦች ዘንድ እልካችኋለሁ አላለንም። እናም ውጊያችን ፈርጀ ብዙና በዚህች ምድር ላይ እስካለንም ድረስ የማያቋርጥም ነው።

Sunday 3 October 2021

የደቂቀ እስጢፋኖሳውያን ተሐድሶና ከዳተኛ ወንድማቸው

Please read in PDF

እስጢፋኖሳውያን፣ የወንጌላውያን ተሐድሶ በአውሮፓ ከመጀመሩ ከዓመታት በፊት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የወንጌል ችቦ እንደ ለኮሱ ይታመናል፤ አንዳንዶች የተሐድሶ አገልግሎት በኢትዮጵያ ውስጥ አጭር ታሪክ ያለው ይመስላቸዋል። ነገር ግን እስጢፋኖሳውያን በኢትዮጵያ ውስጥ አስደናቂና ወንጌላዊ የኾነ ተሐድሶ አሥነስተው ለብዙዎች መዳንና ከጨለማው ዓለም ማምለጥ ምክንያት ኾነዋል። የዚህን ዘመን ክስተት፣ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ታላቅ ዕድል እንደ ነበርና እንዳልተጠቀመችበት የደቂቀ እስጢፋኖሳውያንን ገድል በጻፉት መጽሐፋቸው እንዲህ ይላሉ።

Wednesday 29 September 2021

ተሐድሶ ትርጉሙና ሕይወቱ!

 Please read in PDF

ተሐድሶ፣ “ሐደሰ” ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን፣ ትርጕሙ “አዲስ አደረገ” የሚለውን ትርጕም ታሳቢ ያደርጋል። በተገብሮ (Passive) “ተሐድሰ” ከሚለው ቃል ደግሞ፣ “ተሐድሶ” የወጣ ሲኾን፣ ትርጕሙ “አዲስ ኾነ” ማለት ነው። ስለዚህም ስያሜው ድርጊትን እንጂ ተቋማዊነትን ወይም አደረጃጀትን ፈጽሞ አያመለክትም።


Saturday 25 September 2021

“ቶ”

 Please read in PDF

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ፣ በአንገታቸው የመስቀል ምልክትን የሚያስሩ ብዙዎች፣ “ቶ” ምልክት ያለውን በአንገታቸው ማሰርን በአደባባይ እየተመለከትን ነው። “ቶ” ምልክት ያለው ብቻ ሳይኾን፣ ሌሎችም እንግዳ ድርጊቶች ሲከሰት፣ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶና በሌሎችም አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት ሲከናወን ዝም ማለት አልያም አንዳችም ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቦ፤ ነገሩ ከእንቁላል ወደ ጫጩት እስኪያድግና ብሎም እስኪጐለምስ ችላ ማለት እንግዳ ተግባርም አይደለም።


Thursday 16 September 2021

“ኑ! ወደ ኦርቶዶክስ[ዊነት] እንመለስ!” (የመጨረሻ ክፍል)

 

ካለፈው የቀጠለ …

ዛሬ ኦርቶዶክስ ማን ነው?

“ተዋሕዶ ሳይኾን ስሙ ሃይማኖቱ

ኦርቶዶክስም ሳይኾን ባህሉና ትምህርቱ

ሰርቆና ቀምቶ የሰው ስም በከንቱ

ሰው ኹሉ አለስሙ ምነው መጠራቱ”[1]


Tuesday 14 September 2021

“ኑ! ወደ ኦርቶዶክስ[ዊነት] እንመለስ!” (ክፍል ፩)

 Please read in PDF

ኦርቶዶክስ[ዊነት] ምንድር ነው?

“ኦርቶዶክስ ማለት ኦርቶ ርቱዕ፤ ዶክስ ባህል ሐሳብ፣ ኅሊና፣ ስብሐት፣ ምስጋና ይኾናል፤ በተገናኝ ርቱዐ ሃይማኖት ማለት ነው። … ኦርቶዶክሳዊ ማለት ደግሞ የኦርቶዶክሳዊ ወገን እውነተኛ ቅን፣ በሃይማኖቱ ሐሰትና ስህተት ጽነት የሌለበት።”[1]



Friday 3 September 2021

ተያይዘው የወደቁ ወንድማማቾች (2ሳሙ. 2፥16)

Please read in PDF


ሳኦል የእግዚአብሔርን መንገድ ባለመከተሉ ምክንያት፣ እግዚአብሔር ዳዊትን “በትይዩ” ንጉሥ አድርጎ ቀባው። ለእግዚአብሔር ቃል ያልታዘዘውና እግዚአብሔርን ፈጽሞ ባለመፈለግ ባዛኙ ሳኦል፣ የዳዊትን መሾም ሲያውቅ፣ ዳዊትን ለመግደል የቻለውን ኹሉ ከማድረግ አላረፈም። በሜዳ፣ በምድረ በዳ፣ በዋሻ፣ በተራራ … ባገኘው ሥፍራ ኹሉ አሳድዶ ሊገድለው እጅጉን ፈለገው። ነገር ግን ዳዊትን መግደል ሳይቻለው፣ “ፍልስጥኤማውያን የሞቱትን ለመግፈፍ በመጡ ጊዜ ሳኦልና ሦስቱ ልጆቹ በጊልቦዓ ተራራ ላይ ወድቀው አገኙአቸው። የሳኦልንም ራስ ቈርጠው የጦር ዕቃውን ገፍፈው ለጣዖታቱ መቅደስ ለሕዝቡም የምስራች ይሰጥ ዘንድ ወደ ፍልስጥኤማውያን አገር ሁሉ ሰደዱ።” በማለት እንዴት ባለ አስቀያሚ ሞት እንደ ሞተ ይነግረናል፤ (1ሳሙ. 31፥8-9)።

Friday 20 August 2021

ማርያም፤ ሰባት ጊዜ ሞታ ተነሣች?

Please read in PDF

በኦርቶዶክስና በካቶሊክ ስለ ማርያም ሞት፣ “ትንሣኤና ዕርገት” የማያልቁ አእላፍ ተረቶች አሉ፡፡ ምሳሌ፦ ነገረ ማርያም በግልጥ፣ የማርያምን ስም ትርጉም ሲያብራራ እንዲህ ይላል፣ ማርያም በገሃነም ያሉ ኀጢአተኞችን ባየች ጊዜ፣ “እርሷም እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም እነዚህ ነፍሳት ዘለዓለም በገሃነመ እሳት ወርደው ሲቀሩስ እንኳን አንድ ጊዜ ፯ ጊዜ ልሙት ብላ ሙታለች ኋላም ለፍጥረቱ ኹሉ መጽደቂያ ሁና ተገኝታለችና ወኀብት(ስጥውት) አላት፡፡”[1] ማርያም ለኀጢአተኞቹ ራርታ ሰባት ጊዜ ልሙትላቸው ብላ ሰባት ጊዜ ሞታላቸዋለች! ከዚህም የተነሣ መጽደቂያቸው ኾናለች! መጽሐፍ ቅዱስ ግን፣ “አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤” (ሮሜ 3፥21-22) በማለት የምንጸድቀው በክርስቶስ ብቻ እንደ ኾነ ይነግረናል!

Thursday 19 August 2021

ዕረፉ[አድቡ]! (መዝ. 46፥10) - ክፍል ፪

Please read in PDF

አንፈራም

የሚሰማው፣ የሚታየው፣ የሚነገረው፣ ጠላት በብሩ የሚጎስመውና የሚያጓራው ማጓራቱ እጅግ ጠንካራና አስፈሪ ነው፤ ነገር ግን እኛ አንፈራም፤ የማንፈራበት ምክንያት የማንፈራ ኾነን አይደለም፤ ነገር ግን ፍርሃትንና የፍርሃትን ምንጭ የሚሽር አምላክ ስላለን እንጂ። የማንፈራበት ምክንያት፦

1.   የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፦ ይህ ቃል በዝማሬው ወስጥ እንደ አዝማጅ ተደጋግሞ ተጠቅሶአል (ቊ. 7፡ 11)፤ እርሱ “አምላካችን”፣ የሰራዊት አምላክ”፣ የያዕቆብ አምላክ” ነው። እርሱ በመግቦቱ ለያዕቆብ ወይም ለእስራኤል የተለየ ፍቅር አለው፤ በእርሱ ታምነዋልና። ስለዚህም የእርሱ ከእነርሱ ጋር መኖር ለእነርሱ ክብርና ሞገስ፤ መወደድም እነጂ የፍርሃት ምልክት አይደለም። እርሱ ከእነርሱ ጋር ስለኾነም ለዘላለም መጠጊያና ኀይላቸው፣ በመከራቸው ኹሉ የቅርብ ረዳታቸው (ቊ. 1)፣ መጠጊያቸው (ቊ. 7)፣ ከለላቸው ነው።

Wednesday 18 August 2021

የደብረ ታቦሩ የስንፍና ጸሎት

 please Read in PDF

በአዲስ ኪዳን ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ፣ ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቀረቡ አያሌ ጸሎቶችን እናነባለን። ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቀረቡ አንድ መቶ ሰማንያ ሦስት የሚጠጉ ጸሎቶች መካከል አንዱ ጸሎት፣ “መምህር ሆይ፥ በዚህ መኾን ለእኛ መልካም ነውና አንድ ለአንተ አንድም ለሙሴ አንድም ለኤልያስ ሦስት ዳሶች እንሥራ” (ማር. 9፥5) በማለት ቅዱስ ጴጥሮስ ያቀረበው ጸሎት ነው።

Sunday 15 August 2021

ዕረፉ[አድቡ]! (መዝ. 46፥10) - ክፍል ፩

Please read in PDF

መግቢያ

በዚህ ምዕራፍ፣ መዝሙረኛው የሚዘምረው መዝሙር፣ የቆሬ ልጆችን መዝሙር ነው። የቆሬ ልጆች ከቆሬ ወገን የኾኑ ሌዋዊ መዘምራን ናቸው። በንጉሥ ዳዊት የተሾሙና በዳዊትም ዘመን የቆሬ መዘምራን አለቃ ኤማን የተባለ ሰው ያገለግል የነበረ (1ዜና. 6፥31-47) ሲኾን፣ በቅዳሴ ሥርዓት እግዚአብሔርን በአንድነት ያገለግላሉ። በዳዊት መዝሙር ውስጥ፣ በቆሬ ልጆች ከተሰየሙት ሰባት[1] መዝሙሮች መካከል፣ አንደኛው ዝማሬ ይህ ዝማሬ ነው። ዝማሬው የጽዮን ዝማሬ ነው፣ ዝማሬውን የሚዘምሩትም ደናግላን በደናግል የዜማ ስልት ነው። መዝሙሩ የሚዘመረው በኅብረት፣ የመዘምራን አለቆችም እየመሩት ነው።

መዘምራኑ እየዘመሩ በሰልፍ ወደ ቤተ መቅደሱ ሲሄዱ፣ ደናግላኑ ከበሮ እየመቱ በማጀብ ይከተሉአቸዋል። እጅግ ውብና እግዚአብሔርን በሕዝብ ኹሉ ፊት ከፍ የሚያደርጉበት፣ በእርሱ መታመናቸውንም በአደባባይ የሚገልጡበት ዝማሬ ነው።

Saturday 7 August 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፲፫)

Please read in PDF

ሥራ

ካለፈው የቀጠለ …

ሰዎች ኹሉ ሊድኑ የተጠሩት በክርስቶስ የመስቀል ላይ ሥራ ብቻ ነው፤ መጽሐፍ ቅዱስ ለዚህ ግልጥና የማያወለዳ ትምህርቶቹን እንዲህ ያስተምራል፤

ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።” (ኤፌ. 2፥8-9)

ኹሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ በኢየሱስ ክርስቶስም በኾነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ።” (ሮሜ 3፥23-24)

እንግዲህ ምን እንላለን? ጽድቅን ያልተከተሉት አሕዛብ ጽድቅን አገኙ፥ እርሱ ግን ከእምነት የሆነ ጽድቅ ነው፤” (ሮሜ 9፥30)

Friday 6 August 2021

የክርስቶስ ትንሣኤና የማርያም “ትንሳኤ”

 Please read in PDF

የኦርቶዶክስና የካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናት የማርያምን፣ “በሦስተኛው ቀን” ሳይኾን፣ በጥር ሞታ ነሐሴ “መነሣቷን” ከዶግማ ትምህርቶቻቸው አንዱ አድርገው ይቀበላሉ። ማርያምን “ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች”ና ፍጹም መካከለኛ አድርገው ለመቀበላቸውም ከሚያቀርቡት ማስረጃዎች አንዱ ይህን፣ “ከሞት ተነሥታለች” የሚለውን ትምህርት በዋቢነት በመጥቀስ ነው።

Thursday 5 August 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፲፪)

Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

ሥራ

የክርስትና ትምህርት ጤናማና መዳን የሚገኝበት ቃል ወይም ትምህርት ተብሎ ተነግሮአል (ሐዋ. 13፥26፤ 1ጢሞ. 6፥3፤ 2ጢሞ. 1፥13፤ 2ጢሞ. 3፥15)፤ ትምህርቱ ጤናማ ከኾነ የኑሮ ዘይቤና ጠባዩም ፍጹም ጤናማ መኾኑ አያጠራጥርም። ጤናማው ትምህርት ለእግዚአብሔር ክብር (Orthopraxy) በሚያመጣ እውነተኛ ሕይወት እንድንመላለስ ያደርገናል፤ ይህ ጤናማ ትምህርት ደግሞ ርትዕት ከኾነች እምነት (Orthodoxy) ጋር ፈጽሞ ሊነጣጠል የሚቻለው አይደለም። ሕይወት የሚቀዳውና የሚመነጨውም ከእውነተኛ ትምህርትና ከእውነተኛ ፍቅር (Orthopathy) ነውና።

Thursday 29 July 2021

የመንፈስ ቅዱስን ደስታ መሞላት (ሐዋ. 13፥44-52)

ሰው እንዴት እግዚአብሔርን እየፈራ፣ ፍጹም እግዚአብሔርን ይቃወማል?! እግዚአብሔርን እየፈሩ እግዚአብሔርን የሚቃወሙ ሰዎች፣ ተቃውሞአቸው ከምድር ኹሉ አደገኛውና ከባዱ ሲኾን ፤ በዚህ ኹሉ ውስጥ ግን የመንፈስ ቅዱስ ደስታ አለ! አሜን፡፡ 

Friday 16 July 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፲፩)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

አንድን እውነት ማመን ብቻውን እምነት አይኾንም። ለምሳሌ፦ ሰዎች የእግዚአብሔርን መኖር ብቻ ቢያምኑ እርሱ እውነተኛ እምነት አይደለም። እውነተኛ እምነት ግን ከእግዚአብሔር የሚሰጠውን የዘላለም መዳን ለማግኘት ወይም ለመቀበል በክርስቶስ ኢየሱስ ፍጹም ማመንን የሚጠይቅ ነው። በልጁ የማያምን እምነቱ ርቱዕና ምሉዕ አይደለም። ስለዚህም የአዲስ ኪዳን እምነት በግልጥ ከዚህ በታች የሚከተሉትን እውነቶችን በውስጡ የያዘ ነው፤ እኒህም፦


መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፲)

Please read in PDF

“እምነት ብቻ”ን መጥላት!

ካለፈው የቀጠለ …

ስለ እውነተኛ መዳን ስንናገር፣ ምርጫ አልባ አድርገን የምናቀርባቸው የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶች አሉ። ከእነዚህ ምርጫ አልባ እውነቶች መካከል አንዱ፣ “መዳን በእምነት ብቻ ነው” የሚለው የማይለወጥ እውነት ነው። የ“መድሎተ ጽድቅ” ጸሐፊና አብዛኛው ኦርቶዶክሳውያን ግን ይህን ዐሳብ የሚረዱት በተቃራኒው ነው። መጽሐፍ ቅዱስ፣ “መዳን በእምነት ብቻ ነው” ሲል፣ ሥራን የሚክድና የሚቃወም ወይም ደግሞ በሌላ ጽንፍ፣ “ድነናልና ሥራ ለምኔ!” ለሚሉ አያሌዎች ይኹንታ የሚሰጥ የሚመስላቸው ብዙ ናቸው።



Thursday 8 July 2021

ከፍያለው ቱፋ፤ እግዚአብሔር በምሕረት ያስብህ!

ሃይማኖተኛ ሲታወር፣ ከዓለማዊ ይልቅ ዓመጸኛ እንደሚኾን አውቃለሁ። ትኵረት ለመሳብና ሰውን ለማስከተል፣ እምነቴና መረዳቴ እንዲህ ነው ብሎ መውረድ እንዴት ያጸይፋል?! ጌታችን ኢየሱስ፣ “በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ ለጢሮስና ለሲዶና ይቀልላቸዋል።” (ማቴ. 11፥22) ብሎ ተአምራት አይተው የካዱትን ኮራዚዮንና ቤተ ሳይዳን በጽኑ እንደ ወቀሰው፣ ከደነደነ አማኝ ይልቅ ያላመነ አሕዛብ ተስፋ እንዳለው በግልጥ ነግሮናል።

Sunday 4 July 2021

ከመንፈስ ቅዱስ “የተሻሉ አማኞች”!

 Please read in PDF

“ተግሣጽን የሚወድ ዕውቀትን ይወዳል፤ መታረምን የሚጠላ ግን ደነዝ ነው” (ዐመት)(ምሳ. 12፥1)

አይመጣም እንጂ ቢመጣ፣ ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ዘመን ካሉ አያሌ አማኞች የሚገጥመው ተቃውሞ እንዲህ የሚል ነው፤ “ምን ነክቶህ ነው ግን፣ ያን ኹሌ የቆሮንቶስን ነውር ፊት ለፊት የተናገርከው? በፍቅር ቀስ ብለህ በግል አትነግራቸውም ነበር? አጉል መተቸት ለምን ትወዳለህ? የሐዋርያት “አለቃ” የነበረውን ቅዱስ ጴጥሮስን ፊት ለፊት ስትቃወምስ ትንሽ ለምን አላፈርክም? ደግሞ የገላትያ አማኞችን አዚም[ጥንቆላ] ማን አደረገባችሁ ትላለህ እንዴ? …

Sunday 27 June 2021

ሰዶማዊነትን፣ ፖፑ ሊፈቅዱ ይችላሉን?

 Please read in PDF

ፖፕ ፍራንሲስ ከቅርብ ጊዜ በፊት ስለ ሰዶማውያውን፣ “ማኅበራዊ መብቶች” መናገራቸውን አንዘነጋም። ዛሬ ደግሞ በጻፉት ደብዳቤአቸው፣ “ለእግዚአብሔር ሥራ ሰዶማውያን ጭምር ሊሾሙ እንደሚገባ” መግለጣቸውን ዋሽንግተን ፖስት ደብዳቤአቸውን ዋቢ አድርጎ ዘግቦአል።[1] በእርግጥ በክፋት ከተያዘው ዓለም፣ ቀኖቹ እየባሱ፣ የሚያስቱትም የሚስቱትም እየበዙ እንደሚሄዱ ቅዱስ ቃሉ በማስጠንቀቂያ ጭምር ነግሮናልና፣ ክፉውና ዓመጸኛው ዓለም በክፋቱና በዓመጻው እጅግ መባሱ አያስደንቅም!


Thursday 24 June 2021

ተላላ መጋቢ

 Please read in PDF

ብቻ ይዘምሩ ጉባኤ ያድምቁ

ጭብጨባ አይቀንሱ አሥራት አያስታጉሉ

ልብሳቸው አይደፍ ፊታቸው አይጠውልግ

Friday 18 June 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፱)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

ቅድስና ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ቊልፍ ቃላት መካከል አንዱ ቅድስና የሚለው ነው። በተቃራኒው ደግሞ፣ “የመድሎተ ጽድቅ ጸሐፊ”፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ትርጕም ከሰጣቸው ቃላት አንዱ ቅድስና ነው። ቅድስና የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው፣ “እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ የለምና፥ እንደ አምላካችንም ጻድቅ የለምና፤ ከአንተ በቀር ቅዱስ የለም።” (1ሳሙ. 2፥2)፤ “እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና፤ ሰውነታችሁን ቀድሱ፥ ቅዱሳንም ሁኑ፥ እኔ ቅዱስ ነኝና፤” (ዘሌ. 11፥44)፤“ ጌታ ሆይ፥ የማይፈራህና ስምህን የማያከብር ማን ነው? አንተ ብቻ ቅዱስ ነህና፥” (ራእ. 15፥3) ተብሎ እንደ ተጻፈ፣ እግዚአብሔር አምላክ ብቻ ቅዱስ ነው። በዕብራይስጥ (godesh), በግሪክ (hagiosune) ተብሎ የተጠራው ቅድስና ትርጉሙ፣ መለየት ወይም እግዚአብሔርን መምሰል የሚል ነው። ቃሉ በተለይ በዘሌዋውያን መጽሐፍ ላይ እጅግ ተደጋግሞ የተጠቀሰ ነው።

Friday 4 June 2021

ኹለቱ የእውነት ቃል አገልግሎት አገልጋዮች!

 Please read in PDF

በዚህ ወር “ያለ እውነት፣ የእውነት ቃል አገልግሎት!?” ከሚለው መጽሐፍ መታተም ጋር በተያያዘ፣ ኹለት የእቃአ(ከዚህ በኋላ፣ የእውነት ቃል አገልግሎት ለማለት የሚውል) አገልጋዮች ፊት ለፊት ተገናኝተውኝ አውርተውኝ ነበር። አንደኛው አገልጋይ መጽሐፍ ተርጓሚያቸው ሲኾን፣ ኹለተኛው ደግሞ ሰባኪያቸው ነበር። አንዱን በሰው መካከለኝነት[በወንድም ቴዎድሮስ ደመላሽ አማካይነት] ያገኘኹት ሲኾን፣ ሌላው ግን ያገኘኝ ራሱ ደውሎ ለብቻ ነበር። ኹለቱም በአካል አጊኝተው ሊያወሩኝ በመፈለጋቸው፣ እጅጉን ደስ ብሎኛል።

Thursday 3 June 2021

አዲስ ነገር (ሉቃ. 5፥27-32)

ሙሉ ስብከቱን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው ያድምጡ! በቅዱስ ቃሉ ይባረኩ፤ ለሌሎችም ያካፍሉ፣ የመንግሥቱ ወንጌል ይሰፋ ዘንድ ላልተወደዱ ለሚመስላቸው ኀጢአተኞችና ዓለም ላገለለቻቸው ጋብዙ! የጌታችን ኢየሱስ መንግሥት ከመንፈስ ቅዱስ ኀይል የተነሣ ትሰፋለች፤ አሜን! 





Thursday 20 May 2021

የእውነት ቃል አገልግሎትና የእምነት እንቅስቃሴ ተመሳሳይነት!

 Please read in PDF

የእውነት ቃል አገልግሎት፣ የእምነት እንቅስቃሴ አጋፋሪ ትምህርት ነው። የእምነት እንቅስቃሴ ትምህርቶቹ ኹሉ ሰውንና ራስን ወደ ማላቅ፤ ሰውን አምላክና አንዳች ልዩ ኃይል በውስጡ እንዳለ የሚያሞኙ፣ የሚያጃጅሉ፣ በምኞት የሚያስጎመጁና የሚያነኾልሉ “የከንቱ ከንቱ፤ ከንቱ ከንቱ ስብከቶችና ትምህርቶችን” የታጀለ አስተምህሮ ነው። ትምህርቶቻቸው ማዕከሉ ክርስቶስ መዳረሻውና ፍጻሜው የእግዚአብሔር መንግሥት መስፋት አይደለም።



Wednesday 19 May 2021

ጌታ ኢየሱስ ነቢይም ነው!

 Please read in PDF

ሊቀ ነቢያት ሙሴ እስራኤልን በተናገረው የስንብት ንግግሩ፥ “አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ መካከል ከወንድሞችህ እንደ እኔ ያለ ነቢይ ያስነሣልሃል እርሱንም ታደምጣለህ” (ዘዳግ. 18፥16) በማለት፥ ለጊዜው ከእርሱ በኋላ ለሚነሱ ለሌሎች ነቢያት ሲናገር በፍጻሜው ግን በትንቢት መልክ ስለሚመጣው መሲሕና ትንቢቱ በእርሱም የተፈጸመ መኾኑን እናያለን። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ አምስት ሺህ ወንዶችን ባሳመነበት (ሐዋ. 4፥4) የኢየሩሳሌም ስብከቱ በጌታ ኢየሱስን ትንቢቱ በትክክል መፈጸሙን ጠቅሶ አብራርቶታል።

Saturday 15 May 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፰)

 Please read in PDF

 ካለፈው የቀጠለ …

 እምነት፦ ሰው፣ በእግዚአብሔር ላይ ያለውን መደገፍ ከሚገልጥበት መንገድ አንዱና ተቀዳሚው እምነት ነው። እግዚአብሔር ለዘላለም እርሱም፤ ቃሉም ታማኝ ነው (2ጢሞ. 2፥13፤ ቲቶ 3፥8)። አማኝ እግዚአብሔር በተናገረው ቃሎቹ ላይ ፍጹም መደገፉ እርሱ እምነት ነው። እኛ በእግዚአብሔር ላይ ጥገኞች ነን፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር የፍጥረቱ አካል አይደለም፤ ይልቅ ፍጥረቱን ብቻውን ፈጥሮአልና እርሱ ከፍጥረቱ እጅግ የተለየና ምጡቅ ነው። ፍጥረት በእርሱ ይደገፋል፣ የእርሱን መግቦት ይጠባበቃል፤ እግዚአብሔር ግን በፍጥረቱ ፈጽሞ አይደገፍም።


Wednesday 12 May 2021

ከኦርቶዶክስ ውጭ ያለ መጤ ነው?

Please read in PDF

ከንቱ ትምክህት!

ማኅበረ ቅዱሳንና አንዳንድ የኦርቶዶክስ ሰባክያን፣ ስለ ክርስትና ሲያወሩ፣ ክርስትናን ራሳቸው ጠፍጥፈው የሠሩትና ለዓለም የናኙት ይመስላሉ። እነርሱ በግብዝነት የሚመኩትን ያህል ክርስትና የሰበኩት፣ የመንግሥቱን ወንጌል ለዓለሙ የናኙት የመጀመሪያዎቹ ደቀ መዛሙርት እንኳ እንደ እነርሱ ፈጽሞ አይመኩም፤ አይገበዙምም። እጅግ በጣም የሚያስደንቀው ነገር፣ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ አባ ሰላማ፣ ኢትዮጵያዊ  እንዳልኾነ የሚያውቁ እጅግ ጥቂቶች ናቸው። እንዲያውም ከታወቁት የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፍት አንዱ፣ ቅዱስ ማቴዎስ የተገደለው በኢትዮጵያ ምድር እንደ ኾነ ይነግረናል። ክርስትና አገር በቀል ቢኾን፣ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ምድር ባልተገደለ!


Saturday 8 May 2021

ግንቦት ልደታና የሕይወት ትዝታዬ!

 Please read in PDF

የዛሬ አሥራ ሰባት ዓመት ገደማ፣ ነፍሴ ከግንቦት አንድ አምላኪያን እጅ ያመለጠችበት ቀን ነው። በዚያን ቀን፣ በአርሲ ነጌሌ ሶጊዶ ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓለ ንግሡ ላይ ላገለግል ተጠርቼ በዚያ ነበርኩ። “የተሸሸገ ጣዖት” በሚል ርዕስ፣ የያዕቆብ ሚስት ራሔል ጣዖትን መሸሸጓንና በዚህም የደረሰባትን በማንሳት አንስቼ አገለገልሁ፤ እኛም ይህን ማድረግ እንደሌለብን ብርቱ ማስጠንቀቂያ በማኖር ጭምር። ነገር ግን በዚያን ቀን ሳስተምር፣ ከታቦቱ ጎን ትምህርቴን ቆሞ ይሰማ የነበረ፣ የገጠር ከተማይቱ ጠንቋይ ደም በሰረበ ዓይኖቹ ይመለከተኝ ኖሯል።

Thursday 6 May 2021

ይድረስ እንደ እኔ ለነበራችሁ ኹሉ!

Please read in PDF

እኔ!

በአጭር ቃል፣ እኔ ትላንትና የክርስቶስን መካከለኝነት ነቅፌ የማርያምን መካከለኝነት አስተምር ነበር፤ የክርስቶስን መካከለኝነት ያስተምሩና ይሰብኩ የነበሩትን ነቅፍ፣ ሰድብ፣ በብርቱ ቃል ተች፣ አዋርድ ነበር። እኔ በማደርገው ንግግርና ድርጊት ሰዎች እስኪሸማቀቁ ድረስ ለብዙዎች የመሰናከልና የመውደቅ ምክንያት ነበርኩ። ማርያምን በዝማሬ አምልኬአለሁ፤ ወደ እርሷ ጸልይ፤ በስሟም እማጠን፣ አማልጂኝ ብዬም እለምናት ነበር። ለስእሏ እሰግድ፣ ለስሟም ስዕለት አስገባ፣ በመላእክት፣ ቅዱሳን ተብለው በሚጠሩ ፍጡራን ሰዎችና ቊሳት ኹሉ ስም አምልኮ እፈጽም፣ እግዚአብሔር ሩቅ እንደ ነበር፣ መዳንን በግል ጥረት ማግኘት እንደሚቻል ለዚህም ገዳም ለገዳም እንከራተትም … ነበር።

Saturday 1 May 2021

የሕማም ሰው

Please read in PDF

ነቢዩ ኢሳይያስ ስቁዩንና መከራ ተቀባዩን መሲሕ፣ “ደዌን የሚያውቅ የሕማም ሰው” ብሎ ይጠራዋል (ኢሳ. 53፥3)። መሲሑ መከራን የማይቀበልና ሕመም ተጠያፊ አይደለም፤ ይልቁን ሐዋርያው ጳውሎስ፣ “በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ መኾኑን” (ፊልጵ. 2፥8) በግልጥ ተናገረ። መሲሑ ለመታመም የፈቀደ፣ ለመድቀቅ የወደደ፣ ለመዋረድ ክብሩንና ጥቅሙን ኹሉ በፈቃዱ የተወ፣ እግዚአብሔር ነፍሱ የተደሰተችበት ጻድቅ ባሪያ ነው (ኢሳ. 53፥11)።

Saturday 24 April 2021

Saturday 17 April 2021

ኒቆዲሞስና ነገረ ዳግም መወለድ

 Please read in PDF

ኒቆዲሞስ፣ ኢየሱስን እጅግ በብዙ ከሚንቁት ፈሪሳውያን ወገንና ከአይሁድ አለቆች መካከል አንዱ የነበረ ሰው ነው። በዚያ ዘመን ፈሪሳዊ መኾን ሕጉን እንጠብቃለን፤ ሕጉን በመጠበቅም እንጸድቃለን ለሚሉ ሃይማኖተኞች ብርቱ ትምክህት ነው። ፈሪሳውያን ለሕጉ እጅግ ቀናተኞች ከመኾናቸው የተነሣም፣ ከመካከላቸው ቀራጮችንና ኀጢአተኞችን ፍጹም በማግለል ራሳቸውን እንደ ፍጹም ጻድቃን ይቈጥሩ ነበር።

Thursday 15 April 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፯)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

ጽድቅ“ጽድቅ” የሚለው ቃል የአማርኛ ተካካይ ትርጉሙ፣ “ሕግን መፈጸም፣ እንደ ሕግ መኖርና መመራት፣ ትክክለኛነት፣ እውነት፣ ቀጥተኛ፣ ፍትሓዊ፣ በጎ ምግባር” ማለት ነው። አለቃ ኪዳነ ወልድም በመዝገበ ቃላቸው ሲተረጕሙ “እውነት፣ ርግጥ፣ ቅንነት”።[1] ይላሉ። ይህም በቀጥታ ከእግዚአብሔር ባሕርይ ወይም ከፍጹም ትክክለኛነቱ ጋር የሚገናኝ ነው። ሰው ኀጢአተኛ ስለ ኾነ የእግዚአብሔርን ጽድቅ መፈጸም አይችልም። በተለይ ደግሞ ከመዳን ትምህርት ጋር አያይዘን ስናነሳው እንዲህ ማለት እንችላለን፤ ሰው መጽደቅ የሚችለው ከእግዚአብሔር ልጅ ከክርስቶስ የቤዝወት ሥራ የተነሣ ብቻ ነው።



Tuesday 13 April 2021

አባባይ “shows”

 Please read in PDF

የስህተት መምህራን “የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ ምን ያህል የጽድቅ አገልጋዮች እንደሚመስሉ (2ቆሮ. 11፥13-14)፣ ምን ያህል ውስጠ ተኵላነታቸውን ደብቀው የበግ ለምድ እንደሚለብሱ (ማቴ. 7፥15) … ጃፒ ከኬፋ ሚደቅሳ ጋር ያደረገው ቃለ መጠይቅ ጥሩ ማሳያ ነው[በእርግጥ እንዲህ ዓይነት አባባይ ቃለ መጠይቆች፣ ከዚህ በፊት ብዙ ተደርገዋል]።

Saturday 10 April 2021

ማነው ታማኝ ባሪያ?

 Please read in PDF

ለንዋይ ለክብር ያልተንበረከከ

እዩኝ እዩኝ ማይል ምራቁን የዋጠ

Wednesday 7 April 2021

ዳንኤል ክብረት፣ እውን ባንተ ግብር ተከሰሱ?

 Please read in PDF

 “… ኢየሱስ ክርስቶስም ተቃዋሚ ነበረበት፤ ሙሴም ተቃዋሚ ነበረበት፤ … ሌሎች ትልልቅ ሰዎችም ተቃዋሚ ነበረባቸው”

ይህን ቃል የተናገረው ዳንኤል ክብረት(“ቀሲስ”) ነው፤ የተናገረበትም ምክንያት፣ ከፋና ቴሌቪዥን ጋዜጠኛ፣ “ካንተ ጋር የሚነሡ ክሶችን በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በተዘጋጁ ሰልፎች ላይ ኹሉ፣ ያንተን ፎቶ ኤክስ ምልክት እያደረጉበት ወይም አንተን እያወገዙ የተቃውሞ ድምጾችን እየሰማን ነው … ምንድነው ምላሽህ?” ለሚለው የሰጠው መልስ ነው። በርግጥ ዳንኤል ይህን መልስ አስተውሎ ስለ መመለሱ እርግጠኛ ነኝ።


Saturday 3 April 2021

Maaraanaataa! (1Qoro. 16:22)

Please read in PDF

Jechi “maaraanaataa” jedhu afaan Araamaayik irraa argame; hiikni isaas “yaa Gooftaa! Koottu!” jechuu dha. Kana kan jedhe ergamaa qulqullu kan ta’e Paawloos dha. Kanas kan jedhe kadhannaa isaa keessatti. Ergaa tokkooffaa gara warra Qorontoosiitti barreesse gaafa goolabu ykn xumuru yoo ka’u; dhufaati Kiristoos hawwudhaan ykn bayyee dheeboochuudhaan kan kadhatee dha.


Thursday 1 April 2021

የኮቪድ 19 ክትባትና ውርጃ

 Please read in PDF

“ስለ ምንስ መልካም እንዲመጣ ክፉ አናደርግም? እንዲሁ ይሰድቡናልና አንዳንዱም እንዲሁ እንድንል ይናገራሉና።” (ሮሜ 3፥8)

ክርስትናና ሳይንሳዊ ግኝቶች

ክርስትናና ሳይንስ እርስ በርሳቸው ጥዩፋን አይደሉም፤ ሳይንስ በብዙ መንገዱ ከእግዚአብሔር ባገኘው ጥበብ፣ መልሶ እግዚአብሔርን ተቃዋሚና ተጠያፊ ቢኾንም፣ ክርስትና ግን ለሳይንስ ፍጹም ጀርባውን የሰጠ አይደለም። ክርስትና ለሳይንስ ጀርባውን የማይሰጠውና በእግዚአብሔር መግቦታዊና ሉዓላዊ ጌትነት ሥር ኾኖ የሚቀበለው ግን፣ ሳይንስ ለእግዚአብሔር ፍጥረት አክብሮት ሲሰጥና ራሱ እግዚአብሔርን የሚቃወም እስካልኾነ ድረስ ብቻ ነው። የእግዚአብሔርን ፍጥረት የሚቃወምና ፍጥረት የሚገዛበትን ሥርዓት የሚቃወም እርሱ እግዚአብሔርን ይቃወማልና።


Tuesday 30 March 2021

በጌታ ቸርነት ኹለተኛ መጽሐፌ ታተመ!

 Please read in PDF

“ያለ እውነት፥ የእውነት ቃል አገልግሎት!?” በሚል ርዕስ፣ ስለ “እውነት ቃል አገልግሎት” ማኅበር ከታሪካዊ ዳራቸው ጀምሮ፣ ትምህርቶቻቸውን የሚያስቃኘው መጽሐፌ ታትሞ ከቀን 22/7/2013 ጀምሮ ለንባብ ይበቃል! እንድታነቡት በፍቅር እየጋበዝኩ፣ አስተያየት እንድትሰጡበት፣ አንብባችሁ የማይረባና የማይጠቅም መስሎ ከታያችሁ “ጊዜያችንን አቃጥለህብናል፤ የማይገባ ድካም ደክመሃል” ብላችሁ ልትወቅሱኝ፣ ፍሬና ቁም ነገር ካገኛችሁበት ደግሞ “ታንጸንበታል፤ በርታ!” ልትሉኝ ትችላላችሁ።

Wednesday 24 March 2021

Friday 19 March 2021

አቢግያ - ኹለት ቤት ያዳነች ሴት

Please read in PDF

(የታማኝ ትዳር ውብ ምሳሌ)

መጽሐፍ ቅዱስ፣ እጅግ አስደናቂ ስለ ኾኑ ሴቶች ካስቀመጠልን ሕያው ምስክር አንዷ አቢግያ ናት፤ እንዲህም የተመሰከረላት፣ “የሴቲቱም አእምሮ ታላቅ፥ መልክዋም የተዋበ ነበረ፤” (1ሳሙ. 25፥3)። በተቃራኒው አቢግያ የስሙ ትርጓሜ “ጅል” ተብሎ ለሚጠራው ለናባል ሚስቱ ነበረች፤ እርሱ በምግባሩ “ባለጌ፥ ግብሩም ክፉ ነበረ፤ ከካሌብም ወገን የኾነና … ምናምንቴና ባለጠጋም ነበረ” (ቊ. 3፡ 25)። ሰውየው ባለጌ፣ ግብረ ክፉ፣ ካሌብ የስሙ ትርጉም “ውሻ” እንደ ኾነ፣ የውሻ ጠባይ ያለው ሰው ነበረ፤ ከሚስቱ ፍጹም ተቃራኒ ሰው!


Thursday 11 March 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፮)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

ባለፉት ጊዜያት የ“መድሎተ ጽድቅ” መጽሐፍን በቀጥታ በመጽሐፍ ቅዱስ ከመመዘናችን በፊት፣ በመጽሐፉ ውስጥ ከቅዱሳት መጻሕፍት ዐሳብ ውጭ በኾነ መንገድ እንደ ገና ተተርጕመው የቀረቡትን ቃላት መመልከት መጀመራችን ይታወሳል። ቃላቱን በተመለከተ ዛሬም ቀጣዩን ክፍል የምናቀርብ ይኾናል። መልካም ንባብ።

·        መዳን፦ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥና በአጭር ቃል ስለ መዳን ሲናገር እንዲህ ይላል፣ “በእርሱ[በክርስቶስ] የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።” (ዮሐ. 3፥16)። በመጽሐፍ ቅዱስ መዳን የሚለው ዐሳብ፣ ልክ በዚህ ክፍል እንደ ተጠቀሰው የዘላለም ሕይወት፣ አዲስ ልደት (ቲቶ 3፥5)፣ አዲሱን ሰው መልበስ (ቈላ. 3፥10)፣ አለመጥፋት (ዮሐ. 3፥16፤ 2ጢሞ. 2፥11)፣ ልጅነት (ሮሜ 8፥13)፣ ዳግመኛ መወለድ (ዮሐ. 1፥12-13፤ 3፥3-8) በሚሉ ተካካይ ዐሳቦች ገልጦት እንመለከታለን። 


Monday 8 March 2021

ኢየሱስ እስኪመጣ - ዘጠኝ የአገልግሎት ዓመታቴ

 Please read in PDF

በእግዚአብሔር ቸርነትና የተትረፈረፈ ምሕረት፣ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት በብሎግ ወይም በጡመራ መድረክ አገልግሎት አገልግያለሁ፤ በእነዚህ ዓመታት ከእግዚአብሔር የሰማኋቸውን፣ የተቀበልኳቸውን፣ ቅዱስ ቃሉን ሳነብብና ሳጠና መንፈስ ቅዱስ የገለጠልኝን፣ በኢትዮጵያ በተለያዩ ቦታዎች የደረሱትን እጅግ አሳዛኝ ሰቆቃዎችንና ከፍ ያሉ በደሎችን በአካል በስፍራው ተገኝቼ በመመልከት እግዚአብሔር ምን ይሰማው ይኾን? ብዬ ሙሾ አውርጄአለሁ።   

Saturday 6 March 2021

የጾመ ሕርቃልና የጾመ ዓቢይ ተቃርኖ

 Please read in PDF

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የዓቢይ ጾም የመጀመሪያው ሳምንት ስያሜ “ዘወረደ” ወይም “ጾመ ሕርቃል” ይባላል። የመጀመሪያውን ሳምንት “ዘወረደ” የሚለውን ስያሜ ያገኘው በባለዜማው ያሬድ ሲኾን፣ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ከሰማያት መውረድና የሰዎችን ልጆች ለማዳን ያደረገውን የውርደት መንገድ በማሰብ፣ ከቅዱሳት መጻሕፍት ንባባት እየተነበበ አምልኮ የሚቀርብበትም ሳምንት ነው። ይኸው ሳምንት ከዚህ ከጌታችን ባሕርይ ተቃራኒ በኾነ መንገድ “ጾመ ሕርቃል” ተብሎም ይጠራል።

የጾመ ሕርቃል አጭር ጥንተ ታሪክ[1]

Thursday 4 March 2021

አዲሱ የሮዳስ ተረት!

Please read in PDF

መቼም የሐሰት መምህራንን ጠባይ መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር እንዲህ ይላል፣ “ክፉዎች ሰዎችና አታላዮች፥ እያሳቱና እየሳቱ፥ በክፋት እየባሱ ይሄዳሉ” (2ጢሞ. 3፥13)።  አንድ የስህተት አስተማሪ ፈጥኖ በቅዱስ ፍርሃትና የቅዱሳት መጻሕፍትን ሥልጣን በማክበር በመታዘዝ ካልተመለሰ፣ እየባሰ፣ እየከፋ፣ ኀጢአቱን እየጨመረ፣ አሳሳችነቱን ይበልጥ እየገፋበት ይሄዳል።


Saturday 27 February 2021

ኢየሱስ ጣዖት አይደለም!

Please read in PDF

ዘጠነኛ ክፍል እንግሊዘኛ ያስተምሩን አስተማሪያችን ይኅደጐ ይባላሉ፣ ማስተማር ከመጀመራቸው በፊት ጥቊር ሰሌዳውን በሚገባ ደጋግመው ያጸዱት ነበር፤ አንድ ቀን አንዱ ተማሪ፣ “ቲቸር ለምን እንዲህ ውልውል አድርገው በሚገባ ያጸዱታል?” ብሎ ጠየቃቸው፤ እነርሱም፣ “በሚገባ ባልታጠበ ትሪ ምግብ ትበላለህ?” ብለው ጥያቄውን በጥያቄ መለሱለት። እኔም ዛሬ ሳስተምር፣ እንደ ቀደመው አስተማሪዬ በሚገባ መወልወልን ልማዴ አድርጌ አስቀርቼዋለሁ። ወደ ክርስትና ስመጣ የእኒህ አስተማሪ “መርህ” በዋዛ የሚታለፍ አይደለም።

Monday 22 February 2021

“በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።” (ዮና. 3፥8)

 Please read in PDF

ጥንተ ታሪክ

ሊመጣ ካለው ቊጣና ፍርድ ታመልጥ ዘንድ፣ የንስሐ ዕድልን ሊሰጥ እግዚአብሔር የአማቴ ልጅ ዮናስን ወደ ነነዌ ላከ። ነገር ግን ነቢዩ ዮናስ እግዚአብሔር ላዘዘው ምላሹ አለመታዘዝና ወደ ራሱ ፈቃድ አዘንብሎ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ሸሸ። እግዚአብሔር ግን ሉዓላዊና ኹሉን ሲያደርግ የሚሳነው የሌለ ነውና ዮናስን ወደ ነነዌ በራሱ ማጓጓዣ [በተአምራዊ መንገድ] በዓሳ አንበሪ ሆድ ጭኖ ነነዌ አደረሰው።

Tuesday 16 February 2021

ራቪ ከሞት ወዲያ፤ እኛ ከወዲህ ኾነን!


Please read in PDF

ራቪ ዘካርያስ፣ “የገዛ ሚኒስትሪያቸው” ያረጋገጠባቸው አስቀያሚው የዝሙት ገመና ብዙ ነገሮችን እንዳብሰለስል አድርጎኛል። በርግጥ ከደካማው ሥጋ ለባሽ ይልቅ፣ ቅዱስ ቃሉ የማይለወጥና ብርቱ አስተማሪያችን፣ የሚረባንንና የሚጠቅመንን የሚነግረን ኹነኛ መምህራችን ነበረ፤ እንዳለመታደል በትክክል ከመስማትና ከመታዘዝ ቸል አልን እንጂ። አዎን መጽሐፍ ቅዱስ “የብርቱዎችን” ድካም ያራቆተው፣ እንማርበትና እንታነጽበት ዘንድ እንጂ እንገበዝበት ዘንድ አይደለም።



Monday 8 February 2021

Tuesday 2 February 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፭)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

·        እግዚአብሔርን መምሰል

“በርካታ የምዕራብ ክርስቲያኖች የኦርቶዶክስን የቲኦሲስ ወይም እግዚአብሔርን የመምሰል ሥነ ሐሳብ በትክክል ሊረዱት አልቻሉም። በተለይም ‘ሰው አምላክ ይኾን ዘንድ አምላክ ሰው ኾነ’ የተሰኘውን የቅዱስ አትናቴዎስን ጥቅስ ሲያነቡ፣ ይህ የምሥራቃዊ ሂንዱይዝም ወይም የፓንቴይዝም ተጽዕኖ ነው በማለት ያስባሉ።”[1]

“በቅድስና እግዚአብሔርን በመምሰል የማደግ ሂደትም ከእግዚአብሔር ቅድስና የመሳተፍ ሱታፌያዊ ሂደት ነው። … ሐዋርያው፣ ‘ … ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን።’ ያለው የባሕርዩ መገለጫና መታወቂያ የኾኑትን ነገሮች - ኃይላተ እግዚአብሔር ቅድስና፣ ቸርነት፣ ደግነት፣ ጥበብ፣ እውነተኛነት፣ ገዢነት … የመሳሰሉትን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ የተሰጠን በመኾኑ ነው። ይህም ከፓንቴይዝም እርሾ የጸዳ መጽሐፍ ቅዱሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርት ነው።”[2]