Monday 27 July 2015

“መለከት ድራማ”ና የመጽሐፍ ቅዱስ ይትበሐልን አጠቃቀሙ



                                                    Please read in PDF

“ምነው የ“ጥበብ” መንገድን ከፈጣሪ ቃል ጋር ካልተዘባበታችሁ በ“ጥበብነቷ” ብቻ ማሳየት አይቻላችሁምን? ስለምንስ የማሰናከያን ድንጋይ በትውልድ መንገድ  ላይ  ታስቀምጣላችሁ?”

     “መለከት” ድራማ በተከታታይነት በኢትዮጲያ ብሮድ ካስት ቴሌቪዥን በእሁድ መዝናኛ ፕሮግራም ይቀርባል፡፡  እንደመታደል ጊዜ ሰጥቶ ብዙም ድራማን የመከታተል ልማድ የለኝም ፤ ድንገት ግን እግረ መንገድ ከመጣ አያለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስንና ጌታዬ ክርስቶስን “የሚዳስስ”ና በዚህም ዙርያ በአሉታዊም ሆነ በአዎንታዊ መልኩ የሚንጸባረቅ ከሆነ ትኩረቴን አሳርፍበታለሁ፡፡ እናም “መለከት”ን እንደዋዛ አየሁት ፤ የመጽሐፍ ቅዱስ ይትበሐልን በአንዱ ተዋናይ አማካይነት ሲጠቀም አየሁትና በማስተዋል አጤንኩት ፥ ከዚያም ሁለት ነገርን ከውስጡ እንዲህ አስተውዬዋለሁ፡፡

Friday 24 July 2015

አይበቃም እኮ!


                               Please read in PDF                                           

ልንበላላ ፣ ልንነካከስ ፤
ልንቋሰል ፣ ልንቦዳደስ ፤
ላንተዛዘን ፣ ልንከፋፋ፤
ተጨካክነን ፣ ልንጠፋፋ፤

Monday 20 July 2015

እኛ የክርስቶስን እንጂ የፖፑን (ጳጳሱን) ቃል አንከተልም!!!


                                     

                                                                             Please read in PDF                                                

የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና። (1ጴጥ.2፥21)

    የዘመን ፍጻሜ ደጅ ላይ ነንና ከሐሰተኛው ጠላት ዲያብሎስ (ዮሐ.8፥44) ብቻ ሳይሆን “የክርስትናን ካባና ላንቃ ከደረቡትም አንደበት ቀጥተኛውን የጠላትን ሐሳብ በአደባባይ እየሰማን ነው፡፡ የሮማው ፖፕ “ጌታ እግዚአብሔር አስሩን ሕግጋትና ሌሎችንም ለማሻሻል ሥልጣን እንደሰጣቸውና እንዳሻሻሉም ሰምተናል” ያውም “ግብረ ሰዶምን እንደቅዱስ ተግባር ከመቀበልና ሌሎችም እንዲቀበሉት ከሚያዝ ስብከት ጋር” ፡፡

Friday 17 July 2015

ክርስቶስን በሚያባብል ቃል ለምን? (ክፍል ሦስት)

      
                            Please read in PDF

      የሐሰት መምህራን እውነትን ጨክኖ በመናገር ከሚመጣ መከራና ስደት ይልቅ (2ጢሞ.3፥12)፤ እውነትን ከሐሰት ጋር ሸቃቅጦ በመናገር የሚገኘውን ሥጋዊ ጥቅምና የሚከተላቸው የበዛ ቁጥር ሊኖር እንደሚችል በሚገባ ያውቃሉ፡፡ ሙሴ ከላካቸው አሥራ ሁለት ሰላዮች ፥ አሥሩ ይዘው የመጡትን የሐሰት ወሬ ሰምተው ሕዝቡ ሁሉ ተገልብጠዋል፡፡ ለብዙ ዓመታት ከመራቸው እግዚአብሔርና ሙሴ ይልቅ አሥሩን ወዲያው ተቀበሏቸው፡፡ (ዘኁል.14፥2) “የእስራኤልም ልጆች ሁሉ በሙሴና በአሮን ላይ አጕረመረሙ ማኅበሩም ሁሉ፦ በግብፅ ምድር ሳለን ምነው በሞትን ኖሮ! ወይም በዚህ ምድረ በዳ ምነው በሞትን ኖሮ! እግዚአብሔርም በሰይፍ እንሞት ዘንድ ወደዚች ምድር ለምን ያገባናል? ሴቶቻችንና ልጆቻችን ምርኮ ይሆናሉ ወደ ግብፅ መመለስ አይሻለንምን?” ብለው እስከመካድ የደረሱት ከሐሰት መምህራን አባባይ ቃል የተነሳ ነው፡፡

Monday 13 July 2015

መሞቱ ጥቅም ነው!


                      Please read in PDF   

የ“እኔ አልክድህም” ፣ ስሜታዊ ግለት ፤
ቀደም ቀደም የሚል ፣ የእዩኝ ማንነት ፤
አንተ ደግ መምህር !
አትሞትም ይቅር ! …

Thursday 9 July 2015

ሐዲስ ሕይወት



                                                 Please read in PDF



ምንጭ ፦ ቴዎፍሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጲያ መልእክት ፤ ፩ኛ አመት የፓትርያርክነት በዓለ ሢመት መጽሔት ፤ ግንቦት ፩ ቀን ፲፱፻፷፬ ዓ.ም ፤ ገጽ ፯- ፱፡፡

     ሰላም ለክሙ ወጸጋ እግዚአብሔር አቡነ ወእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘአፍቀረነ ወሐደሰ ለነ ፍኖተ ሕይወት በመንጦላዕተ ሥጋሁ ከመ ናንሶሱ ውስተ ሐዲስ ሕይወት ወወሀበነ ፍሥሐ ዘለዓለም ዘሎቱ ክብር ወስብሐት ለዓለም ዓለም፡፡
     የሰው ልጅ ዳግም ልደት ያገኘበት መንፈሱ ፤ ሕሊናው ፤ ሁለንተናው የታደሰበት ሁል ጊዜ በየቀኑ የሚታደስበት የዘለዓለም ፍሥሐ መገኛ የሚሆን የእግዚአብሔር ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን፡፡

      ይህን የሐዋርያውን መልእክት መሠረት በማድረግ የእግዚአብሔር ረቂቅ ጥበብ በየጊዜው ያስነሣቸው አበው ሊቃውንት እየተመራመሩ ያደራጁትን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በዘመናችን የቃልና የጽሁፍ ማሰራጫ ዘዴዎች አማካይነት በአዲስ መልክና አቀራረብ ተርጉመን ለማቅረብ ግዴታችንም ምኞታችንም ስለሆነ በልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ግንቦት  ፩ ቀን ፲፱፻፷፫ ዓ.ም የኢትዮጲያ ፓትርያርክ በኢትዮጲያ ምድር ከተሾመበት ጀምሮ በየጊዜው የሚታተም አንድ መጽሔት መሥርተናል፡፡ ስሙንም “ሐዲስ ሕይወት” ብለነዋል፡፡ ይህም ከላይ የጠቀስነውን የሐዋርያውን ቃል መሠረት በማድረግ ነው፡፡

Sunday 5 July 2015

ክርስቶስን “በሚያባብል ቃል” … ለምን?! (ክፍል ሁለት)



                                       Please read in PDF

እኒህም፦
       ክርስቶስን እንደሌሎች በሚያባብል ቃል አንሰብክም፡፡
       ሐሰተኝነትንም በማለዘብ አንቃወምም፡፡

ክርስቶስን በሚያባብል ቃል ስላለመስበክ

“እምነታችሁም በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ እንዳይሆን፥ ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለጥ ነበረ እንጂ፥ በሚያባብል በጥበብ ቃል አልነበረም።” (!ቆሮ.2፥4-5)

   ወንጌል ስንሰብክ የሰዎችን ነጻነት (የአመለካከትና የማሰብ) አንጋፋም፡፡ ይህንን ላለመጋፋት ዕውቀትን በጥበብ የመግለጥ መንፈስ ቅዱሳዊ ጸጋን እንጂ (ሐዋ.17፥16-17 ፤ 1ቆሮ.12፥8) የማባበልና የመሸቃቀጥን መንገድ አንከተልም፡፡ የተቆረጠን እውነት ለመናገር በእርግጥም የቆረጠ ልብና መንፈሳዊ ጭካኔ ያስፈልጋል፡፡

Wednesday 1 July 2015

ዲያስፖራዎቻችንን አናምናቸውም!!!

     
                                       Please read in PDF

     ይህንን ፎቶ ሳይ፥ ደንግጬ ክው ብዬ ነው የቀረሁት!!!  ማን ያምናል ኢትዮጲያውያን “ግብረ ሰዶም በመጽደቁ ደስ ብሏቸው ሰልፍ ወጡ ፤ ወይም እንዲጸድቅላቸው እነርሱም ሰልፍ ወጡ” ቢባል?! ግን ይኸው ሆኖ አየን፡፡