Friday 27 January 2023

የአዳዲሶቹ ጳጳሳት ሹመት ስጋት፣ ተስፋዬና ትዝብቴ

Please read in PDF

ጌታ እግዚአብሔር በሉዓላዊ አምላክነቱ፣ ክፉውን ነገር ኹሉ ለክብሩ ሊጠቀምበት፣ ወደ በጎ እንደሚያመጣው እናምናለን፤ ኀጢአት እንኳ ከእግዚአብሔር የሉዓላዊነት ወሰን አልፎ አያውቅም፤ እናም በምድራችን ላይ የምንሰማውን መለያየትና ጥቅመኝነትን ጌታ እግዚአብሔር አጥፍቶ፣ ለሕዝባችን መታነጽና ለክብሩ ታላቅነት እንዲሠራ ከኹሉ በፊት አስቀድመን እንማልዳለን።

አዎን! እግዚአብሔር የፈርዖንን ልበ ደንዳናነት፣ ለሕዝቡ ጥበቃና ትድግና እንደ ተጠቀመበት መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። እግዚአብሔር ሉዓላዊ ነው ስንል፣ በመላለሙ ላይ መጋቢና ሠራዒ፤ አስተዳዳሪና ጌታ ነው እያልን ነው፤ ስለዚህ የምድራችን ነገር የሚገደውና የሚያስብልን ተንከባካቢና ጻድቅ ጌታ አለን ማለታችንም ነው!



Sunday 22 January 2023

“ጳጳሳቱ”ም እንደ “ጐበዝ አለቃ”

Please read in PDF

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ፣ ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘመናት ለቍጥር በሚታክቱ የጐበዝ አለቆች ሥር ወድቃ ታውቃለች፤ እኒህ የጐበዝ አለቆች “ለሕዝባቸው” ዘለላ ርኅራኄ የላቸውም፤ ሕዝባቸውን ቆራርሰው ከማስጨነቅ፤ የራሳቸውን ልድልድና ምቹ የዙፋን ሠረገላ ከማመቻቸት የዘለለ፣ ሕዝቡን ሲፈይዱ አልታዩም። እንዲያውም “የሰኞ ገዳይ”፣ “የማክሰኞ መጋቢ” ተባብለው በሳምንቱ ቀናት ላይ ተሿሹመው አስጨናቂ አስገባሪዎች እንደ ነበሩ ዛሬም ድረስ የምናስተውለው እውነታ ነው።


Wednesday 18 January 2023

የመንፈስ ቅዱስ እንደ ርግብ መውረድ

Please read in PDF

በጥምቀት ወራት ከሚነሡት ዐሳቦች መካከል አንዱ፣ “ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤” (ማቴ. 3፥16) የሚለው ቃል ይታወሳል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲጠመቅ፣ መንፈስ ቅዱስ እንደ ርግብ በጌታችን ላይ ወረደ።

Tuesday 17 January 2023

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፳፫)

 

“በመድሎተ ጽድቅ” መጽሐፍ ውስጥ፣ የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን በተመለከተ ጐልተው የሚታዩትን ስህተቶች በባለፈው ክፍል ከጠቀስናቸው ስህተቶች ባሻገር የሚከተሉትም ይካተቱበታል።

1.2.    የተባለውን በትርጉም በመቃወም፦

የመድሎተ ጽድቅ ጸሐፊ፣ መዳን በክርስቶስ ብቻ እንዳልኾነና በመዳን ውስጥ እኛም ድርሻ እንዳለን ለማሳየት ከተጠቀመበት ጥቅስ አንዱ እንዲህ የሚል ነው፤

“ኦርቶዶ ክሳውያን አባቶቻችን የጸጋው ሥጦታ ነጻ(እንዲሁ) የሚሰጥ መኾኑን በአንድ በኩል ፣ የሰውን ነጻ ፈቃድ (ነጻነት) ደግሞ በሌላ በኩል አስተባብረው በመያዝ ለሰው መዳን የኹለቱ መስተጋብር አስፈላጊ መኾኑን በአጽንዖት ያስተምራሉ። ይህም በቅዱስ ጳውሎስ  ከእርሱ ጋር አብረን የምንሠራ ነንና።” ተብሎ የተገለጸው ነው(1ቆሮ. 3፥9)”

Friday 6 January 2023

ጌታዬ ኢየሱስ ለእኔ የተወለደባቸው ምክንያቶች

 Please read in PDF

በምድራችን ላይ ሲሰሙ ከሚወደዱ ታላላቅ ምሥራቾች ኹሉ፣ የሚልቀውና አቻ የሌለው ምሥራች፣ የጌታችን ኢየሱስ መወለድን የሚያህል ሌላ ምሥራች የለም! መልአኩ እንዲህ አለ፣ “እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።” (ሉቃ. 2፥10-11)፤ ለሰው ኹሉ የሚበቃና ሰውን ኹሉ በእኩል ደስ ማሰኘት የሚችል ምሥራች ከክርስቶስ በቀር አለመኖሩ እንዴት ይደንቃል!