Wednesday 28 September 2016

የጳጳሱና የሰባክያኑ ቤተ ክርስቲያንን “መለካዊ” የማድረግ ሃሳባቸው እስከምን ድረስ ነው?!

Please read in PDF      

          ነቢየ እግዚአብሔር ኤርምያስ በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ዘንድ “አልቃሻው ነቢይ” ተብሎ ይጠራል፡፡ ይህንንም ስያሜ ያገኘበት ዋናው ምክንያት፥ ሕዝቡ በኃጢአትና በነውር ምድሪቱን እጅግ በማርከሳቸውና ፊታቸውን ወደንስሐ ዘወር እንዲያደርጉ፥ ከእነርሱ ጋር እየተራበና እየተጠማ በመካከላቸው ሆኖ አዘውትሮ ቢናገራቸውም፥ እስራኤል ሊሰሙት ካለመውደዳቸው ባሻገር አጥብቀው ስለተቃወሙትና ሊቀበሉት ፈጽመው ስላልወደዱት ነው፡፡
    በዚህም ምክንያት በጥልቅ ሐዘን መዋጡን፥
    “አንጀቴ! አንጀቴ! ልቤ በጣም ታምሞአል፥ በውስጤም ልቤ ታውኮብኛል፤ ነፍሴ ሆይ፥ የመለከትን ድምፅና የሰልፍን ውካታ ሰምተሻልና ዝም እል ዘንድ አልችልም፡፡ … ሕዝቤ ሰንፈዋልና አላወቁኝም ሰነፎች ልጆች ናቸው፥ ማስተዋልም የላቸውም፤ ክፉ ነገርን ለማድረግ ብልሃተኞች ናቸው፥ በጎ ነገርን ማድረግ ግን አያውቁም፡፡”፤ (ኤር.4፥19-22)፤ “ተወግተው ስለ ሞቱ ስለ ሕዝቤ ሴት ልጅ ሰዎች ሌሊትና ቀን አለቅስ ዘንድ ራሴ ውኃ፥ ዓይኔም የእንባ ምንጭ በሆነልኝ! ሁሉም አመንዝሮች፥ የአታላዮች ጉባኤ ናቸውና ሕዝቤን እተዋቸው ዘንድ ከእነርሱም እለይ ዘንድ በምድረ በዳ የመንገደኞች ማደሪያን ማን በሰጠኝ? ምላሳቸውን ስለ ሐሰት እንደ ቀስት ገተሩ፤ በምድር በረቱ ነገር ግን ለእውነት አይደለም፤ ከክፋት ወደ ክፋት ይሄዳሉና እኔንም አላወቁምና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ወንድምም ሁሉ ያሰናክላልና፥ ባልንጀራም ሁሉ ያማልና እናንተ ሁሉ ከባልንጀሮቻችሁ ተጠንቀቁ፥ በወንድሞቻችሁም አትታመኑ፡፡ ሰውም ሁሉ ባልንጀራውን ያታልላል በእውነትም አይናገርም፤ ሐሰትን መናገርንም ምላሳቸው ተምሮአል፥ ክፉንም ለማድረግ ይደክማሉ፡፡”(9፥1-5)፤ “እረኞች ሰንፈዋልና፥ እግዚአብሔርን አልጠየቁትምና አልተከናወነላቸውም፥ መንጎቻቸውም ሁሉ ተበትነዋል፡፡”(10፥21)፤ “ስለ ነቢያት፤ ልቤ በውስጤ ተሰብሮአል አጥንቶቼም ሁሉ ታውከዋል፤ ከእግዚአብሔር የተነሣ ከቅዱስ ቃሉም የተነሣ የወይን ጠጅ እንዳሸነፈው እንደ ሰካራም ሰው ሆኛለሁ፡፡ ምድር ከአመንዝሮች ተሞልታለችና፥ ከመርገምም የተነሣ ምድር አልቅሳለች፤ የምድረ በዳ ማሰማርያ ደርቆአል፤ አካሄዳቸው ክፉ ነው፥ ብርታታቸውም ቅን አይደለም፡፡ ነቢዩና ካህኑም ረክሰዋልና፥ በቤቴም ውስጥ ክፋታቸውን አግኝቻለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡” (23፥9-11)
የሚለው የነቢዩ ንግግር የሚያየው የእስራኤል ክፋት ምን ያህል እንዳቆሰለውና እንዳሳዘነው በትክክል ይገልጠዋል፡፡

Tuesday 20 September 2016

በዘመን መለወጫ የተቀማጠለው ንጉሥ (የመጨረሻ ክፍል)

  please read in PDF

ልንመርጥ የምንችለው አንድ መንገድ ብቻ ነው፤ ከኃጢአትና ከጽድቅ መንገድ አንዱን፡፡ ከሁለቱ አንዱን እንጂ ለሁለቱም ማመቻመች አንችልም፡፡ “ከኃጢአት ጋር እየተጋደላችሁ ገና ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ አልተቃወማችሁም፤” (ዕብ.12፥4) የሚለው ቃል በእውነት ላይ እስከመጨረሻ አለመጽናትንና አለመጨከንን የሚያሳይ ነው፡፡ ለእውነት ከቆምን እስከሞት ድረስ እንጂ ሁለቱን ለማደላደል መሞከር ከውርደት አያድነንም፡፡
    የሳሙኤልን መጽሐፍ የጻፈው ጸሐፊ፥ በንጉሥ ዳዊት ሕይወት የሆነውን ውድቀት ሁሉ ምንም ሳያዛንፍ ነው፡፡ አስቡ! የነቢዩ ሳሙኤልን ሕይወት፥ “እነሆኝ በእግዚአብሔርና እርሱ በቀባው ፊት መስክሩብኝ የማንን በሬ ወሰድሁ? የማንንስ አህያ ወሰድሁ? ማንንስ ሸነገልሁ? በማንስ ላይ ግፍ አደረግሁ? ዓይኖቼንስ ለማሳወር ከማን ጋር እጅ ጉቦ ተቀበልሁ? እኔም እመልስላችኋለሁ፡፡ እነርሱም፦ አልሸነገልኸንም፥ ግፍም አላደረግህብንም፥ ከሰውም እጅ ምንም አልወሰድህም አሉ፤” (1ሳሙ.12፥3-4) በማለት ገልጦታል፡፡ እንዲሁ የዳዊትን ደካማና ኃጢአተኛ ሕይወት ሳያቅማማ ነው የገለጠው፡፡

Wednesday 14 September 2016

... አዲስ ዘመን የለም



ቢግተለተል ዕድሜ፥ ምን ቢረዝም ዘመን፤
ተቆጥሮ ተሰልቶ፥ ቢሰጠን ብዙ ቀን፤

Friday 9 September 2016

በዘመን መለወጫ የተቀማጠለው ንጉሥ (ክፍል አንድ)


Please read in PDF

እንኳን ለንስሐ የሚሆን ዘመን  ተጨመረላችሁ!!!
     ቅምጥልነትን፥ ቅዱስ ጳውሎስ “ቅምጥሊቱ ግን በሕይወትዋ ሳለች የሞተች ናት” (1ጢሞ.5፥6) በማለት ይገልጠዋል፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት መሞትን በሕይወት ቆሞ መሄድ አይተካውም፡፡ መንፈሳዊ ሞት ወደር የለሽ እጅግ አስጨናቂ ሞት ነው፡፡ ቆሞ በመሄድ ማማር የለም፤ በቁም “በውጭ አምረው የሚታዩ” ሁሉ ደመ ግቡዎች አይደሉም፤ ውስጣቸው “ርኩሰትም ሁሉ የተሞሉ በኖራ የተለሰኑ መቃብሮችን ሊመስሉ ይችላሉና”፤ (ማቴ.23፥27)፡፡ እንዲህ ያሉ ሰዎች በሕይወት የሞቱና ሕያውና የሚያድን ድምጽ መስማት የሚያስፈልጋቸው ናቸው፡፡
     ጌታችን “ሙታናቸውን እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው፤ አንተስ ሄደህ የእግዚአብሔርን መንግሥት ስበክ” (ሉቃ.9፥60) በማለት የተናገረው፥ በመንፈስ ሙት የሆኑ በሥጋ ሙት የሆኑትን ሊቀብሩ እንዳሉና በመንፈስ ሕያው የሆነ ግን የእግዚአብሔርን መንግሥት በብርታት ማገልገልና መስበክ እንዳለበት አጽንቶ ሊናገር ወዶ ነው፡፡ አስተውሉ! ጥቂት ቅምጥልነት ለምን አይነት መንፈሳዊ ሞት አሳልፎ ሊሰጠን እንደሚችል፡፡
   ንጉሥ ዳዊት ሁሉንም “ጠላቶቹን” ቢያሸንፍም፥ አሞናውያንን [1] ግን ገና አላሸነፈም ነበር፤ (2ሳሙ.10፥19)፡፡ እኒህ የቀሩ ጠላቶች ቢኖሩትም ግን፥ “እንዲህም ሆነ፤ በዓመቱ መለወጫ ነገሥታት ወደ ሰልፍ በሚወጡበት ጊዜ፥ ዳዊት ኢዮአብን ከእርሱም ጋር ባሪያዎቹን እስራኤልንም ሁሉ ወደጦርነቱ ሰድዶ ለራሱ ግን በኢየሩሳሌም ቆየ፤” (2ሳሙ.11፥1) አመሻሽ ላይ በዚያ ምቹና ተስማሚ ሰገነት ላይ (1ሳሙ.9፥25) ዳዊት ይመላለስ ነበር፡፡ በሌላ ንግግር ወደዳዊት ሕይወት ቅምጥልነት ሰተት ብሎ ገባ ማለት ነው፡፡ “በልክ መዝናናት” አንድ ነገር ነው፤ ለሥጋዊ ተድላና ለቅምጥልነት ተዘልሎ መቀመጥ ግን ራስን በወጥመድ ውስጥ የማስገባት ያህል እጅግ አደገኛ ነው፡፡

Sunday 4 September 2016

የኢትዮጲያ “መካከለኞች” ወዴት ናቸው?

Please read in PDF     

       ቺቸሮ “አለመግባባት መፍትሄ የሚያገኘው በሁለት መንገዶች በውይይት ወይም በኃይል ነው፡፡ የመጀመርያው የሰው ባሕርይ ሲሆን ሁለተኛው የአራዊት ነው” ይላል፡፡ ባለመታደል ሁላችንም ሁለተኛውን መረጥን፡፡ ማሸነፍ እንጂ መሸነፍን ያለመቀበል እንደባህል አድርገን በመያዛችንና በሃገሪቱ የፖለቲካ ልምድ ካለመኖር ጋር ተዳምሮ የኢትዮጲያ ተራማጆች ኃይልን መርጠው በመንቀሳቀሳቸው የደም መፋሰሱንና የጥፋቱን መጠን በማባባስ ለሃገር ግንባታ ይውል የነበረ ወጣት ለቅስፈት ተዳርጓል፡፡ (ሌ/ኰሎኔል ፍሥሐ ደስታ፤ አብዮቱና ትዝታዬ ፤ 2008 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ፤ ፀሐይ አሳታሚ ድርጅት)

       ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለ ማርያም “እርምጃ እንዲወሰድ ከማዘዛቸው” በፊትም ሆነ በኋላ፥ የሕዝብ ኩርፊያ አሁንም ጋብ ያለ አይመስልም፡፡ ሕዝብ እንደሚናጠቅ የአንበሳ ደቦል “በገዛ ወገኑ” [እርስ በራሱ] ላይ ያደባ ይመስላል፤ “መንግሥት ሆይ!  ችግር አለብህ፤ ተስተካከል” ለማለት እየሄደበት ያለው አቅጣጫና አንዳንዶች እንደሚሉት ሕዝቡን የሚመራው “ሦስተኛው አካል” ዓላማና ግቡ ምንም እንደሆነ በትክክል አለመታወቁ ነገሮች የበለጠ እንዲወሳሰቡ ያደረገ ይመስላል፡፡
     እርግጥ ነው፥ የአብዛኛው ሰው ስሜት ሲደመጥ፥ “ይኼ መንግሥት በቃው፤ ይውረድ” ይመስላል፡፡  ይህ አካሄዱ ግን ፍጹም ኢ መንፈሳዊነት ብቻ ሳይሆን ኢ ሰብዓዊነት፣ ኢ ሥነ ምግባራዊነትና ኢ ሞራዊነት የሰፈነበት መሆኑ ነገሩን አስጨናቂና እጅግ አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡ ምንድር ነው አስጨናቂና አሳሳቢ የሚያደርገው? ብንል፦
1.     ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ምን ሆነው? በማን ላይ ነው እርምጃ እንዲወሰድ አዝዣለሁ ያሉት? ከእርምጃው በፊት ማወያየትና ማነጋገር አይቀድምም ወይ? ምክር አይፈለግም ወይ? እርምጃ የመጀመርያ ደረጃ መቀራረቢያና መግባቢያ መንገድ ነው ወይ? ሕዝብን ማድመጥና ፍላጐቱን መጠየቅ አይገባም ወይ? በደፈናው ከመፈረጅ ጥንተ ምክንያቱን ማጥናት፤ መረዳት አይገባም ወይ? ወይም ለምንድነዉ መንግስት በፖለቲካ አቅጠጫ ማሸነፍ የተሳነው? የሚሉና ሌሎች ብዙ ጥያቄዎችን መምዘዝ ይቻላል፡፡