Wednesday 28 October 2015

ኢየሱስን የሚጋርዱ - ባህላዊ “ሰባኪ” ዎቻችን



       
                                                 Please read in PDF

     የክርስቶስ አገልጋይ ትጥቁ አጭር (ማቴ.10፥5-11) ፤ ዕለት ዕለት መስቀሉን ተሸክሞ በመከተል የሚኖር (ማር.8፥34) ፤በቁም ሳለ ከሚገድል ቅምጥልነት የራቀና “ወደዓለም ምንም እንኳ አላመጣንምና፥ አንዳችንም ልንወስድ አይቻለንም፤ ምግብና ልብስ ከኖረን ግን፥ እርሱ ይበቃናል።” የሚል ቅዱስ አቋም ያለው (1ጢሞ.5፥6 ፤ 6፥7-8) ፤ በሕይወቱ (ሮሜ.12፥2) ፣ በንግግሩ (ቈላ.4፥6) ፣ በመንገዱ ሁሉ የአምላኩን ስም የሚያስመሠግንና ከማስነቀፍ ፈጽሞ የራቀ ፤ ለሁልጊዜ ለፈጣሪው የሚያደላና የሚኖር ፤ ለሕይወቱ ምሳሌና መርሕ የሚሆነውን ነገር ለመፈለግ ሁልጊዜ እግረ ልቡን ወደ ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ የሚያቀና ሊሆን ይገባዋል፡፡ (ሐዋ.17፥10 ፤ 1ዮሐ.4፥1)
እንዲህ ስል አገልጋይ ባዕለ ጠጋ መሆን የለበትም የሚል አቋም የለኝም ፤ ዳሩ ግን አማኝም ሆነ አገልጋይ መሠረታዊ የሆነውን ነገር፥ ማለትም ምግብን ፣ ልብስንና መጠለያ በማግኘቱ ፣ እርካታ ይኖረው ዘንድ አስፈላጊ ፤ የተገባም ነው፡፡ ይህ ማለት አገልጋይ እንደሚሠራው ሁሉ አገባብ ያለው ደመወዙ ይገባዋል ማለት ነው፡፡ እንዲሁ ገንዘብ የሚጠይቅ የተለየ ነገ ርቢከሰት ፣ በልግስና በመስጠት እግዚአብሔርን እያገለገለ (2ቆሮ.8፥3 ፤ 9፥6) “በመከራ ቀን ጥራኝ፥ አድንህማለሁ አንተም ታከብረኛለህ።” እንዲል፥ እግዚአብሔር እንዲሰጠው ወደእርሱ መመልከት ይኖርበታል፡፡ (መዝ.50፣15) ይህንን የምንለው ሁልጊዜ መንግሥቱንና ጽድቁን መቅደምና ማስከተል ከሌለብን ብቻ ነው፡፡ (ማቴ.6፥33)

Friday 23 October 2015

የፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ንግግር ሳጤነው ምጥ አለበት!!!


ብዙዎች ያልጨከንለትና ያልደፈርንለት እውነት!!!

      በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በተካሄደው 34  መደበኛ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ፥ ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጥቅምት 8 ቀን  2008 ዓ.ም ካስተላለፉት አባታዊ መልዕክት የሚከተለው መልዕክት ላይ ማተኮር ፈለግሁ፡፡
 
“ … የምዕመናን ፍልሰት በየጊዜው እየጨመረ የመሄዱ መነሻ ምስጢር ምንድን ነው? የሚለውን ጥያቄ ቤተ ክርስቲያናችን በአጽንዖት ልታጤነው ይገባል ፤ በዚህ ዙርያ የሚታየው ክፍተት ፈጣን ምላሽ በመስጠት መግቻ ካላበጀንለት ነገ ከባድ የሃይማኖትና የታሪክ ወቀሳ ማስከተሉ እንደማይቀር ልብ እንበል፡፡
     ለመሆኑ ምዕመናን ከቤተ ክርስቲያናችን እየወጡ  ወደሌላ ካምብ ለመግባት ለምን መረጡ?
-       የሚያስተምራቸውን ካህን አጥተው ነውን?
-       የቤተ ክርስቲያናችን ትምህርተ ሃይማኖት ክፍተት ኖሮት ነው?
-       የቤተ ክርስቲያችን አስተዳደር የማያረካ ሆኖ ነውን?
-       የካህን እጥረት ስላለ ነውን?
-       ወይስ ሌሎች ከእኛ የተሻሉ ሆነው ስለተገኙ ነው፤?
የዚህ ሁሉ መልስ በእያንዳንዳችን ኅሊና ውስጥ ቁልጭ ብሎ ስለሚታወቅ የጥያቄው መልስ ለእናንተው ሰጥተናል፡፡  … ”

     ደግሞም ልቀጥል፦ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መጀመርን አስመልክቶ ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም  ቅዱስነታቸው በሰጡትም መግለጫም እንዲህ አሉ፦

Wednesday 21 October 2015

ድንግል ማርያም በድንግል ማርያም አንደበት ክፍል - 5






4.  በመንፈስ ቅዱስ ደስታ የተመላችም ነበረች

     ደስታ ከመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች አንዱ ነው፡፡ (ገላ.5፥22) ደስታ፥ የመብልና የመጠጥ ፣ በወገን መካከልም የመቀመጥ ፣ በተድላ የመንቀባረር ፣ የመልበስና የማማር ጉዳይም አይደለም ፤ ተድላና ደስታን ለማየት ለመቅመስም የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ያሻል፡፡ “ያለ እርሱ ፈቃድ የበላ ደስ ብሎትም ተድላን የቀመሰ ማን ነው?” (መክ.2፥25) እንዲል ደስታችንም ፍጹም የሚሆነው በእርሱ ብቻ ነው፡፡ (ዮሐ.15፥11) ዘወትር ለሁልጊዜ በጌታ ልንደሰት እንደሚገባንም ቃሉ ይነግረናል፡፡ (ፊልጵ.4፥4 ፤ 1ተሰ.5፥16)
    ድንግል ማርያም ትልቁ ሐሴትና ደስታዋ በእግዚአብሔር መድኃኒትነት ላይ ያላት መደገፍ ነው፡፡ “መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች” የሚለው መዝሙሯ፥ “እግዚአብሔር ሕያው ነው፥ አምላኬም ቡሩክ ነው፥ የመድኃኒቴም አምላክ ከፍ ከፍ ይበል።” (መዝ.18፥46) ከሚለው ከዳዊት መዝሙር ጋር ፤ “ … የጽድቅንም መጐናጸፊያ ደርቦልኛልና በእግዚአብሔር እጅግ ደስ ይለኛል፥ ነፍሴም በአምላኬ ሐሤት ታደርጋለች።” (ኢሳ.61፥10) ከሚለው ከኢሳይያስ መወድስ ጋር ፤ “ … እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ።” (ዕንባ.3፥18) ከሚለው ከዕንባቆም የጽናት ዝማሬ ጋር ፍጹም የሚዛመድ ነው፡፡

Tuesday 13 October 2015

አድመኝነት - ከማን የተማርነው ነው?



      
                                   Please read in PDF
            

   ጌታ ኢየሱስ በተያዘባት በሐሙስ ማታው ግርግር፥ ደቀ መዛሙርት አይሁድ ጌታን ቆርጠው ለመግደል በብዙ ጦርና አድማ ተደራጅተው ምክራቸውን እንደጨረሱ ሲያውቁ ፦ “ጌታ ሆይ፥ እነሆ፥ በዚህ ሁለት ሰይፎች አሉ አሉት።” (ሉቃ.22፥38) የአይሁድ የካህናት አለቆች ሙሉ ለሙሉ በአድማ ሲነሳሱ ስላዩ፥ ደቀ መዛሙርቱም ምላሽ ለመስጠት በሰይፍ ለሚያስታጥቅ አድማ ለራሳቸው ተዘጋጁ፡፡ ጌታ ኢየሱስ እንዳያደርጉት በምፀት ቃል “ይበቃል” ቢላቸውም፥ እነርሱ ግን ቃል በቃል ተርጉመው፥ አድማቸውን ወደጥቃት አሸጋግረው የአንዱን ወታደር ጆሮ በመቁረጥ ደመደሙ፡፡ ጌታ ግን “ሰይፍ የሚያነሡ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉና ሰይፍህን ወደ ስፍራው መልስ።” በማለት በተግሳጽ ቃል ተናገረ፡፡ (ማቴ.26፥52)
     ደቀ መዛሙርቱ ጌታ ከእነርሱ ጋር የተስማማ መስሏቸው ይህን ቢያደርጉም፥ ጌታ ግን ድርጊቱን አብዝቶ ተጠይፏል፡፡ በእርግጥም አድመኝነት የሥጋ ፍሬ ነው ፤ (ገላ.5፥20) ትርጉሙንም ስናሰላስለው ለመለያየት የመጀመርያ ምልክት የሆነ ፤ የግል መሻትና ፍላጎት ባላቸው ሰዎች መካከል የሚፈጠር መለያየት ፤ በፍጻሜም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት የሚያጠፋ  ወይም የሚቃወም ድርጊት ነው፡፡ ይህም በአንድ ሃሳብ የሚስማሙና የግል ሃሳባቸውን የሚያስቀድሙ ሰዎች ወገናዊነትን ፤ እኛዊነትን ፤ እኔዊነትን በመፍጠር ፥ በሌላው ላይ በማሾክሾክ ፤ በማማት ፤ በመጥላትም ጭምር ራሳቸውን በማግለል ቡድናዊነትን በመመሥረት በሌላው ላይ የበላይነትን ለማሳየት የሚያደርጉት ድርጊት ነው፡

Wednesday 7 October 2015

አንተ ስትደክም …


          Please read in PDF                     


ብትጠቁር ብትከሳ
ብትሞግግ በአበሳ
አጀቡ የሐዘን
ምትክህ ሰቀቀን …

Friday 2 October 2015

ግብረ ሰዶማዊነትን ለመቃወም ሙጋቤያዊ አቋምም ከመሪዎቻችን ያስፈልጋል!

   
                          Please read in PDF     

                        እኛ ግብረ ሰዶማውያን አይደለንም!!!” (ሮበርት ሙጋቤ)


    በዘመናችን መንፈሳዊ ማንነታችን ስለተጐሳቆለብን ኃጢአትን በአለም መድረክ የሚቃወሙት አለማውያን መሪዎች፥ ከእኛ ይልቅ በብዙዎች ዘንድ የመደመጥን ዕድል ያገኙ ይመስላል፡፡ ቤተ ክርስቲያን በቅድስና ፍጹም ስትዋብ በአለማውያን መሪዎች ላይ ተጽዕኖ ስለማሳደሯ ምንም ጥርጣሬ የለውም፡፡ ከቤተ ክርስቲያን መለያ ባሕርያት መካከል አንዱ ክርስቶስ በገዛ ደሙ መሥርቷታልና ቅድስት መሆኗ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የቅድስናን ጠባይ ገንዘብ ያደረገችው፥ ከመሠረታትና ቅድስና የባሕርይ ገንዘቡ ከሚሆን ከክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡
     ቤተ ክርስቲያን ከአለማውያን መሪዎች ጋር ያላት ግንኙነት እጅግ ጤናማ መሆን አለበት፡፡ ግንኙነቱ ጤናማ መሆን አለበት ስንል፥ መርሑ ቅድስናና ንጽሕናን ብቻ በተከተለ መንገድ መሆን መቻል አለበት ማለታችን ነው፡፡ ቅድስና በኃጢአተኛው ላይ እጅግ ከፍ ያለ ተጽዕኖ ማሳደር ይችላል፡፡ በቤተ ክርስቲያን በስደት ዘመን የሰማዕታትን አንገት ይቀሉ የነበሩት ወታደሮች፥ በሚያስደንቅ መንገድ የጌታ ባለሟሎች የሆኑትና ከመግደል ለጌታ እስከመሞት የደረሱት የሰማዕታቱን የቅድስና ጉልበት አንገት በመቁረጥ ፤ በማቃጠልና በብዙ መከራ ማሸነፍ ስላልቻሉ ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር የክርስቶስ ኢየሱስን ሕይወትና ቃሉን እጅግ በመውደድና በማንበብ ለአገራቸው ሕዝቦች እጅግ ቅን የነበሩትን እንደመሃተመ ጋንዲ ያሉ መሪዎችንም ማንሳትም ይቻላል፡፡