Thursday 28 July 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል አንድ)

Please read in PDF
ያለነው እንደሸማኔ መወርወርያ በሚፈጥነውና በሚቸኩለው ዘመን ፤ ኃጢአትም ከተመሸገበትና ካደባበት ሥፍራው ላይ መገለጥና “እነሆ አለሁ” በሚለው አካላዊ ማንነቱን ማሳያ ዘመን ላይ ነን፡፡ ከቀደመው ዘመን ይልቅ የኃጢአት ጽዋ በዓለም መካከል ብቻ ሳይሆን “የእግዚአብሔር ነን” በሚሉትም መካከል እየሞላና እየፈሰሰ መሆኑን እያስተዋልን ነው፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ፦ “ … ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል” (2ጴጥ.3፥9) እንዲል እየሆነ ያለው እግዚአብሔር ስለሌለ አይደለም፡፡

Friday 22 July 2016

ትልቅ ነው አምላኬ

Please read in PDF

ከፍ ከፍ በል ጉላና ድመቅ
ወገብህን አጽና ዝናርህን ታጠቅ
መስባትንም ስባ
ለድልደህም ወፍር
ሙሉ ብረት ለብሰህ ሸልልና ፎክር
በል በልብህ ጀምር ከ’ኔ ማን ሊወደር?

Thursday 14 July 2016

“የ‘ፌስቡክ’ ትውልድ” (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF
ምን እናድርግ?
1.     በእኒህ ማኅበራዊ የመረጃ መረቦች ላይ የሚጠቅመንንና መንፈሳዊ ነገሮቻችንን ብቻ ልናስተላልፍበት ፤ እንዲሁም የምናየውን ፣ የምናደምጠውን ፣ የምናነበውን ... ከእግዚአብሔር ቅዱስ ቃል ጋር የሚያቃርነን ነገር እንዳይሆን በብርቱ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የተጠራነው በቅድስና ሕይወት እንድንኖር ነው ፤ እርሱ የጠራን ቅዱስ ነውና(1ጴጥ.1፥14-16)፡፡
    “አባታችን ሆይ”፥ ብለን እግዚአብሔርን በጸሎት ከጠራን፥ እንደእግዚአብሔር ልጆች ለፈቃዱ ብቻ ልንታዘዝ ይገባል፡፡ እርሱ ፈቃዱ ቅድስና ነው፡፡ ቅድስና ከኃጢአት ከርኩሰት ተለይቶ ፤ ለእግዚአብሔር ብቻ መሆንን የሚፈልግ ዓቢይ ጉዳይ ነው፡፡ ሁላችን በየትኛውም ጉዟችን “ቅድስና ለእግዚአብሔር” የሚል አዲስ ኪዳን በክርስቶስ ኢየሱስ ገብተናል፥ ለዚህ ኪዳናችን ታማኞች በመሆን ሁሉን እንደቃሉ ልንመረምር ይገባናል፡፡

Tuesday 5 July 2016

“VOA”ና ባልንጀሮቹ ከኃጢአት በቀር “ሥርየት”ን መች ይሆን የሚዘግቡት?

   በኃጢአት ውድቀታችን የሰይጣን ልጆች ስንሆን፥ በትንሣኤ ልቡና በምናደርገው የንስሐ መመለስ ደግሞ ከክርስቶስ ሞትና ከትንሣኤው ኃይል የተነሣ የእግዚአብሔር ልጆች እንባላለን፡፡ ማደፍ ፣ መርከስ ፣ መውደቅ የሥጋ ባሕርይ ነውና ሁላችን በዚህ በኩል፥ “ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ፤ አስተዋይም የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚፈልግ የለም፤ ሁሉ ተሳስተዋል፥ በአንድነትም የማይጠቅሙ ሆነዋል፤ ቸርነት የሚያደርግ የለም፥ አንድ ስንኳ የለም። ... አፋቸውም እርግማንና መራርነት ሞልቶበታል፤ ...” (ሮሜ.3፥11-14) የሚለው ፍርድ የአዳምን ልጆች ሁሉ አጊኝቷቸዋል፡፡
    እናምናለን፤ ሁላችንም ያለክርስቶስ የሚታይ ምንም መልካምነት የሌለን ከንቱዎች ፤ የእግዚአብሔር ክብር የጐደለን እርባና ቢስ ነን፡፡ ለዚህም ነው ክርስቶስ ከነበርንበት ጨለማነት ፣ ጠላትነት ፣ የቁጣና ያለመታዘዝ ልጅነት ፣ የኃጢአት ባርያ (ሮሜ.6፥20) የኃጢአተኝነት ሕይወት ፍጹም በማውጣት ወደሚደነቅ ብርሃን ፣ ወዳጅነት ፣ የመታዘዝና የእግዚአብሔር ልጅ ወደመሆን በደሙ አጽድቆ ፣ ቀድሶ ያፈለሰንና ወደአባቱም ንጹሐንና ነውር የሌለባቸው አድርጐ ያቀረበን፡፡