Thursday 30 January 2014

ቃሉ “የማይሰራ አይብላ” አይልም!!! (ክፍል - 1)


Please read in PDF :- kalu Yemaysera aybila aylim(part 1)

       እግዚአብሔር ሠራተኛ ነው፤ ይሠራል፡፡እግዚአብሔር አገልጋይ ነው፤ ያገለግላል፡፡በፍጥረት መጀመርያ እግዚአብሔር ለፍጥረቱ የተገለጠው ሠራተኛና ሠሪ ሆኖ ነው፡፡ፍጥረትን በዝምታ፣በቃሉና በድርጊት ፈጥሯል፡፡ሠራተኛ ነውና ሲሰራ አይተነዋል፡፡የሠራውንም ለዓይኖቻችን ድንቅ ሆኖ አይተነዋል፡፡በአስገኚነቱና በፈጣሪነቱ የሚታወቀው ቀዳማዊ አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ “ሁሉ በእርሱ የሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ ያልሆነ”(ዮሐ.1÷3) ፣ብርቱና አስገኚ ጌታ ነው፡፡ሁሉ በእርሱ የሆነው ጌታ እግዚአብሔር ወልድ አዛዥ የሌለበት ሠራተኛ ነው፡፡
       እግዚአብሔር እርሱን እንድንመስልበት ከሰጠን ጠባዩ አንዱ ሥራ ነው፤እርሱ ሥነ ፍጥረትን ፈጥሮ በሠራዒነቱ እንደሚንከባከብ ሁሉ የመጀመርያው ሰው አዳምንም ምንም ባልጎደለባት የተድላይቱ ምድር “ … ያበጃትም ይጠብቃትም ዘንድ በዔድን ገነት አኖረው።”(ዘፍ.2÷15)ይለናል፡፡ የመጀመርያው ሰው ሁሉንም በጸጋ ያገኘውና የተሠጠው ቢሆንም ሥራ ፈት እንዳይሆን የማስተዳደርና የመንከባከብ የሥልጣን ሥራ በዚያ ሥራ ወዝና ድካም በማይጠይቅበት በገነቱ የጸጋ ዘመን ተሰጠው፡፡

Tuesday 28 January 2014

የኢየሱስ ደም - የመጨረሻ ክፍል


7- ደሙ መካከለኛችን ነው፡፡


ከጥንት “… በሀሳባችን ጠላቶች” … “ … ከፍጥረታችንም የቁጣ ልጆች የነበርነውን” … “አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቀን፡፡”(ቆላ.1÷22፤ኤፌ.2÷3) ከመጀመርያው የሀሳብ ጠላትና የቁጣ ልጆች የነበርነውን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአባቱ ጋር ሊያቀራርበን እንደያዕቆብ መሰላል መካከለኛ ሆኖ ተገለጠ፡፡ቅዱስ ሄኔሬዎስ እንዲህ አለ፦
          “አባታችን ያዕቆብ ወደሜሶፖታምያ በሚጓዝ ጊዜ ፣በህልሙ እርሱን /ወልድን/ አየው፡፡
           መሰላል ቆሞ(ዘፍ.28÷10-15)፤እርሱም ከምድር እስከሰማይ የተዘረጋ ዛፍ ነው፡፡በእርሱም
          ምዕመናን ሁሉ ወደመንግስተ ሰማያት ይደርሳሉ፡፡የእርሱ መከራ መስቀል ለእኛ ወደላይ 
          መውጫ መንገዳችን ሆኗልና፡፡”(ዳንኤል ክብረት(ዲያቆን)፡፡አበው ምን ይላሉ?፡፡
           (1999)አሳታሚና አከፋፋይ ማህበረ ቅዱሳን፣ቦታ አልተጠቀሰም፡፡)
      በእርግጥም ወንጌል የመሰከረለት በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የተዘረጋው መሰላል ክርስቶስ ነው፡፡(ዮሐ.1÷52)ክርስቶስ መካከለኛ የሆነው ሰው ሆኖ ፤ደሙን አፍስሶ በሠራልን የቤዛነቱ ሥራ ነው፡፡ክርስቶስ በፍጹም ሰውነቱ እኛን ፤በፍጹም አምላክነቱ ደግሞ እግዚአብሔርን ወክሎ ሁለታችንን ያቀራረበ መካከለኛ አማኑኤል ነው፡፡እርሱወደአባቱ ለመድረስ ጐዳና ፤ወደወለደው ለመግባት የሚሆን በርነው፡፡ጎዳናው ልክ እንደመሰላሉ ከምድር እስከሰማይ የሚደርስና የቀናም ነው፡፡በዚህ መካከለኛነቱምየአብ ሊቀ ካህናት የሚሆን እርሱ የሰውን ባህርይ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀ፡፡”(መጽሐፈ ቅዳሴ ጕልህ፡፡(1994)፡፡አዲስ አበባ፣ትንሳኤ ማተሚያ ድርጅት፡፡ገጽ 146፤የቅዳሴ ሥርዐት ገጽ.82)


Saturday 25 January 2014

ነፃ አወጣን


በራሣችን ፈርደን የሞት ኑሮ ስንኖር፤
በመንፈሰ ደይን ባርያዎች ተብለን፤
በኃጢአት ጭቅቅት ጠረናችን ጠፍቶ፤
የነፍስ ገላዋ በዕድፈት ተበላሽቶ፤
ያልፈጠረን ጌታ በዕዳ ጽህፈት፤

Tuesday 21 January 2014

የኢየሱስ ደም - ክፍል ስድስት

    Read in PDF:
    6- ደሙ ከኃጢአታችን ሁሉ ያነጻናል፡፡

“የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።” (1ዮሐ.1÷7)

“… እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ።” (1ዮሐ.2÷2)

“… እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፥ ልብሳቸውንም አጥበው በበጉ ደም አነጹ።” (ራዕ.7÷14)

“በአንድ ልጁ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ከኃጢአታችን መዳንን የሰጠን ፤የሁሉ ህይወት ወደእርሱ የሚሸሹትን የሚረዳ ወደእርሱ ለሚጮኹ ሰዎች ተስፋቸው፡፡” (የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ)

“ጥበብ ግን መድኃኒታችን ነው በሥጋው መሥዋዕትነት ያዳነን በደሙም ፈሳሽነት የተወዳጀን ለመንግስቱም የመረጠን...”(የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ)
       ጌታ በመዋዕለ ሥጋዌው ከአይሁድ የገጠመው ዋናውና ትልቁ ተቃውሞ ኃጢአትን ይቅር ስለማለቱ ነው፡፡(ማር.2÷6)በእርግጥም ኃጢአትን ይቅር ማለት የሚቻለው አምላካዊነት ባህርይ ያለው አካል ብቻ ነው፡፡አይሁድ በዚህ ምክንያት ኢየሱስን እስከሞት ጠሉት፡፡ክርስቶስ ኃጢአትን ይቅር የማለት ሥልጣን እንዳለው በግልጥ አሳይቷል፡፡ይህ ግን ለአይሁድ እግዚአብሔርን እንደመናቅ ያለ ታላቅ ስድብ ነበር፡፡ለዚህም ነው ሉቃስ በወንጌሉ “ … ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢአት ሊያስተሰርይ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ ብሎ … ” በማለት በግልጥ የፃፈልን፡፡(ሉቃ.5÷24)

Friday 17 January 2014

ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ፡፡(ማቴ.3÷8)

Read in PDF

የስሙ ትርጓሜ “እግዚአብሔር ፀጋ ነው” ማለት ነው፤የተወለደው “በጌታ ትዕዛዝ ህግጋት ሁሉ ያለነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ከነበሩት” ከቅድስት ኤልሳቤጥና ከካህኑ ዘካርያስ ነው፡፡(ሉቃ.1÷6)፡፡ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ኃጢአትን ያልሰሩ ጻድቃን አልነበሩም ነገር ግን የእግዚአብሔርን ህግና ሥርዓት በማክበር ታማኞችና እጅግም ቅኖች ነበሩ፡፡የእግዚአብሔር ቅዱሳን ህይወታቸውን በንስሐ ያጠሩ ብቻ ሳይሆኑ ፤ንስሐቸውም ፍሬ የሚያፈራና የሚታይ ህይወት የሚነበብበት ነው፡፡ኤልሳቤጥና ዘካርያስ ህይወታቸው በእግዚአብሔር ፊት ያለነቀፋ የሆነውን ያህል በሰውም ፊት ነውር ያልነበረባቸው ነበሩ፡፡
     በሌላ ንግግር ኤልሳቤጥና ዘካርያስ ስም ብቻ ያልነበራቸውና ያልከበዳቸው አማኞች ነበሩ፡፡ለታመኑለት ጌታ የሚታመንና በፍሬ የሚታይ ህይወት ነበራቸው፡፡ዛሬ ክርስትናችንን ከሚያስነቅፉብን ነገሮች ዋነኛውና ትልቁ “ክርስቲያን የሚለው ስም አለን ነገር ግን ስሙ በእኛ የማይሰራ ሙትመሆኑ ነው፡፡(ራዕ.3÷1)፡፡ክርስቲያን ተብሎ የሚጠራው ጥቂት የማይባለው ማህበረሰብ የነጠላ ያህል በነውር ካጌጠ ፣የላንቃ ያህል በዝሙት ከተቆነጀ፣በጉበኝነት ከተሞሸረ፣አለልክ በማግበስበስና በስግብግብነት ከተካነ …  ዘመን ቆጥሮብናል፡፡

Wednesday 15 January 2014

አድጎ ያፈራ 'ለት


ሳንጀምረው ፈርተን
ሳንቀርበው ርቀን
ሳንሻገር ቆመን
እሾሁን መንጥረን
ኩርንችቱን ነቅለን
ካ'ንድም ሁለት ሶስቴ ሳንጎለጉል ደክመን
እርፍና ሞፈሩን ቀንበርም አጣምደን
የእርሻና የዘር ወራቱን ታግሰን
ብናርስ ብንኰተኩት
በዓላማ በጽናት፤

Sunday 12 January 2014

ነጻነትን ለኃጢአት?

ከበለዐም መርገም አስማትና ምዋርት
ከባላቅም ምክር ቃየላዊ ክፋት
እስራኤል አምልጧል ከበዛው ተግዳሮት
ቀስቱ ተቀንጥሶ ወጥመድ ተሰብሮለት፡፡
           ተሽሯል እርግማን ኃይል አጥቷል አስማቱ
           የሠራዊት ጌታ ጣልቃ በመግባቱ
           በአህያ አንደበት የታላቁ ነቢይ ታግዶ እብደቱ፡፡

Wednesday 8 January 2014

የኢየሱስ ደም (ክፍል - አምስት)



3-ደሙ የተዋጀንበት ዋጋችን ነው፡፡

              “በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደሌለው እንደ
               በግ ደም በክቡር የክርስቶስ ደም እንደ ተዋጃችሁ ታውቃላችሁ።
                   (1ጴጥ.1÷19)
      “ዋጀየሚለውን መዝገበ ቃላቱገዛ፣ካሳከፈለ (ከሞት፣ ከባርነትለማዳን)፣አዳነብሎ ይፈታዋል፤ (ኣማርኛ መዝገበ ቃላት፡፡(2001)፤ አዲስ አበባ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ማተሚያ ቤት፡፡ገጽ.426) ውጅት ማለት ቀድሞ የራስ የነበረን ንብረት በኋላ ግን ከዋናው ባለቤት ወጥቶ ወደሦስተኛ አካል የገባን ዋጋ ያለውን ሀብት የሚያስፈልገውን ሁሉ ቅጣት በመቀበልና ዕዳውን በመክፈል ነጻ ማውጣትና የራስ ማድረግ ማለት ነው፡፡በዚህ አገባብ ከጥንት የእግዚአብሔር የነበረው ታላቁ ሀብት የሰው ልጅ በገዛ ነጻ ፈቃዱ ወደዲያብሎስ ፈቀቅ በማለቱ ክርስቶስ ኢየሱስ ሰው ከእግዚአብሔር ፈቀቅ በማለቱና ኃጢአት ሠርቶ ሊቀበል የሚገባውን መራራ መከራና ሞት (ቅጣቱን) ተቀብሎ፤ዕዳውን ሁሉ በመክፈል በገዛ ደሙ የሰውን ልጅ ገዛው፡፡
     የተዋጀነው በቀዳሚነትከሕግ እርግማንነው፤ (ገላ.3÷13) እርሱ ስለእኛ የተረገመ ሆኖ እኛን በሕጉ ከመረገምና ሕግን ባለመፈጸም ከሚመጣብን የሞት እርግማን ዋጀን፡፡ እርግማናችን ሁሉ በመስቀሉ ተጠርቆ ከመንገድ ተወግዷልና አሁን እኛ በመስቀሉ ሥራ፤ በክርስቶስ ሞትና በደሙ ተዋጅተን ንጹሐን ሆነናል፡፡ በቀጣይነት የተዋጀነውከአመጽ ሁሉነው፤ (ቲቶ.2÷14) በሐዲስ ኪዳን ጸሐፍት ኃጢአት ሁሉ አመጽ ነው፤ (1ዮሐ.5÷17) ክብር ይግባውና ከእንዲሁ ምህረቱ የተነሳ መድኃኒታችን በመድኃኒት ደሙ አዳነን፡፡