Friday 28 February 2014

Waaqni Guddaan akka nu ilaalutti !!! (kutaa – 2)

Please read in PDF

   

Yoosef akka namni isa ilaalutti hinjiraatu.osoo akka namni isa ilaalutti jiraate Yoosef fedhinna isaa raawachuudhaaf haalli hundi isaaf mijaa’e jira.haalalummaa raawachuuf isheen fedhinnaa niqabdi,namni isaan argu hinjiru,sireen tolfamee miidhagee jira, … wanti hundi dhoksaadhaan raawatamuu ni danda’ama.kun hundi garuu akka namaatti malee akka Waaqayyootti wanti dhoksaa ta’e hinmula’ane tokkoleen hinjiru.isa duratti dukkani ifa dha.isa duraas fagaachunis ta’e dhokachuun bakka inni hinjirretti jiraachuun hindanda’amu.(Miil.7÷8,Faar.138÷12)
     Qulqulluun Yoosef wanti hundi isaaf mija’a ta’us; isheenis isa kadhachuu qofa osoo hintaane fiigdee “koottu ana wajjin halaalummaa raawadhuu” jettee yemmuu qabdu “ani Waaqayyoo duratti akkamitti cubbuu raawadha!?” jedhee huccuu harka isheetti dhiisee fiigaati ala bahe.sababii kanaan sobaan himatamee mana hidhaa seene.bareedini fi dargagummaan Yoosef kan barbaadame qulqulluumaafi osoo hintaane xuraawamudhaaf. Hara’as bareedina ofiif barbaadu malee bareedini Waaqayyoof nama jedhu arguun ni danda’amaa laata?! Biyyi lafaa tun dargagoota qulqullumaaf kan barbaadus miti;humnaa fi sammuu isaani sababii adda addaatiin xureesuuf malee.

Tuesday 25 February 2014

ከሰማይ የወረደው (ዮሐ.3÷13)



ያለንበት ጊዜው የአዋጅ ጾም ወቅት ነው፡፡የጾሙ ቀዳሚው ሳምንት ስያሜ ደግሞ ዘወረደ፡፡ቅዱስ ያሬድ የጌታን የጾም ወራት ሳምንታትን በሥያሜ ከፋፍሎ ከጌታ ትምህርትና ህይወት ጋር ቃኝቶ እንድንገለገልበት አደላድሎ አስቀምጦታል፡፡ጾሙ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ከስያሜው ጋር ፍጹም ተዛምዶ ያላቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ንባባትና ዜማዎች ይሰበካሉ፡፡አሁን ላለንበት ሳምንት ከስያሜው ጋር የሚስማማ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ በርዕሳችን የጠቀስነው ነው፡፡
     ኒቆዲሞስ የሰማው ነገር እጅግ ግር አሰኝቶታል፡፡የአይሁድ አለቃና የእስራኤል መምህር ቢሆንም አሁን እየሰማ ላለው ትምህርት እንግዳ ነው፡፡መንፈሳዊ ለመሆን መሰረቱ ህልቅናና ሥልጣን ቢሆን ኖሮ ኒቆዲሞስ ያን ያህል ግራ ባልተጋባ ነበር፡፡ዳግም መወለድ ለሥጋ አዕምሮና ለዚህ ዓለም ማስተዋል የሚገባ(የሚረዳ) አይደለም፡፡ክርስቲያን ከማመን ይልቅ በማየት የሚመላለስ ከሆነ ከአለማውያን ይበልጥ ይዝላል፡፡ብፅዕና በማመን እንጂ በማየት አይደለምና፡፡(ዮሐ.20÷29)
   የሥጋ አይናችን የዚህ ዓለም ብርሃን (ፀሀይ፣ጨረቃ፣መብራት …) ካልተዋሃደው ማየት አይችልም፡፡ በተዋሐደው ጊዜ ግን በዚህ አለም ብርሃን የዚህን አለም ነገር ያያል፡፡ መንፈሳዊውን ዓለም በማመን ለማየት ከዚህ ዓለም ያልሆነ ብርሃን ያስፈልገናል፡፡ሰማያዊውን ዓለም የምናየው ከዚህ ዓለም ባልሆነ ብርሃን ነውና፡፡አልያ ግን “ማየት ማመን ነው” የሚለው አባባል “ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል?” የሚለውን ኒቆዲሞሳዊ ጥያቄ አይመልስም፡፡ የእግዚአብሔር ብርሃንነት ከፍሎ አያሳይም፡፡ብርሃኑ ፍጹም ነውና አጮልቆ ወይም በጨረፍታ አያይም፡፡“በብርሃንህ ብርሃንን እናያለን” እንዲል፡፡(መዝ.35(36)÷9)

Wednesday 19 February 2014

የማይቆም ድምጽ አለ !



ተቻኮልና ሂድ
  አትቁም ከመንገድ
  ደፍረህ ተናገረው
  ጩህና ስብከው
         አትዘግይ ወደኋላ
         ፈልቶ በዝቶ ተኩላ
         አትተኛ ንቃ በክርስቶስ ብርሐን
         ጮኸህ ተናገረው የወንጌሉን መዳን

Monday 17 February 2014

Waaqni Guddaan akka nu ilaalutti !!! (kutaa – 1)

Please Read in PDF


             Waaqni Guddaan akka nu ilaalutti !!! (kutaa – 1)
http://abenezerteklu.blogspot.com/
      Gatii keenya isaa bara baraa wantoota nujalaa dhabamsisan keessa inni  tokkoofi guddaan jiruun keenya akka Gooftaan guddaan ilaalutti osoo hintaane akka namni nuargutti waan jiraanuuf dha. Qulqullumaan keenya kan madaalamu ijaa fi ilaalcha namaatiin osoo hintaane ijaafi jecha wangeela Waqayyotiin.Warrotni Waaqayyoof bullee jedhan hedduun isaani qulqulluumaan isaani akka nama duratti mula’utuuf malee akka Waaqayyoo duratti mula’utuuf hedduu hineegatan.
    Yeroo bayyee namootni nama duratti shakki malee qulqulluu ta’u danda’u; garuu Waaqayyoo duratti namootni qulqulluu ta’an yeroo baayye fudhatama namaa hinargatan. Jechi Waaqayyoo seenaa Yoosef yemmuu ibsu “Waaqayyoo Yoosef wajjin ture hojiin isaas nama raawatameef ta’e” jedha.(Uuma.39÷2) Yoosef jibbinsa obboleewwan isaa isaaf qabaniin mana abbaa isaa irraa fagaatee, gabrummaadhaaf gurguramee biyyaafi namoota hinbeekne jiddu kan jiraatu ta’us inni garuu “namni na beeku hinjiru,kanaaf yoo of jijjiiree cubbuu raawadhe hoo?” Jedhee ofiif bilisummaa cubbuu hinlabsine.namoota muraasaan alatti barumasaaf, jireenyaaf,hojiidhaaf … namootni yeroo teessoo isaani jijjiiratan gaarumman isaanitis wajjin jijjiirama. Bakka deeman hundatti akka uumaan isaani isaan argutti osoo hintaane waanuma nama beekan irraa fagaataniif ija Waaqayyoo duraas waan fagaatan isaanitti fakkaata.

Thursday 13 February 2014

ቃሉ “የማይሰራ አይብላ” አይልም!!! (የመጨረሻ ክፍል)


Please read in PDF - kalu yemaysera aybila ayilm

     “ኢየሩሳሌም ትምህርት ቤት እንደገባሁ ሰሞን ከተማሪዎች ጋር የደረቀ ፍግ በአካፋ እየዛቅን በሚገፋ ጋሪ ወደየአትክልቱ እንድናፈስ ታዘዝን፡፡ተማሪዎቹ የለመዱት ሥራ ስለነበር እየተዝናኑ እየተጫወቱ ይሰራሉ፡፡የክፍል አለቃዬ መጣና 'ጎባው አትሰራም እንዴ?' ቢለኝ 'እኔ ፍግ ለመዛቅ አልመጣሁም ለመማር እንጂ!' ብዬ መለስሁለት፡፡የክፍል አለቃዬ ይህንኑ ሄዶ ለዋናው አስተዳደር ነገራቸው፡፡እሳቸውም 'ተውት ግድ የለም እሱ ሥራ መስራት ካልለመደ ሀገር ስለሆነ እስኪለምድ ድረስ አትንኩት' ብለው ሲናገሩ ሰማሁ፡፡እኔም ጥቂት ደቂቃዎች ከቆየሁ በኋላ ቆጨኝና የሚገፋውን ጋሪና አካፋዬን ይዤ እንደጓደኞቼ እየተሻማሁ መስራት ጀመርሁ፡፡ከዚያ በኋላ ሥራ ህይወት መሆኑን ተማርሁና ኑሮዬን ማቅናት ቻልሁ፡፡”(ከንቲባ ገብሩ ደስታ በኢየሩሳሌም ለትምህርት ሄደው የገጠማቸውን ኮሎኔል ዳዊት ገብሩ እንደዘገቡት) ከንቲባ ገብሩ ደስታ የኢትዮጲያ ቅርስ፡፡(1985) አዲስ አበባ፣ቦሌ ማተሚያ ቤት፡፡ገጽ.22)
     በሀገራችን በተለይ የሥራ ባህልን በተመለከተ ያለው እውነት እጅግ በጣም አስፈሪና አስደንጋጭ ነው፡፡ከላይ በምሳሌነት የጠቀስነው የከንቲባ ገብሩ ደስታ ህይወት የጥቂቶች ሳይሆን የብዙዎች መገለጫ ነው፡፡ካለብን አስነዋሪ ስያሜዎች አንዱ “በዓለም ላይ ካሉት ፍጹም ድኃ ከሚባሉት ሀገሮች ውስጥ መመደባችን ሳይሆን ረሀብተኞች የሚለውን አለመፋቃችን ከማሳዘን አልፎ ዛሬም የሥራ ባህላችን ቁልቁል መንደርደሩን ሥናይ ማደግ ሆይ ወዴት ነህ? ሥልጣኔ ሆይ ወዴት ተሰወርክ? የሚለው መባዘን ገና የሚያቆም አይመስልም፡፡

Monday 10 February 2014

የነነዌ ንስሐ (ዮና.3÷5-9)


Please read in PDF :- yeNenewe nisiha

        የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ ለጾም አዋጅ ነገሩ፥ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ።ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ እርሱም ከዙፋኑ ተነሥቶ መጐናጸፊያውን አወለቀ ማቅም ለበሰ፥ በአመድም ላይ ተቀመጠ።አዋጅም አስነገረ፥ በነነዌም ውስጥ የንጉሡንና የመኳንንቱን ትእዛዝ አሳወጀ፥እንዲህም አለ፦ ሰዎችና እንስሶች ላሞችና በጎች አንዳችን አይቅመሱ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ፡፡ሰዎችና እንስሶችም በማቅ ይከደኑ፥ ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩኹ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይጸጸት እንደ ሆነ፥ ከጽኑ ቍጣውም ይመለስ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?”(ዮና.3÷5-9)፡፡
      እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ለእስራኤል ብቻ ሳይሆን የትድግና ሥራውን ለአህዛብም እንዲናገሩ ነቢያትን አዟል፡፡እግዚአብሔር በቤቱ ስላሉት ብቻ አይጨነቅም፡፡በሩቅ ያሉ እስኪሰሙ ድረስም ሳያቋርጥ በፉጨት ድምጽ ይጣራል፡፡በቀደመው ዘመን ኤልያስና ኤልሳዕ (1ነገ.17÷24፤2ነገ.8÷1-17)በኋላም እነአሞጽ ከይሁዳ ውጪ ለእስራኤልና ለአህዛብ የእግዚአብሔርን የትድግና ሥራ የተናገሩ ነቢያት ናቸው፡፡ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእስራኤል ውጪ ወዳሉ ከተሞችና ሀገሮች እየሄደ ያስተምር ነበር፡፡መድኃኒቱ ጌታ “እምነትሽ ታላቅ ነው፤እምነትህ ታላቅ ነው፡፡”(ማቴ.15÷28፤ሉቃ.7÷9) ያላቸው ሁለቱ ሰዎች የተገኙት ኪዳን ከተቀበሉትና መቅደስ ከነበራቸው ህዝቦች መካከል ሳይሆን ከአህዛብ ወገኖች እንደሆነ ቃሉ ይመሰክራል፡፡
      አገልግሎታችን የራቁትን መቅረብ ካልቻለና ከመቅደስ እስከአውደ ምህረት ብቻ ከሆነ የጌታ ፈቃዱ እንዲህ አይደለምና ዳግም ልናርመውና ልናስተካክለው ይገባናል፡፡ ብዙውን ጊዜ በቤቱ ብቻ ስላለን የምንመካ ጥቂት አይደለንም፡፡ጽሁፎች ፌስቡክ ላይ ሲለቀቁ የሚሰጡ አስተያየቶችን  አያለሁ፡፡ የሚደንቀው ነገር አስተያየቱን የሚሰጡት ጥላቻን የማያልፉ ፣ቅንነት የጎደላቸው ፣የሌላውን ሰው እምነትና አመለካከት የሚያጥላሉ “የስም ክርስቲያኖች” መሆናቸውን ሳይ ለሌላው የተወደደ አክብሮት ያላቸውን ክርስቲያኖች ያልሆኑ ወገኖቼን አከብራቸዋለሁ፡፡
     ጌታ እግዚአብሔር ጭከናና ዝርፊያ፣አመንዝራነትና ጥንቆላ፣በንግድ ማጭበርበር የምትበዘብዘዋን እንዲሁም በእርሱ ላይ በክፋት የማታሴረውን ታላቂቱን የአሶርን ከተማ ነነዌን (ናሆ.1÷11፤2÷12፤3÷1፡19፤3÷16) እንዲሁ ሊተዋት አልወደደም፡፡ነዋሪዎቿ አህዛብ ፤ሥራዋ ደግሞ እንደሰዶምና ገሞራ ክፉ መንገድና አመጽ ቢሆንም (ዮና.3÷8-10) እግዚአብሔር ግን ወደዚህች ከተማ ታላቁን ነቢይ ዮናስን ላከው፡፡

Friday 7 February 2014

በምዕ.1÷8 ታዘዙ በምዕ.8÷1 ፈጸመው!!!




ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደሰማያት ሲያርግ ለደቀመዛሙርቱ የሰጠው ትልቁ ተልዕኮ "በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ፡፡" የሚለው ነው፡፡ይህን የምስክርነት አገልግሎት በእርግጥ ያለመንፈስ ቅዱስ ምሪትና ጉልበት ለመፈጸም መቃተት የማይታሰብ ህልም ነው፡፡የመጀመርያይቱ ቤተ ክርስቲያን ለወንጌሉ አገልግሎት ትልቅ የጸሎት ዝግጅት ነበራት፡፡አገልጋይ ደቀ መዛሙርትን ለመላክ ብቻ የምትጸልይም አልነበረችም፤ከላከችም በኋላ የኋላ ደጀን ሆና በጸሎት የምትተጋም ነበረች፡፡
         መንፈስ ቅዱስ ከወረደ በኋላ የቤተ ክርስቲያን ትልቁ የአገልግሎት ሥፍራ ኢየሩሳሌምና ይሁዳ ብቻ አልነበሩም፡፡ቅዱስ ጴጥሮስ ገና በቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን መንፈስ ቅዱስ እንደወረደ በሰበከው አጭር ስብከት ሦስት ሺህ አማኞችን ለክርስቶስ ማረከ፡፡ስብከቱ የቃል ጋጋታ፣ማባበል፣ፍርሃትያልነበረበት የመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ጥበብ የነበረበት ነውና ገና ሲናገር ሰዎችን ለእውነት የሚገዛ ነበር፡፡አገልግሎታቸውን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚቆዩበት ዘመን ርዝማኔ እንጂ ፍሬንና አማኝን ከማፍራት አንጻር የማይመዝኑ ሰዎች በዚህ ታሪክ ራሳቸውን ቢያዩ መልካም ነው፡፡አገልግሎት ዕድሜ መቁጠር ሳይሆን ባለችን ጥቂትም ትሁን ረዥም ዕድሜ ያፈራነው ፍሬ የሚመዘንበት ነው፡፡ጴጥሮስ በጥቂት ደቂቃ ስብከት ሦስት ሺህ ሰው ከማረከ ዛሬ ሦስት ሺህ ስብከት ሰብከንም ሆነ ተሰብከን ያላፈራንና እልኸኛ የሆንን ጥቂት አይደለንም፡፡

Monday 3 February 2014

ዘምርለታለሁ ቤተ ክርስቲያኑ


ፊት ከመጨማደድ
ጠቁሮ ከመናደድ
       ከነውርና እድፈት
       በበዛ ምህረት
ካነጻኝ በደሙ
ሾሞ ካነገሰኝ በገናናው ስሙ