Sunday 27 June 2021

ሰዶማዊነትን፣ ፖፑ ሊፈቅዱ ይችላሉን?

 Please read in PDF

ፖፕ ፍራንሲስ ከቅርብ ጊዜ በፊት ስለ ሰዶማውያውን፣ “ማኅበራዊ መብቶች” መናገራቸውን አንዘነጋም። ዛሬ ደግሞ በጻፉት ደብዳቤአቸው፣ “ለእግዚአብሔር ሥራ ሰዶማውያን ጭምር ሊሾሙ እንደሚገባ” መግለጣቸውን ዋሽንግተን ፖስት ደብዳቤአቸውን ዋቢ አድርጎ ዘግቦአል።[1] በእርግጥ በክፋት ከተያዘው ዓለም፣ ቀኖቹ እየባሱ፣ የሚያስቱትም የሚስቱትም እየበዙ እንደሚሄዱ ቅዱስ ቃሉ በማስጠንቀቂያ ጭምር ነግሮናልና፣ ክፉውና ዓመጸኛው ዓለም በክፋቱና በዓመጻው እጅግ መባሱ አያስደንቅም!


Thursday 24 June 2021

ተላላ መጋቢ

 Please read in PDF

ብቻ ይዘምሩ ጉባኤ ያድምቁ

ጭብጨባ አይቀንሱ አሥራት አያስታጉሉ

ልብሳቸው አይደፍ ፊታቸው አይጠውልግ

Friday 18 June 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፱)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

ቅድስና ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ቊልፍ ቃላት መካከል አንዱ ቅድስና የሚለው ነው። በተቃራኒው ደግሞ፣ “የመድሎተ ጽድቅ ጸሐፊ”፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ትርጕም ከሰጣቸው ቃላት አንዱ ቅድስና ነው። ቅድስና የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው፣ “እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ የለምና፥ እንደ አምላካችንም ጻድቅ የለምና፤ ከአንተ በቀር ቅዱስ የለም።” (1ሳሙ. 2፥2)፤ “እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና፤ ሰውነታችሁን ቀድሱ፥ ቅዱሳንም ሁኑ፥ እኔ ቅዱስ ነኝና፤” (ዘሌ. 11፥44)፤“ ጌታ ሆይ፥ የማይፈራህና ስምህን የማያከብር ማን ነው? አንተ ብቻ ቅዱስ ነህና፥” (ራእ. 15፥3) ተብሎ እንደ ተጻፈ፣ እግዚአብሔር አምላክ ብቻ ቅዱስ ነው። በዕብራይስጥ (godesh), በግሪክ (hagiosune) ተብሎ የተጠራው ቅድስና ትርጉሙ፣ መለየት ወይም እግዚአብሔርን መምሰል የሚል ነው። ቃሉ በተለይ በዘሌዋውያን መጽሐፍ ላይ እጅግ ተደጋግሞ የተጠቀሰ ነው።

Friday 4 June 2021

ኹለቱ የእውነት ቃል አገልግሎት አገልጋዮች!

 Please read in PDF

በዚህ ወር “ያለ እውነት፣ የእውነት ቃል አገልግሎት!?” ከሚለው መጽሐፍ መታተም ጋር በተያያዘ፣ ኹለት የእቃአ(ከዚህ በኋላ፣ የእውነት ቃል አገልግሎት ለማለት የሚውል) አገልጋዮች ፊት ለፊት ተገናኝተውኝ አውርተውኝ ነበር። አንደኛው አገልጋይ መጽሐፍ ተርጓሚያቸው ሲኾን፣ ኹለተኛው ደግሞ ሰባኪያቸው ነበር። አንዱን በሰው መካከለኝነት[በወንድም ቴዎድሮስ ደመላሽ አማካይነት] ያገኘኹት ሲኾን፣ ሌላው ግን ያገኘኝ ራሱ ደውሎ ለብቻ ነበር። ኹለቱም በአካል አጊኝተው ሊያወሩኝ በመፈለጋቸው፣ እጅጉን ደስ ብሎኛል።

Thursday 3 June 2021

አዲስ ነገር (ሉቃ. 5፥27-32)

ሙሉ ስብከቱን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው ያድምጡ! በቅዱስ ቃሉ ይባረኩ፤ ለሌሎችም ያካፍሉ፣ የመንግሥቱ ወንጌል ይሰፋ ዘንድ ላልተወደዱ ለሚመስላቸው ኀጢአተኞችና ዓለም ላገለለቻቸው ጋብዙ! የጌታችን ኢየሱስ መንግሥት ከመንፈስ ቅዱስ ኀይል የተነሣ ትሰፋለች፤ አሜን!