Sunday 25 December 2016

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ“አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አንድ)

   Please read in PDF
     የዚህ ጽሁፍ ዋና ጭብጥ፥
1.      ዋናችን ጌታ ኢየሱስን በክርስትና ሕይወታችን ሁሉ ትኩር ብለን እንድንመለከት፤
2.     ዋናችን የሆነውን ጌታ ኢየሱስን ትተን በእርሱ “ሎሌዎች” ላይ ዓይናችንን የተከልን፥ በንስሐ እይታችንን እንድናጠራ፥ ከሰባኪ አድናቂነትና ተከታይነት ወደጸጋ አደላዳዩና ሠጪው ጌታ እንድናተኩር፤
3.     አገልጋዮች የሆንንም፥ “የሚከተሉንን” ምዕመናንና ምዕመናት የተሰጠንን “ስጦታ” ሳይሆን፥ ሰጪውንና ሁሉን አድራጊውን እንዲመለከቱ፥ በሁላችንም ላይ የሚፈርደውንና የሁላችንን ሥራ ለሚያየው ጌታ ሕይወታቸውንና መንገዳቸውን አሳልፈው በማስጨከን እንዲሰጡ በማሰብ የተዘጋጀ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምልከታ ነው፡፡
መንደርደርያ
    ለብዙ ዘመናት ሰይጣን ሰዎች ዋናውን ጌታ እንዳይመለከቱና “ሥጦታውን መመልከት ሠጪውን የመመልከት ያህል ነው” ወደሚል ከንቱ ማታለል ብዙዎችን ሲመራ አይተናል፡፡ በተለይም በዘመናችን ይህ እውነታ ጎልቶና ደምቆ በመካከላችን በሚገባ ይስተዋላል፡፡ ሰዎች ሰባኪ[ሎሌውን] ብቻ መስማትን ልክ እግዚአብሔርን እንደመስማት ሲቆጥሩት፥ ቅዱሱን ወንጌል ከመመርመርና ጌታ ኢየሱስን በትክክል በመመልከት የክርስትና ሕይወት ሩጫቸውን ከመሮጥ ተዘናግተዋል፤ [ይህ በወንጌሉ ፍጹም እውነትነት ላይ የቆሙትንና ለቃሉ ፍጹም በመታመን በማገልገል ያሉትን የጌታ ታማኝና እውነተኛ አገልጋዮችን አይመለከትም]፡፡

Tuesday 20 December 2016

ከመናገር ለሚያልፈው ለሶርያ ልጆች እባካችሁ አልቅሱ!

    ከመናገር ለሚያልፈውና ደም መፍሰሱ ቅጥ ላጣው ለሶርያ ልጆችና ለምድሯ ሁሉ ሰቆቃ እባካችሁ አልቅሱ፣ እዘኑ፣ ራሩ፣ ጹሙና ጸልዩ! 

Friday 16 December 2016

የወዳጅ ሕመም

ደድሯል አካሌ፣ አመርቅዞ ውስጤ ፤
ነፍሴ ተኮራምታ፣ ተራቁታብኝ አቅሌ፤
ያጎረስሁት ያው እጅ፣ ይሸረክተኛል፤

Monday 12 December 2016

ጸሎትና ጾም ለኢትዮጲያ(የመጨረሻ ክፍል)


2.     “እግዚአብሔር ለዚህ ሕዝብ እንዲህ ይላል፦ መቅበዝበዝን ወድደዋል እግራቸውንም አልከለከሉም፤ ስለዚህ እግዚአብሔር በእነርሱ ደስ አይለውም፥ በደላቸውንም አሁን ያስባል ኃጢአታቸውንም ይቀጣል፡፡ እግዚአብሔርም፦ ለዚህ ሕዝብ ስለ መልካም አትጸልይላቸው፡፡ በጾሙ ጊዜ ጸሎታቸውን አልሰማም፤ የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የእህሉን ቍርባን ባቀረቡ ጊዜ አልቀበላቸውም፤ በሰይፍና በራብ በቸነፈርም አጠፋቸዋለሁ አለኝ፤” (ኤር.14፥10-12)
     በኤርምያስ ዘመን የነበሩት ሕዝቦች ወደእግዚአብሔር በፍጹም ንስሐ ከመመለስ ይልቅ በክፋታቸው በመጨከናቸው ምክንት ሊመጣ ያለውን ቅጣት ነቢዩ ይናገራል፡፡ በልባቸው ወደጣዖት አምልኮ አዘንብለውና በእግራቸው ወደዚ እየቸኮሉ ነገር ግን ጾምን ቢጾሙ፣ መሥዋዕትን ቢያቀርቡ እግዚአብሔር በዚህ ፈጽሞ አይረካም፡፡ ኤርምያስ እንዲህ ላለ ሕዝብ ፈጽሞ እንዳይማልድ በተደጋጋሚ ተክልክሏል፤ በክፋቱ የጸና ሕዝብ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይተዋል እንጂ ምንም አይነት እርዳታ አይደረግለትም፡፡

Thursday 8 December 2016

ጸሎትና ጾም ለኢትዮጲያ



  ታላቁ ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን ስለረሃብ እንዲህ “ተቀኝቶ” ነበር፥

Monday 5 December 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና - (የመጨረሻ ክፍል)

2. ሕበረ - ሰበ መስቀሉን ማብዛት፤
    ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀሉ ሞት መልካሙን ያደርጉ ዘንድ አዲስ ማሕበረሰብን ፈጥሯል፡፡ ይህን ማሕበረሰብ ያዋቀረው ደግሞ “… ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር አስታርቆ ነው (ኤፌ.2፥10 ፤ 16)፡፡ “ሁለታቸው” የተባሉት “በሥጋ አሕዛብ የነበሩት፥ በሥጋ በእጅ የተገረዙ በተባሉት ያልተገረዙ የተባሉትና” (ኤፌ.2፥11)፤ ቤተ እስራኤል ናቸው፡፡ ከእነዚህ ከሁለቱም አንዳች የዘርና ቀለም፤ የቋንቋና የነገድ ልዩነት ሳይኖር ነው፡፡
“ … አይሁድ ብንሆን የግሪክ ሰዎችም ብንሆን ባሪያዎችም ብንሆን ጨዋዎችም ብንሆን እኛ ሁላችን በአንድ መንፈስ አንድ አካል እንድንሆን ተጠምቀናልና። ሁላችንም አንዱን መንፈስ ጠጥተናል”
(1ቆሮ.12፥13)
እንደተባለ ክርስቶስ ኢየሱስ ልዩነትን ሽሮልናል ብቻ ሳይሆን ፍጹም አንድነትን እንኖርበት ዘንድ ሰጥቶናል፡፡