Monday 26 May 2014

የትንሣኤው ምስክሮች

    የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መካከል ሙስና መቃብርን አጥፍቶ መነሣት የክርስትና መሠረት የቆመበት ጽኑ ዐለት ነው፡፡ አሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ደም በጸጋ ድነናል፤ ወደፊት ደግሞ ፍጹም እንድናለን፤ (ኤፌ.2፥8) ብለን ደፍረንና ጨክነን ጮኸን የምንናገረውና ቤተ ክርስቲያንም አሰምታ የምትሰብከው እርሱ ዝጉን መቃብር ሳይከፍት፤ የታተመው ድንጋይ ሕትመቱ ሳይፈታ፤ ሞትን ድል አድርጎ ከሙታን መካከል ስለተነሣ ነው፡፡
     የጌታ ትንሣኤ የስብከቶች ሁሉ ዋናውና የመጀመርያው፤ ትልቁም ርዕስ ነው፡፡ አንድ ሰባኪ የእግዚአብሔርን ቃል ሊናገር በወጣበት አውደ ምሕረት ላይ “ብዙ ቃል” ሰብኮ የጌታን ትንሳኤ ሳይናገር ቢወርድ፤ በእውነት! እውነተኛ ሰባኪ መሆኑ ያጠራጥራል፡፡ ምንም እንኳ ጥቂት እንከኖች ቢኖርባትም ያቺ በተራራ ላይ የተሠራችውና ታበራ የነበረችው የሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን በአስቆሮቱ ይሁዳ ፈንታ ሌላ ሐዋርያ ሊመርጡ ባሉ ጊዜ ያስቀመጡት የመጀመርያው መስፈርት “ … ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር የትንሣኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል”(ሐዋ.1፥22) የሚል ነው፡፡
    ደቀ መዛሙርቱ ያልተደራደሩበት እውነት “ከእኛ ጋር የትንሣኤው ምስክር” የሚሆን ብቻ እርሱ እውነተኛ የጌታ ሐዋርያ ነው ብለው ማመናቸው ነው፡፡ ጌታ ከሙታን መካከል መነሣቱን የሚያምኑና የሚያውቁ ብዙ ሰዎች በዚያን ጊዜ ነበሩ፡፡ ይሁን እንጂ በዚህ ጊዜ የተፈለገው፤ ጌታ “እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ ”(ሮሜ.1፥4) መሆኑን ሳይፈራ ሳያፍር በአደባባይ የሚመሰክር ሐዋርያ ነው፡፡

Wednesday 21 May 2014

“Innoo ka’eera,asi hinjiru.” (Mat.16:6)

Please read in PDF

Goftaan IYesus Kirstos irra-daddarbaa fi cubbuu ilmaan namaa baadhachuudhaan fannoo irratti fannifameera. kanas barreesitootni wangeelaa sagalee tokkon mirkaneesaniru. (Mat.27:35,Mar.15:25,Luq.23:33,Yoh.19:18).duu’a fi dhiignii Goftaa IYesuus biyya lafa tanaafi ilmaan namaa hundaaf baayyee barbaachisaa dha. Sababn isaas dhiiga osoo hindhangalaasin dhiifamuun cubbuu waan hinjirref.(Ibr.9:22)
     Ilmaan namaa bittaa cubbuufi waanjoo seexanaa jalaa gaarummaa fi hojii isaaniitiin bilisa ba’u hindandeenye. qajeelummaatti fi hojiin gaariin keenya sababii cubbuu irra kan ka’een akka huccuu abaarsaatti ta’e (Isa.64:6) nuti  hundinuu karaa Waaqayyoorraa gorree ture. (Rom.3:12) kanaaf cubbuu nama tokko irraa kan ka’een gara biyya lafaa hundatti duuti dhufee. akkasumaas namootni waan yakkaniif du’i sanyii namaa hundaa walga’era.(Rom.5:12)
   Biyyii lafaa hundii abdii dhabee, du’a fi dukkanaan marfamee, seexanni bittaasaa yeroo babbal’ifatee jirutti, namni aarsaa hoolaa fi jibbichaa dhiyeesuus  gatii lubbuusaa wajjin waan walhinmadaaleef … baraarsa cubbuu fi nageenya sammuu waan argachuu hindandeenyeef Waaqayyoon ilmowwasaa hunda akkanumatti  waan nu jaalateef nu kenneera.(Yoh.3:16)

Monday 19 May 2014

አንደኛው መስቀል

Please Read in PDF
በህይወት የማይስማሙ በሞት ይጣመራሉ፡፡በክርስቶስ የሚካካዱ ለሰይጣን ሊገዙ በአንድ ያብራሉ፡፡በምድረ በዳ ሰው ለመግደል ፣የሰው ንብረት ለመዝረፍ የሚስማሙ ቀራንዮ ላይ መለያየት ይጀምራሉ፡፡በወንበዴነት ሚስማሙ የክርስቶስ በመባል ግን ይለያያሉ፡፡በኃጢአት የሚጣበቁ በጽድቅ ይነጣጠላሉ፡፡አይለያዩም የተባሉ የኃጢአት ባልንጀሮች ክርስቶስን በማመንና ባለማመን  እስከማይተዋወቁ ድረስ ይከፋፋሉ፡፡
       ቀራንዮ ድካማችን አይጸድቅባትም፡፡ድካማችንን በመስቀሉ ጠርቀን፤ ክፉ ምኞት አንቂ አሮጌውን ሰው ሰቅለን አዲሱን ሰው የምንለብስባት፤ ለአንዱ ጌታ መገዛታችንን በግልጥ ውሳኔያችንን የምንገልጥባት ስፍራ ናት፡፡ቀራንዮ ላይ ብዙ አማራጮች ብዙ መንገዶች የሉም፡፡ብዙ የመዳን ቀመሮች ፣ከሁለት የዘለሉ የድህነት ስሌቶችም የሉም፡፡ቀራንዮ ላይ ሁለት መንገዶች ብቻ አሉ፡፡አንዱ የሲዖል አንዱ ወደእግዚአብሔር ገነት፡፡ሦስተኛ ምርጫ የለም፡፡ብንፈልግም ፈጽሞ ማግኘት አይሆንልንም፡፡
        አንደኛው መስቀል ላይ ዘመኑን በውንብድና የጨረሰ፣ለክፋቱ ዳርቻ ሳያበጅ ከነክፋቱ የተገኘ ለጥፋቱም ተካካይ ፍርድ በህጉ የተሰጠው አንድ ደካማ ሰው አለ፡፡አለም ሞት ብትፈርድበትም ክርስቶስ ግን ዛሬም የርህራሔ እጁን ዘርግቶ እስከማታ "ልጄ ሆይ አትሙትብኝ እኔ ልሙትልህ!!!" እያለ ይለምነዋል፡፡ ከእግዚአብሔር መዝገብ ፍርድ እስካልወጣ አለም ሞት ፈርዳ ለፍርዱ መፈጸም ብትቻኮልም የህይወት ጥላችንን ማንም አያጥፈውም፡፡አለም ሞት ብትደግስም ክርስቶስ ግን የማይደክም የማዳን እጅ ዘርግቶለታል፡፡

Sunday 11 May 2014

ደቀ መዛሙርት የጌታን ትንሳኤ ለምን ተጠራጠሩ?(የመጨረሻ ክፍል)


3.    መጠራጠር ፦ ደቀ መዛሙርቱ ነገረ ትንሳኤውን ሲሰሙ የተነገራቸው “ … ቃል ቅዠት መስሎ ታያቸውና አላመኑም፡፡”(ሉቃ.24፥11) ደቀ መዛሙርት አርብ ዕለት በክርስቶስ ኢየሱስ የሆነውን መከራ አይተነዋል፡፡ስለዚህ ሁሉም “ተሰብስበው … አይሁድን ስለፈሩ ደጅ ዘግተው … ” በፍርሐት ቆፈን ውስጥ ሆነው ተቀምጠዋል፡፡ (ዮሐ.20፥19) እግዚአብሔርን የማይፈራ ፍርሃት ጥበብ የጎደለው ፍርሃት ነው፡፡እግዚአብሔርን እስከመካድ ያደርሳልና፡፡
   ጴጥሮስ “አንተ ክርስቶስ የህያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ”(ማቴ.16፥16) ብሎ የመሰከረለትን ጌታ ከሥጋዊ ፍርሃት የተነሳ በአንዲት “ነጻነት በሌላት”ሴት ፊት በተጠየቀ ጊዜ “የምትይውን … ሰውየውን አላውቀውም” ብሎ ካደ፡፡(ማቴ.26፥70፤72) “መለኮታችን” መለኮትን ፤ፍርሃታችን እግዚአብሔርን መፍራት ካልቻለ ፍርሃታችን የራሱን መለኮት ፈጥሮ መካዳችን የማይቀር ነው፡፡ጌዴዎን የመፍራቱና የመጠራጠሩ ምንጭ የምድያማውያን ጥቃትና እግዚአብሔርም እንደተዋቸውና እንደጣላቸው ማሰቡ ነበር፡፡(መሳ.6፥11-13) 
     አይሁድ ሁሉንም ሰው በክርስቶስ ሞት እንዲተባበር ኢየሱስን ግን እንዲያጠፉት ወይም እንዲገድሉት ህዝቡን እጅግ አባብለዋል፡፡ስለዚህም ሁሉም ይሰቀል እያሉ ጩኸት አብዝተዋል፡፡(ማቴ.27፥20፤23) ይህም በራሱ ለደቀ መዛሙርቱ ከባድ የፍርሃትና የጥርጥር ምንጭ ነው፡፡ አለሙ የተስማማበት ብዙዎች የተከተሉት ውሸት በእርግጥ ለዘመናት ብዙዎችን በጥርጣሬ መንፈስ ወደኋላ ስቧል፡፡ ዛሬም ወንጌልን በድፍረት እንዳንመሰክር የሚያደርገንና የፍርሃታችን አንዱ ዋናው ምንጭ ስህተት የሆነውን ነገር የተቀበለው ህዝብና ወገን በፍጥራዊው አይናችን ፊት በዝቶ ስለታየንና ትልቁን የጌታ ክንድ መዘንጋታችን ወይም መጠራጠራችን ነው፡፡ በመጠራጠር ወደኋላ መመለስ ደግሞ ውጤቱ ካለማመን ይበልጥ ሊከፋ ይችላል፡፡ስለዚህም “እግዚአብሔር የኃይልና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሃት መንፈስ አልሰጠንምና”(2ጢሞ.1፥7) በመንፈስ አካለ መጠን ልንጎለምስ ይገባል፡፡

Tuesday 6 May 2014

ደቀ መዛሙርት የጌታን ትንሳኤ ለምን ተጠራጠሩ? (ክፍል - 2)

     ደቀ መዛሙርቱ የተወራውን ወሬ በማመናቸው ሲጠራጠሩ ታይተዋል፡፡የመግደሎሟ ሴት “ጌታዬን ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አላውቅም … አንተ ወስደኸው እንደሆንህ ወዴት እንዳኖርከው ንገረኝ”(ዮሐ.20፥13-16) ማለቷ መሰረቁንና መወሰዱን ያመነች ይመስላል፡፡ጌታ ስለዚህ አለማመኗ “አትንኪኝ” በማለት ወቅሷታል፡፡ማርያም መግደላዊት ቀድሞ የት እንዳኖሩት ወይም እንደቀበሩት ቆማ ተመልክታ ነበር ግና ከመነሳቱ መሰረቁን ተቀበለች፡፡(ማር.15፥47)፡፡የጠላት ወሬ ምን ያህል ልብ እንደሚለውጥ አስቡ! ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ እነሳለሁ ያላቸውን ጌታ ረስተው፤ ቃሉን ዘንግተው ግን የተወራውን አብልጠው ተቀበሉ፡፡ደቀ መዛሙርቱ ከወንጌሉ ይልቅ ለጊዜውም ቢሆን የጠላትን ወሬ ማመናቸው እጅግ ይደንቃል!
   በእርግጥም የዛሬ ዘመን እልፍ አገልጋዮችና አማኞች የሚፈሩት ነገር ከሌላ ወገን የሚወራን ወሬ ነው፡፡ከሁሉ ይልቅ በተለይ ብዙዎች አገልጋይና አማኞች በኢየሱስና በስሙ መታማት አንፈልግም፡፡ምክንያቱም ስሙን ከደጋገምን አንድ ከባድ የሚለጠፍብን ታርጋ አለ፡፡“ጴንጤ ፣ተሐድሶ፣ጸረ ማርያም፣ጸረ ቅዱሳን፣መናፍቅ … ”የሚሉና ሌሎችም፡፡ ብዙ ጊዜ የክርስቶስ ስሙን ለሆዳቸው የሚቸረችሩ አገልጋይና አማኞችን በማየቴ ብዙም አልደነቅም፡፡ነገር ግን ለእውነት ሳንቆም በገና ለገና የሰው ወሬ የምንፈራ ከሆንን እውነተኛ ምስክር መሆናችን አይገለጥም፡፡
   ወሬው በጊዜው ቀላል አይደለም፡፡ማቴዎስ ወንጌሉን ይጽፍ በነበረበት ዘመን እንኳ ተሰርቋል የሚለው ወሬ በአይሁድ ዘንድ በጣም ይወራ ነበር፡፡(ማቴ.28፥15) አዎ! ታርጋ ከተለጠፈብን በኋላ ስለምንናገረው እውነት ሰሚ ማግኘት በጣም ከባድ ነው፡፡ለልባችን ቅርብ የነበሩቱ እንኳ በወሬው ብቻ በጠላትነት ጎራ ሊሰለፉብን ፣የማያውቁን አይናቸውን ጨፍነውና በጨው አጥበው ስማችንን ጥላሸት ሲቀቡት ተለምዶ፣ተዋህዶ፣ሥርዓት ሆኖ ይኸው እያየን ነውና በእርግጥም ያማል፡፡
     በተለይ መገናኛ ብዙሃን ለእውነት ሳይቆሙና ሳይቀኑ በእንቶፈንቶ ቋታቸውን ሲሞሉ ለሀገርና ለወገን የሚረባውን ትተው ተራ ወሬና ያልተባለን እየቀጣጠሉ ሲያወሩና እንደመቃኞ በሬ ሰዎችን ሲነዱ ማየት የበለጠ ልብ ይሰብራል፡፡ ብናስተውል ፖለቲካችን ያልተፈወሰው፣ስብከታችን የጠነዛው፣ክህነታችን የገረጀፈው፣ድቁናችን የነቀዘው፣ ቅስናችን የተናቀው፣ጵጵስናችን የተነቀፈው፣ ንግግራችን የተጠላው … ወሬን ማለፍ ስላልቻለና ከተግባራችን ጋር ፍጹም ዝምድና ስለሌለው ነው፡፡