Friday 24 June 2022

“ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” (መዝ. 68፥31)

 Please read in PDF

ኢትዮጵያ ቅድስት አገር እንደ ኾነች ለማሳመን፣ ከሚጠቀሱት ጥቅሶች መካከል አንዱ ይህ ጥቅስ ነው። ብዙዎችም በዚህ ጥቅስ በጣም ደስ ይላቸዋል፤ እንዲያውም አንዳንዶች ይህን ጥቅስ በመጥቀስ፣ “ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋ ነበር” ብለው ሲሞግቱ እንሰማቸዋለን። ነገር ግን ጥቅሱ እውን ሰዎች የሚሉትን ይናገራል ወይ? ክፍሉን ብንመረምር ተቃራኒውን ኾኖ እናገኘዋለን።

መግቢያ

Saturday 18 June 2022

“... ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤ ” (ዳን. 10፥13)

Please read in PDF

ይህን ቃል የተናገረው ነቢዩ ዳንኤል አይደለም፤ ከመላእክት መካከል ዕርዳታ ይፈልግ ከነበረ መልአክ መካከል አንዱ ወይም መልአኩ ገብርኤል ነው። የተናገረው ደግሞ ለነቢዩ ዳንኤል ነው። እንዴት?

ነቢዩ ዳንኤል በምዕ. 10፥1 በተመለከተው ታላቅ የጦርነት ራእይ እጅግ አዝኖ አለቀሰ። እናም እንደ አንድ ታላቅ መንፈሳዊ አገልጋይ፣ ያየውን ነገር በእግዚአብሔር ፊት ለማቅረብ፣ ባየው ራእይ ላይ የእግዚአብሔር ፈቃድ ምን እንደ ኾነ ለማወቅ፣ ራሱን ከምግብና ከመጠጥ በመከልከል ሦስት ሳምንታት እስኪፈጸሙ ጾምን ጾመ።

Wednesday 15 June 2022

መዳንም በሌላ በማንም የለም!

 Please read in PDF

·        ዛሬ በኢየሱስ ስም መስበክ ወይም ኢየሱስ ያድናል ማለት መናፍቅ አሰኝቶ ያስወግዛል!

·        ገድለ ተክለ ሃይማኖት ደግሞ፣ የተክለ ሃይማኖትን ስም የጠራ ይድናል ይላል!

 “መዳንም በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የተሰጠን ከሰማይ በታች ሌላ የለም” (የሐ.ሥ 12፥4)

ይህን ቃል የተናገረው ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ነው። የተናገረውም በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ በቅዱስ ድፍረት ውስጥ ኾኖ ነው። ይህን ቃል ለመናገር ያበቃው ደግሞ፣ ሲወለድ ጀምሮ ሽባ የነበረውን ሰው ከፈወሰ በኋላ ለተነሣው ሙግት ምላሽ ነው። ሰውዬው ለመሥራት ለመሮጥ፣ ለመቅደም፣ ለመታገል የማይችል ምስኪን ሰው ሆኖ፣ በወላጆቹ ላይ ወድቆ የሚኖር ሰው ነበር። ጥዋትና ማታ በቤተ መቅደስ በር ላይ እያመጡ ይጥሉታል፣ ከሕዝብ ምጽዋት እየለመነ የዕለት እንጀራውን ያገኛል። ከዚህ ሕይወት የሚያወጣው ሌላ እድል አያገኝም፣ ተስፋው በሙሉ በሰው ስጦታ ላይ የተመሠረተ ነው። አንድ ቀን በትክክል ቆሜ እራመዳለሁ ብሎ አስቦ አያውቅም፣ የሚያስበው በቀን ምን ያህል ምጽዋት እንደሚያገኝና ኑሮውን እንደሚገፋ ብቻ ነው። በዚህ ሁኔታ ከ40 ዓመት በላይ አሳልፎአል።

Sunday 12 June 2022

መንፈስ ቅዱስና አማኙ

 Please read in PDF

  ከግሪኩ “ፓራክሊቶስ” ወይም ከዕብራይስጡ “ፕራቅሊጥ” ከሚለው ግስ የተገኘው፣ “ጰራቅሊጦስ” የሚለው ቃል ትርጉሙ፦ “አማላጅ፣ አስታራቂ፣ አፍ፣ ጠበቃ፣ ትርጁማን፣ አምጃር፣ እያጣፈጠ የሚናገር፣ ስብቅል ካፉ ማር ጠብ የሚል።…፤ ናዛዚ፣ መጽንዒ፣ መስተፈስሒ፤ መንፈስ ቅዱስ” በማለት አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ተርጉመውታል።[1]

Wednesday 8 June 2022

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፲፮)

 Please read in PDF

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን፣ የራሱ የእግዚአብሔር ሥልጣን ነው!

“የመጽሐፉ ባለቤት ጌታ ራሱ ካልረዳ በስተቀር የቅዱሳት መጻሕፍትን ትርጓሜና ምስክርነት ለመረዳት አይቻልም። መጻሕፍቱ ምንም በሰው እጅ የተጻፉ ቢኾኑ በጌታ ትእዛዝ እንደ ተጻፉ እናምናለን።”[1] 

መግቢያ

ክርስትናም ኾነ የብሉይ ኪዳን እምነት የተመሠረተው፣ በመጽሐፍ ቅዱስ እውነትና ሥልጣን ላይ ነው። እግዚአብሔር ለወደቀው ዓለም፣ ተስፋ መስጠቱን ያረጋገጠበት እውነተኛ ሰነድ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። የኦሪት መጻሕፍት የመሰጠታቸው ዓላማ፣ በምድረ በዳ ለነበረችው እስራኤል የተሰጠ አስደናቂ የተስፋና የእምነት መጽሐፍ ነው። የእግዚአብሔር ኹሉን ቻይነትና ታዳጊነት እንዲደገፉበት የተጻፈ መጽሐፍ ነው። ቅዱሱ ፍጥረት፣ ውድቀቱ፣ ተስፋውና ደገፌታው ጭምር በውስጡ መጠቀሱም በዋናነት ይኸንኑ ሊያመለከት አለ።

Thursday 2 June 2022

ዕርገት - ወደ ሄደው ጌታ እንሄዳለን!

 Please read in PDF

የክርስቶስ ኢየሱስ ስቅለትና ሞቱ፣ የኀጢአታችን ዕዳ ፍጹም መከፈሉንና ቤዛችን እኛን ወክሎ መከራ መቀበሉን ያበሥራል፤ ትንሣኤው ደግሞ የዕዳችን ክፍያ ፍጹም መጠናቀቁንና መረጋገጡን የሚያመለክት ታላቅ ደስታችን ነው። ሞቱ ያለ ትንሣኤው ከንቱ ነበረ፤ ትንሣኤው ግን ሞቱን ጽድቃችን አደረገው፤ ከትንሣኤው ኃይልና ሕይወት የተነሣም የጸደቅንና የተቀደስን መኾናችንን ቅዱሳት መጻሕፍት ይመሰክሩልናል፤ “እርሱ[ክርስቶስ] ስለ ኀጢአታችን እንዲሞት ዐልፎ ተሰጠ፤ እኛን ጻድቅ አድርጎ ለማቅረብም ከሞት ተነሣ” እንዲል፤ (ሮሜ 4፥25)።