Friday 30 March 2018

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል አንድ)

Please read in PDF
    
    ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለኃጢአተኛው ዓለም ራሱን አሳልፎ ሰጥቷል፤ ራሱን አሳልፎ  የሰጠበትና ተሰቅሎ ዓለምን የሚያድንበት፣ ሁሉን ወደራሱ የሚያቀርብበት ኹኔታም፣ “እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ፤” (ዮሐ.12፥32) ተብሎ ተገልጧል፡፡ እርሱ የወደቁትን በማንሣት ወደር የለሽና የማይዝል የአብ ክንዱ ነው። ቢዋረድም፣ ዝቅ ዝቅ ቢል፣ በሰው ምስል ኾኖ እንደባርያ ቢያገለግልም ... እርሱ ለአብ አንድያ ልጁ፣ ከአምላክ የተገኘ አምላክ፣ ከብርሃን የተገኘ እውነተኛ ብርሃን ነው።
    “መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን የተነሣ” ነው፤ (1ቆሮ.15፥3-4)፡፡ ታላቁ መጽሐፍ ይህን እውነት የሚያስረዳን አጉልቶና አድምቆ ነው፤ የቤተ ክርስቲያንም ታላቅና ውድ ምስክር ነው፤ ምስክርነቷም የቃል ብቻ ሳይኾን በሚያስፈልግም ጊዜ በሕይወት ጭምር ዋጋ በመክፈል የምትመሰክረው የሕይወት ዘመን ምስክርነቷ ነው። ደግሞም ይህ የከበረ እውነት በብዙ ምስክሮች ያጌጠና ያሸበረቀ ነው።

Thursday 29 March 2018

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፲

Please read in PDF

  እግዚአብሔር ልጅነታችን እስከመለኮት መኾን የሚደርስ ነውን? በሚለው ርእስ ሥር፣ “አይደለም” በማለት ጥቂት ነገር መጨመርን ፈልጌያለሁ፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ስንል፣ ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለታችን ነው፡፡ እግዚአብሔር ከኾነ ደግሞ መጀመርያና መነሻ የሌለው፣ ያለ፣ የነበረና የሚመጣው ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ፣ ሕያውና ዘላለማዊ ነው ማለታችንም ጭምር ነው፤ (ራእ.1፥8)፡፡
     ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ ስለዚህ ጉዳይ ሲናገር፣ “ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።” (ዮሐ.1፥3) ይለናል፡፡ ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታችን እግዚአብሔርነትን ከጊዜ ብዛት ወይም በኾነ ጊዜ ያገኘው አይደለም ወይም እግዚአብሔርነትን ያገኘው በኾነ በታወቀ ጊዜ[ለምሳሌ፦ ከቅድስት ድንግል ሲወለድ ወይም በዮርዳኖስ ወንዝ ሲጠመቅ] አይደለም፤ ከዘላለም ጀምሮ እግዚአብሔር ነበረ፤ በዘላለም ውስጥም እርሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ “ቃል እግዚአብሔር ነበረ” ሲል፣ ከመጀመርያውም የነበረበትን መለኮታዊ፣ ፍጹም አምላካዊ ሁኔታን የሚያስረግጥ ነው፡፡

Wednesday 21 March 2018

ታማኝ ባርያ


Please read in PDF

ማኅሌታይ ያሬድ የዓቢይ ጾምን ኹሉንም ሳምንታት ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወትና ትምህርት እንዲኹም ማንነት ጋር በማዛመድ ስያሜ ሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም የተነሣ ይህ አሁን ያለንበት ሳምንት ስያሜ ገብር ሔር ይባላል፤ ትርጉሙም መልካም ባርያ ማለት ነው፡፡ የስሙ ትርጉም የተወሰደው ከማቴ.25፥23 ላይ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ በዚያ ክፍል በመልካምነትና በታማኝነት ስላገለገሉ አገልጋዮች ስለሚሰጠው ታላቅ ሽልማትና ክብር እንዲሁም ደግሞ፣ ላልታመኑት አገልጋዮች እንዴት ያለ ታላቅ ተግሳጽና ዘለፋ እንዲሁም ፍርድ እንደሚያገኛቸው ያስተማረበት ክፍል ነው፡፡
     የተሰጠን መክሊት በአግባቡ መጠቀም እጅግ አስተዋይነት ነው፡፡ መክሊቱ ልዩ ልዩ ሥጦታን የሚያመለክት ነው፤ ሥጦታዎቹ መንፈሳዊም ኾኑ ሥጋዊ ሥጦታዎች፣ የተፈጥሮ ወይም የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታዎች ሊኾኑ ይችላሉ፤ (1ቆሮ.12፥7-11፤ ገላ.5፥22) ራሱ መንፈስ ቅዱስም ለሚያምኑ ኹሉ የተሰጠ ውድና ክቡር ሥጦታ ነው፡፡ ስለዚህም የሁሉ ሥጦታዎቻችን ምንጭ ራሱ እግዚአብሔር አምላክ እንጂ እኛ አይደለንምና በሥጦታዎቻችን ልንመካ አይገባንም፡፡ ከመጀመርያም የሥጦታ የመሰጠት ምክንያቱ ለእኛ ሳይኾን ለቤተ ክርስቲያን ብቻ ነው፤ እኛማ ከፍጥረታችን እኛ የቁጣ ልጆች እንጂ ምንም መልካም ነገር ያልነበረንን ነን፤ (ኤፌ.2፥3)፡፡ ስለዚህ ታማኝነታችንን መግለጥ የሚገባን በተሰጠን መክሊት ልክ ነው፡፡

Wednesday 14 March 2018

እንዳትራራ ያኔ!

Please raed in PDF

ዛሬ ባንተ ጉልበት ጸጋህን ታምኜ
ከደምህ በኾነ ፍጹም ብቃት ድኜ
ስተጋ ለቃልህ ለወንጌልህ ሥራ

Tuesday 13 March 2018

“መጻጉዕ” ኢትዮጲያ ሆይ! እግዚአብሔር በምሕረት ይማርሽ!


Please read in PDF
   ኢትዮጲያ ታምማለች፤ ሕመሟም ጸንቶባታል፤ ክሳትዋ፣ ግርጣትዋ፣ መሞገጓ፣ መጥቆርዋ፣ መጠልሸቷ፣ ኩምሽሽ ኩምትር ማለቷ፣ አንዱ ሌላውን ሊበላላና ሊጠፋፋ ማሰፍሰፉ፣ ደም ማፍሰስ ወዳድነታችን ያመረቀዘበት፣ ሰው በሰውነቱ አልከበር ብሎ ብሔርና ቋንቋ መስፈርት አድራጊያን የበዙባት … ምድር ኾናለችና ምድሪቱ ታምማለች፤ አጐንብሳ ታቃስታለች፤ መሪዎቿ ሊያስታምሟት የወደዱ አይመስሉም፤ ከእጅግ በጣም ጥቂቶቹ በቀር ልባቸው ደንድኗል፤ ኅሊናቸው ታውሯል፤ ሽማግሌዎች ከመደመጥና ከመከበር ይልቅ መታፈሪያቸውና መከበሪያቸው “ያበቃለት” ይመስላል፤ ሁሉም ነገር “የራሳቸውን ሕይወት አውጥተው በማያስገቡና በማይደማመጡ” ወጣቶች እጅ ለመውደቅ እያዘመመ ይመስላል፤  … የኢትዮጲያ መጻጉዕነት መልኩና ፈርጁ እየበዛ እየሰፋ መምጣቱን ለመናገር ነቢይነት አያሻውም። እጅግ አሳዛኙ ነገር ግን ይህች “ቅድስትና ብዙ አማኞች እንዳላት የሚነገርላት አገር” በዚህ ሁሉ ነገሯ ለመንፈሳዊ ነገር መታወሯና ቅድሚያ ለመስጠት አለመወሰኗ እጅግ አስጨናቂና መራራ ኹኔታ ነው። እግዚአብሔር ስሙ እየተጠራባት እግዚአብሔር ባዕድ የኾነባት አገር!!!

    ለየትኛውም አማኝ ሚዛኑ፣ ማዕከሉ፣ የአንድ ነገር መለኪያ ቱንቢው ቃለ እግዚአብሔር ወይም መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ነገሮችን ከቃለ እግዚአብሔር አንጻር ሳይሆን፣ ከጊዜው ትኩሳት አንጻር ብቻ የምንዳኝ ከሆነ ፍጹም እንስታለን። ነገሮችና ኹኔታዎች የዘመኑን መልክ ሊይዙ ይችሉ ይኾናል፤ የእግዚአብሔር ቃልና ባሕርይ ግን የጸናና ለዘለዓለምም የማይናወጥ ነው። ስለዚህም ከጸናው ጋር እንጸናና እንቆም ዘንድ የቃሉ ስንቅ መመገብ የዘወትር ልማዳችን ሊኾን ይገባዋል ማለት ነው።

Thursday 8 March 2018

ስድስት ዓመታት በጡመራ መድረክ አገልግሎት

      “አስቀድሜ ስለ ሁሉም ነገር አምላኬን በኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለሁ።” (ሮሜ.1፥8) ላለፉት ስድስት ዓመታት በጡመራ መድረክ አገልግሎት መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ያደረጉ ትምህርቶች፣ ስብከቶች፣ ዕቀብተ እምነታዊ ምልከታዎች፣ ካነበብኳቸው፣ ግጥሞችና ሌሎችንም ጽሑፎችን ለአማኝ አንባብያንና ለሌሎችም ወገኖች አቅርበናል። በተለይም ዕቅብተ እምነታዊ ሥራዎችና ትምህርቶች በዚህ ዓመት በስፋት ከቀረቡት ውስጥ የሚካተቱ ናቸው።
   ምክንያቱ ደግሞ፣ ከፊት ዓመታት ይልቅ የስህተት አስተምኅሮ በግልጥ ታይቷል፤ እጅግ ቅርባችን የነበሩትንም ሰዎች መርዘዋል፤ ከተሰቀለውና ከተነሣው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አማንያንን ለይተዋል፤ አደላድለዋል፤  ምንም እንኳ የሐሰት መምህራኑንና ደቀ መዛሙርቶቻቸውን የማውራት ሥራ ቢሠራም፣ ከዚያ በኋላ ግን ይህንን በግልጥ ለመቃወም አንዳች በራሳችን አልተማከርንም፤ የእግዚአብሔር ቃል የሚጠየፈውን ኹሉ ሳንራራ ተጠይፈናል። ስለዚህም በዚህ ረገድ ሰፋ ያለ ዕቀብተ እምነታዊ ሥራ በሥፋት ለመሥራት ጥረት ተደርጓል።