Sunday 24 January 2021

የማርያም ምስልና የሚካኤል ክንፍ!

 Please read in PDF

መግቢያ

በብዙዎች ዘንድ ከምንከሰስበት ነገር አንዱ፣ “ስለ ማርያም አትሰብኩም፤ ስለ ቅዱሳንም አትመሰክሩም” የሚል ክስ ነው።  ይህን የሚሉ አካላት እያወቁም ይኹን በጽንፈኝነት ከመጽሐፍ ቅዱስ ተቃራኒ በመኾን ዘመናቸውን ስለ ማርያምና ስለ ቅዱሳን “በመስበክ” ይከስራሉ። ከዚህም የተነሣ አያሌዎች ማርያምን በመስበክ የታወቁ ናቸው። ከሰሞኑ እንኳ ካየነው የዘበነ ለማን ዓይን ያወጣ ግብዝነት ማንሳት እንችላለን። ይህን ሳሰላስል የመጣልኝ አንድ አስቂ ታሪክ አለ። መልአኩ ሚካኤል አንድ ክንፉ ያዘቀዘቀበት ምክንያትና የማርያም ከፍጥረተ ዓለሙ በፊት መታየት።

Monday 18 January 2021

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት

 Please read in PDF

መግቢያ

በመጽሐፍ ቅዱስ ዋና ዋና ከሚባሉት ትምህርቶችና አማኞች ሊጠመቁት ከሚገባው ጥምቀት አንዱ፣ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ነው። የብዙዎች ትኵረትና መሻት ያለው የውኃ ጥምቀትና በየዓመቱ ከጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ የሚከበረውን የከተራ በዓልን እንጂ ስለ መንፈስ ቅዱስ ጥምቀት እምብዛም ግንዛቤው ያላቸው አይመስልም። ነገር ግን አስገዳጅ ከኾኑ መንፈሳዊ እውነቶች አንዱ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ነው፤ በመንፈስ ቅዱስ ያልተጠመቀ እርሱ እውነተኛ አማኝ ወይም መንፈሳዊ አይደለም።

Thursday 14 January 2021

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፬)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

·        የእግዚአብሔር ቊጣ

መጽሐፍ ቅዱስ፣ ኀጢአት የእግዚአብሔርን ቊጣ እንደሚያነሣሣ በግልጥ ይናገራል፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ባሕርይውና ፈቃዱ ቅዱስና ጻድቅ ነውና፣ በኀጢአት ፈጽሞ አይደሰትም። በሌላ ንግግር ኀጢአትን ፈጽሞ ይጠየፋል፣ ይጠላልም፤ በኀጢአት ከቶም ደስ አይሰኝም ማለታችን ነው። አደራረጉ ፍጹም ቅዱስና ንጹሕ ነው። ስለዚህም “በቍጣውና በመዓቱ ኀጢአተኞችን ይገለባብጣቸዋል፤ ኪዳኑን የሚተዉትንም ይነቅላቸዋል፤ ” (ዘዳ. 29፥23-28)። ቅዱሱ እግዚአብሔር፣ ያለ ተጨባጭ ምክንያት እንደ ሰው በንዴትና በብስጭት የሚቈጣ አይደለም፤ ቊጣው ወዲያው የሚነሣ ደግሞም ቶሎ የሚበርድም አይደለም። በተለይ ኀጢአተኞችን ለኀጢአታቸው በመተው ቊጣው ይገለጣል፤ (ሮሜ 1፥24)።

Monday 11 January 2021

ብሔራዊ ውርደታችን!

Please read in PDF

ዛሬ ላይ በምንም ዓይነት ሚዛን፣ አጼ ኃይለ ሥላሴን እንዲያ መዋረዳቸውን፣ 60ዎቹ ሚኒስትሮቻቸው ደግሞ በአንድ ጉድጓድ ውስጥ በጅምላ ተገድለው መቀበራቸውን የሚደግፍ ሰብዓዊና ጤነኛ ሰው ይኖራል ብዬ አልገምትም።  ይህን የማይደግፈው አጼው አልበደሉም፤ ሚኒስትሮቻቸውም ንዑዳን፤ ቅዱሳን ናቸው ብሎ እንዳይደለ፤ ነገር ግን አገር ለመሩ፣ ጥቂት ውለታ ለዋሉ ምንም ያህል ክፉ ቢሠሩ ብድራታቸው ግድያ፤ በጅምላ መረሸን፣ መዋረድና መንገላታት እንዳልኾነ ዕዝነ ልቡናው ያስባል፤ ያሰላስላል ብዬ እንጂ።



Monday 4 January 2021