Friday 19 January 2024

“እያጠመቃችኋቸው፥ … እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤” (ማቴ. 28፥20)

 Please read in PDF

ለቤተ ክርስቲያን ከተሰጡ ሐዋርያዊ ተልእኮዎች ውስጥ፣ ቀዳሚውና የዘወትር ተግባር “አማኞችን ደቀ መዛሙርት ማድረግ” ነው። እንደ ጌታችን ትምህርት፣ አማኞች ደቀ መዛሙርት የሚኾኑት፣ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሲጠመቁ፣ ጌታ ያዘዘውን ኹሉ እንዲጠብቁ ሲማሩ፣ እንዲሁም በመታመን እርሱን ለመከተል ደቀ መዛሙርት በሕይወት ሲኾኑ ነው።

Thursday 18 January 2024

“ከእኛ ጋር ለምን አስተካከልሃቸው?” (ማቴ. 20፥11)

 Please read in PDF

ጌታችን ኢየሱስ መንግሥተ ሰማያት ምን እንደምትመስል በሰጠው ውብ ምሳሌ፣ እግዚአብሔርን የወይኑ እርሻ ባለቤት አድርጎ ያቀርበዋል። የእርሻው ባለቤት በአትክልቱ ስፍራ ሰውን ለመቅጠር ፈልጎ ጥሪ አቀረበ። በጥሪው መሠረት ሠራተኞቹ፣ አንድ ዲናር ሊከፈላቸው ተስማምተው ወደ እርሻው ቦታ መጡ። የሥራው ሰዓትም ከማለዳ 12 ሰዓት እስከ ምሽት 12 ሰዓት ነበር።

Wednesday 17 January 2024

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፯)

 Please read in PDF

ካለፈው ቀጠለ …

   5. የቅድስት ሥላሴ ትምህርት ምስጢር ነው!

ትምህርተ ሥላሴ ምስጢር ነው ስንል፣ ምን ማለታችን ነው? ብንል፣ ለሰው ያልተገለጠ ብዙ ትምህርት ወይም ብዙ ነገር አለ ማለታችን ነው። ኾኖም ግን በመጽሐፍ ቅዱስ ሦስቱን አካላት ለማጥናት ብዙ ትምህርት እንዳለ ልንዘነጋ አይገባም። በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ትምህርቶች ምስጢር ተብለዋል፤ ለምሳሌ፦ ጌታችን ኢየሱስ፣ ለደቀ መዛሙርቱ፣ “ለእናንተ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፥ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም።” ሲል (ማቴ. 13፥11)፣ ምሳሌዎቹ የተነገሩት በሕዝቡ ኹሉ ፊት ቢኾንም፣ ትርጕማቸው ወይም ምስጢሩ ግን የተነገረው ለደቀ መዛሙርት ብቻ ነው።



Thursday 11 January 2024

Sagantaa Addaa Ayyaana Yaadannoo Dhaloota Kiristoos!

" ... Ishiini ilma deetti; atis maqaa isaa Yesuus jettee moggaafta; inni saba isaa cubbuu isaanii irraa ni fayyisaatii." (Matt. 1:22)

 

Saturday 6 January 2024

ከባሪያዪቱ የተወለደ ንጉሥ!

 Please read in PDF

የክርስትና ትምህርት ከደመቀበትና ከተንቈጠቈጠበት ቀዳሚው እውነት አንዱ፣ የእግዚአብሔር ልጅ በእርሱ የሚያምኑትን ኹሉ በጸጋ የእግዚአብሔር ልጆች ያደርግ ዘንድ የሰው ልጅ መኾኑ ነው። እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ኾኖ፣ ዓለማትን የፈጠረና ደግፎም የያዘ ወይም ዓለሙ ተያይዞ የቆመው (ዮሐ. 1፥3፤ ቈላ. 1፥17፤ ዕብ. 1፥3) በእርሱ በታላቁ አምላክ ቢኾንም፣ በተለየ አካሉ  ከባሪያዪቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም (ማቴ. 1፥21፤ ዮሐ. 1፥14) ሥጋን ነሥቶ ተወለደ።

Monday 1 January 2024

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፳፯)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

ባለፈው “የመድሎተ ጽድቅ” ጸሐፊ፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ (Exegesis) ሳይኾን ወደ መጽሐፍ ቅዱስ (Eisegesis) እንደሚተረጕም አንድ ምሳሌ አንስተን ነበር። ዛሬ በድጋሚ ኹለተኛ ምሳሌ በማንሳት በዚህ ርዕስ ሥር ያለውን ዐሳብ እንቋጫለን።