Wednesday 26 February 2020

ቤተ ክርስቲያንንም ለ“መደመር”?፤ ተዉ!

Please read in PDF

   በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ነገሥታት “በዶግማና በቀኖና” አንድ ያልነበሩትን “አብያተ ክርስቲያናት”፣ አንድ ለማድረግ እጅግ መጣራቸውን እናስተውላለን።


   “ከኬልቄዶን ጉባኤ በኋላ ለሚቀጥሉት ፩፻፶ ዓመታትያህል የነገሡ የቊስጥንጥንያ ነገሥታት ቤተ ክርስቲያንን ለማዋሐድ ብዙ ጥረት አድርገዋል። ለምሳሌ ከ፬፻፸፬-፬፻፺፩ ዓ/ም የነገሠው ዘይኑን(ዚኖን)፣ ከ፬፻፺፩-፭፻፲፰ዓ/ም የነገሠው እናስታሲዮስ በተዋሕዶ አንድ ባሕርይ የሚለውን የተዋሕዶ እምነት ተቀብለው ቤተ ክርስቲያን በሰላም የምትመራበትን መንገድ ለመፈለግ ተነሳሰተው ነበር። ለዚህም በጎ ፈቃድ መሰናክሉ የኬልቄዶን ጉባኤ ውሳኔና የልዮን ጦማር መኾኑን በመገንዘብ የቊስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳስ አባ አጋግዮስ(አካኪዮስ) እና ንጉሡ ዘይኑን ተስማምተው ይህን ለመሰረዝና ቤተ ክርስቲያንንም ወደ ጥንታዊ የተዋሕዶ እምነቷ ለመመለስ ከአንጾኪያና ከእስክንድርያው ፓትርያርኮች ጋር ውይይት ጀመሩ።”[1]

Thursday 13 February 2020

በነነዌ ማግስት!

Please read in PDF

በነነዌ ምድር …
ኀጢአት ተከተተ፣ ነውር ተከደነ
ዓመጻ ታለለ፣ ምሕረት ገነነ

Thursday 6 February 2020

ንቀት (ክፍል ፲ እና የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF
እንኪያስ፦
1.      ትናናቁ፦በማንኛውም የኑሮ ዘይቤ የሚኖሩ ሰዎችን ስታከብሩ፣ ሠሪያቸውን ወይም የፈጠራቸውን ያህዌ ኤሎሂምን ነው የምታከብሩት። እግዚአብሔር ሰውን ወደዚህ ምድር ሲያመጣው በትልቅ ዓላማና ለክብሩ መገለጫ ይኾን ዘንድ ነው። እኛ እንደ ሳይንቲስቶች ወይም እንደዚህ ምድር ጠቢባን በፈጠረው ዓለምና ሰው እጅግ በመደነቅና በመመሰጥ የምንዋጥና በዚህ ብቻ የምንቀር አይደለንም፤ ይልቁንም እግዚአብሔር ዓለምንና ሰውን የፈጠረው ያህዌ ኤሎሂም ከሰው ጋር ግላዊና ኅብረታዊ ግንኙነትን ሊመሠርት እንዳለው እናምናለን።

Wednesday 5 February 2020

ንቀት (ክፍል ፱)

Please read in PDF

ኢየሱስ ክርስቶስ ዋናው አብነታችን!
ጌታችን ኢየሱስ ፍጹም ተንቆአል!
በአንድ ወቅት በክርስቶስ ኢየሱስ ጉዳይ በአይሁድ ሸንጐና ሕዝብ ክርክር መደረጉን፤ በመካከላቸው መለያየት በተደጋጋሚ መከሰቱንም የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ይነግረናል፤ (7፥43፤ 9፥16፤ 10፥19)።ለዚህ ምላሽ እንዲኾንም የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ለማስያዝ ያደረጓቸው ተግባራት ለኢየሱስ የነበራቸውን ንቀት ፍንትው አድርጐ ያሳያል። ዮሐንስ ይህን በሚገባ ይገልጠዋል፤ አስቀድሞ እነርሱ ከሚያከብሩአቸው ሰዎች ታላላቅ ሰዎችን በመላክ ለኢየሱስ ያላቸውን አክብሮት ቢያሳዩም፣ በኋላ ላይ ግልጹ ዐሳባቸው ታውቆአል፤ ይኸውም ለኢየሱስ ያላቸውን ንቀት ለማሳየት ጠባቂዎችንና ዝቅተኛ ሥልጣን ያላቸውን ሰዎች ልከዋል፤ ነገር ግን ከፊተኞቹ የኒቆዲሞስ ማመን ከኋለኞቹም ጠባቂዎች “እንደዚህ ሰው ማንም እንዲሁ ከቶ አልተናገረም” የሚል ምስክርነት መገኘቱ እጅግ የሚደንቅ ነው፤ (ዮሐ. 7፥45-52)።

Sunday 2 February 2020

ንቀት (ክፍል ፰)

Please read in PDF
1.    በአገራችን አስተዳደጋችን ምንታዌነት አለው
   በመጀመሪያቱ ቤተ ክርስቲያን ቤተሰቦች ውስጥ የነበሩት ባሪያዎች፣ አንዳንዶቹ በጌታ ኢየሱስ ያመኑ ነበሩ፤  ስለዚህም እኒህን ባሪያዎች እንደ ወንድሞቻቸው እንጂ እንደ ቤት አገልጋዮቻቸው እንኳ አይመለከቱአቸውም ነበር፤ ነገር ግን እኒህ ባሪያዎች በተቃራኒው ጌቶቻቸውን መናቅ ጀመሩ፤ የክርስትናው ነጻነት ይበልጥ ሊያከብሩአቸውና ሊሠሩላቸው እንዲገባ ማዘዙን ዘነጉት፣ እነርሱ ግን በተቃራኒው አደረጉ። አንድ አገልጋይ በግዴታ ያገለግል በነበረበት ወራት ይሠራ የነበረውን ሥራ ኹሉ፣ አኹን ግን በፍቅር መሥራት ተሳነው። ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ፦
የሚያምኑም ጌቶች ያሉአቸው፥ ወንድሞች ስለሆኑ አይናቁአቸው፥ ነገር ግን በመልካም ሥራቸው የሚጠቅሙ የሚያምኑና የተወደዱ ስለሆኑ፥ ከፊት ይልቅ ያገልግሉ።” (1ጢሞ. 6፥2)