Thursday 28 January 2016

“በኦርጋን ልንዘምር ይገባል ፤ አይገባም” ከሚለው ክርክር ጀርባ ...


       የቤተክርስቲያንን ታሪክ እንደምናጠናው ቤተክርስቲያን እጅግ ዘግናኝና አሰቃቂ የአላውያን ነገሥታትን ስደትና መከራ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ድል አድራጊነት የተወጣችውን ያህል፥ የተድላውን ዘመን ማለፍ ሲሳናት አስተውለናል፡፡ ለምሳሌ ያህል፦ የመካከለኛው ዘመን በሚባለው ከ590-1517 ዓ.ም [1] ከብዙው መካከል በዋናነት ሁለት አስነዋሪና ዘግናኝ ስህተቶችንእ ናስተውላለን፡፡

Monday 25 January 2016

“Qottoon hidda mukaa hundumaa irra kaa'amee jira;”(Maate.3፥10)




     Jecha kana kan dubbate Yohannis Cuuphaa dha. Kan dubbatees Fariisotaa fi Saduuqota laga Yordaanositti cuuphamuudhaaf gara isaatti dhufan erga argee booda dha. Yohannis cuuphaan “Mootumman waaqaa dhi’aateeraatii yaada garaa keessanii geedaradhaa!” jedhee jecha raajicha Isaayaas kaasuudhaan yeroo mootummaa Waaqayyoo labsuu; warri Yeerusalem jiraatan, warri Yihuuda, warri kutaa biyya naanna’aa Yoordanoositti jiraatan hundi gara isaatti dhuufuun cuuphamaYohannis cubbuu isaani himachaa ofii isaanii cuphsiisaa turan.
    CuuphaanYohannis jiruu fi umrii isaa guututti Waaqayyoof kan kennee waan ta’eef mootummaa waaqaa labsuu malee hojii biro hinqabu ture. Kanas kan labsaa ture soda tokko malee dha.Namootni isa bira dhufaa turan uummata hedduu, namoota qaraxa guuran, warri looltuuni fi… kaneen biros isa bira dhufanii “mee maal goodhu qabna?” yeroo jedhani gaafatan; hunda isaaniitiif waan isaan irraa eegamuu sirritti itti himaa ture. Yeroo ammaa kana keessatti rakkoon dhugaa mootummaa waaqaa ifatti fi sirritti barsiisuu(labsuu) dhabuu dha. Waldaaleen hedduun miseensoonni isaani cubbuu keessatti akka argamanitti himuu dhiisanii waljajanii qofa wajjiin jiraatu. Waaqayyoon garuu yaada namaa fi garaa namaa ni fonqolcha ykn sakkata’a.(Mula.2:23)

Monday 18 January 2016

መንፈስ ቅዱስ በጥምቀቱ በኢየሱስ ላይ ለምን ወረደ?


እንኳን ለጌታችን ጥምቀት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
    ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከመንፈስ ቅዱስ የተነሳ ያለወንድ ዘር ፤ ከሴት ዘር  ተወለደ፡፡ (ሉቃ.1፥31 ፤ 2፥6-7) እርሱ በኃጢአት ከወደቀውና በበደሉ ምክንያት ዘሩ ካደፈው አዳም ሳይሆን እኛን ከወንድ ዘር ያይደለ ፤ ከማይጠፋ ዘር ሊወልደን (ዮሐ.1፥13 ፤ 1ጴጥ.1፥23) በልዩና ፍጹም ቅዱስ በሆነ የመንፈስ ቅዱስ አሠራር ተወለደልን፡፡
    ጌታችን ከተወለደ በኋላ በአሥራ ሁለት አመቱ ወደኢየሩሳሌም ለበዓል ወጥቶ ከኢየሩሳሌም ሲመለስ፥ “ … ከእነርሱም ጋር ወርዶ ወደናዝሬት መጣ፥ ይታዘዝላቸውም ነበር።” (ሉቃ.2፥51) ከሚለው በቀር እስከሠላሳ አመቱ ምን ይሠራ እንደነበርና የት እንደቆየ መጽሐፍ ቅዱስ ዝም ብሏል፡፡ ሠላሳ አመት በሆነው ጊዜ ግን ሊጠመቅና ይፋዊ አገልግሎት ሊጀምር ወደዮርዳኖስ መጣ፡፡ ኦሪት “አንድ ሰው ሙሉ ሰው ነው ፤ ይፋዊ አገልግሎት ሊያገለግል ይገባል” ብላ “ፈቃድ የምትሰጠው” በሠላሳ አመቱ ነውና፡፡ (ዘኍል.4፥47)

Tuesday 12 January 2016

ወንድሜ ማን ነው? (ክፍል ሦስት)




                                     ዮሴፍና የአባቱ ልጆች ተገናኙ፤

     ምድር ሁሉ በረሃብ በተያዘችበት ዘመን እግዚአብሔር ዮሴፍን በግብጽ ምድር ሀገረ ገዢ አድርጐ፥ ጥበብን ሰጥቶ እህልን አከማቸ፡፡ ያዕቆብ በግብጽ እህል እንዳለ ሲሰማ፥ (ዘፍጥ.42፥1) ልጆቹን ወደዚያ ላከ፡፡ ብንያም ከቤት ቀርቶ አሥሩ “ወንድሞች” ተነስተው ወደግብጽ ወረዱ፡፡ እግዚአብሔር በጊዜው ሊሠራ፥ እነርሱ ከእግዚአብሔር ሃሳብ “ገፋንህ” ብለው ዮሴፍን ወደክብር ሰገነቱ እያስቸኮሉ አቀረቡት፡፡
     ግብጽ ሲደርሱ ሰገዱለት ፤ የዮሴፍ ሕልም ተፈጸመ፡፡ እርሱ አወቃቸው እነርሱ አላወቁትም፡፡ አውቆም ተለወጠባቸው ፤ እነርሱ ግን ለጠየቃቸው ጥያቄ በብዙ መሃላ ሊያስረዱት ፈለጉ፡፡ ሐሰተኞች ሆነው እውነተኞች ነን አሉ ፤ ከፊታቸው ያለውንና ቆሞ የሚያወራቸውን ወንድማቸውን ጠፍቷል ብለው ተናገሩ፡፡ (ዘፍጥ.42፥13)

Tuesday 5 January 2016

“ …ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ” (ማቴ.1፥21)


Please raed in PDF

እንኳን ለበዓለ ልደቱ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ አሜን፡፡
      ለሁለት ሺህ ዓመታት ያልተዘነጋ ፤ ለአንድም ቀን ሳይነሳ የተዋለበት ቀን የሌለ ድንቅ ስም፤ ክርክር ፣ ሙግት ፣ ክህደት ፣ ፍልስፍና ፣ ነቀፋ ፣ ስድብ ፣ ትችት ፣ መሸቃቀጥን ድል ነስቶ ያሸነፈ ፤ ነቢያት ሊሰሙትና ሊያዩት የወደዱት፣ መላዕክት በምስጋና ያደነቁት ግሩም ስም ፤ ባለፈው ፣ ባለውና ገና በሚመጣው ትውልድ ተወዶ ያልተጠገበ ስም ቢኖር ኢየሱስ ብቻ ነው፡፡
    ኢየሱስ የሚለው ቃል “የሹዋ” ለሚለው የዕብራይስጥ ቃል አቻ የግሪክ መጠሪያ ስም ሲሆን፥ ትርጉሙም “እግዚአብሔር ያድናል ፤ እግዚአብሔር ድኅነት ነው” ማለት ነው፡፡ በሌላ ንግግር ኢየሱስ በግሪኩ ሲሆን በዕብራይስጡ ኢያሱ ነው፡፡ ትርጉሙም አንድ ነው፡