Tuesday 29 January 2019

ቤተ ክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 9)

1.8.      ግብረ ሰዶማዊነት

“ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ፤ እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ …” (ሮሜ 1፥26-27)
“… ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ … የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።”   (1ቆሮ. 6፥9-10)
  ኀጢአትን አዘውትረው ለሚሠሩ ሰዎች ሁሉ (ክርስቲያኖችን ጭምር) መንፈሳዊ ሞት የሚያገኛቸው መኾኑን ታላቁ መጽሐፍ ደጋግሞ ተናግሯል (ሮሜ 6፥16፤ 8፥13፤ ገላ. 5፥21፤ ኤፌ. 5፥5-6፤ 1ዮሐ.2፥4፤ 3፥9፤ ያዕ. 1፥15)። ኀጢአትን በተመለከተ ምንም መታለል አይገባም፤ ብዙ ሰዎች በክርስቶስ ሞት ያገኙትን ነጻነት ለራሳቸው የኃጢአት ሥራ በነጻነት ለመፈጸም እንዲያመቻቸው ሲጠቀሙበት እናያለን። ይህንንም በተመለከተ ታላቁ መጽሐፍ፦ “ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ ለአርነት ተጠርታችኋልና፤ ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ፥ … ” (ገላ. 5፥13) እንዲሁም “አርነት ወጥታችሁ እንደ እግዚአብሔር ባሪያዎች ሁኑ እንጂ ያ አርነት ለክፋት መሸፈኛ እንዲሆን አታድርጉ” (1ጴጥ. 2፥16) በማለት በግልጥ ያለምንም ማወላወል አርነታችንን ኀጢአትን ለመፈጸም እንደ መሸፈኛ ማቅረብ እንደማንችል ያስቀምጣል።

Tuesday 22 January 2019

“ከ“መጋቢ”ው የተሻለ መናፍቅ፣ በዚህ ዘመን ይገኝ ይኾንን?”


Please read in PDF

   “ … መጽሐፍ ቅዱስ ማኑዋል አይኾንም ወይ? መጽሐፍ ቅዱስ እኮ፣ የኃጢአታችን ውጤት እንጂ የጽድቃችን ውጤት አይደለም፣ አርፈን ገነት ብንቀመጥ አንድ ሺህ ገጽ መጽሐፍ አይጫንብንም ነበር፣ አዳምና ሔዋን ተንቀዥቅዠው ከገነት ከወጡ በኋላ ነው፣ አንድ ሺህ ገጽ ጉዳችንን የሚዘረዝር ኀጢአት ተዘርዝሮ፤ እርሱማ የጉዳችን ማኑዋል ነው፣ ጠባያችንን አይገልጥም፤ ለዚህ ነው እኔ የኀጢአት ውጤት ነው፣ በነገራችን ላይ ብሉይ ኪዳንም ኾነ አዲስ ኪዳን፣ ቁርአንም ኾኑ ሌሎቹም መጻሕፍት በጠቅላላ ከገነት ከተባረርን በኋላ ለስደተኛ የተጻፉ መጻሕፍት ናቸው፤ ስደተኛውን ለማረጋጋት የተጻፉ መጻሕፍት ናቸው እንጂ፣ ማኑዋልማ ሊኾን አይችልም፤ በግል ልታወራኝ ትችላለህ፣ እኔ የገባኝ ይህ ነው፤”(ጫጫታና ሳቅ፣ ጭብጨባ ከሕዝቡ)

   “መጋቢ” [አ]ዲስ ይህን ንግግር የተናገሩት፣ ዶክተር ምሕረት ደበበ በሚያዘጋጀው፣ “mindset” እየተባለ በሚጠራ መደበኛ ፕርግራም ላይ፣ “ህሊናና ስብዕና” በሚል ርእስ ተዘጋጅቶ በነበረው የውይይት መድረክ  ነው። በውይይቱ ላይ ማናቸውም ሰው መሳተፍ እንደሚችልና “አእምሮን ለመገንባት” በሚል “ዒላማም”፣ የተለያዩ ዝግጅቶች ጭምር እንደሚቀርቡበት ይታመናል። ለዚህም ይመስላል የተለያየ ግንዛቤና ዝንባሌ ያላቸው ሰዎች በፕሮግራሙ ላይ በመጋበዝ ሃሳብ ይሰነዝራሉ፣ የውይይት መነሻ ሃሳቦችን ያቀርባሉ፣ ጥናቶችን ያስደምጣሉ፣ ውይይቶች ይደረጋሉ። ከሚቀርቡት ሰዎች መካከል ደግሞ መጋቢ” አዲስ አንዱ ናቸው።

Tuesday 15 January 2019

ቤተ ክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 8)

Please read in PDF
1.7.   እንደ ወንጌሉ ታላቅ መርሖ አለመኖር
1.7.1.   መርሖ አንድ፦ “ሂዱ”
       ከወንጌል ትውፊትና ዋና መርሖ አንዱ ሂዱ የሚለው ነው። የቤተ ክርስቲያን የዕድሜ ልክ ታላቁ ተልዕኮዋም “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ …” (ማቴ. 28፥19) የሚለው ነው። ቤተ ክርስቲያን ተዘልላ ተቀምጣ የሚመጡትን ብቻ መጠበቅ የለባትም። ውኃ በአንድ ቦታ ሲቀመጥ ይሸታል፤ አማኞችም አንድ ቦታ ሰፍረው እንዲቀመጡ አልተባለላቸውም። እንደ ዘር እንዲበተኑና እየዞሩ ወንጌሉን እንዲሰብኩ እንጂ  (ሉቃ. 10፥1፤ ሐዋ. 8፥4 ፤ 13፥1-4)።

Wednesday 9 January 2019

ቤተ ክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 7)


Please read in PDF


1.5.      በፍርድ ቤት መክሰስና መካሰስ
     በታሪክ እስከ አኹን ያልተሰማ እንግዳ ሆኖ እየሰማን ካለው ነገር አንዱ፣ የቤተ ክርስቲያን የገዛ ልጆቿን ዓለማዊ ፍርድ ቤት አቁማ፤ ጠበቃ ቀጥራ የመክሰሷ ጉዳይ ነው። እንዲህ ያለ ነገር በቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ተከስቶ እንደ ነበር “… ወንድም ወንድሙን ይከሳል፥ ይህም በማያምኑ ፊት ይደረጋልን? እንግዲህ ፈጽሞ የእርስ በርስ ሙግት እንዳለባችሁ በእናንተ ጉድለት ነው” (1ቆሮ. 6፥6-7) በማለት ሐዋርያው አስቀምጧል።

Saturday 5 January 2019

ሕጻኑና እናቱ


Please read in PDF
    የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ከቅድስት ድንግል የመወለዱን ነገር ከጻፉልን ወንጌላውያን አንዱ ቅዱስ ማቴዎስ ነው፤ መሲሑ ተናፋቂው ማስያስ፣ በነቢያት ትንቢትና በአበው ምሳሌ የተነገረለትና የዘመናት ናፍቆት የነበረው ሕጻንና ጌታ፣ አባትና ልዑል ምጡቅ ከኾነው ከአባቱ ከሰማይ ወጥቶ ወደ ሰው ልጆች ኹሉ[ወደ እኛ] በመምጣቱ ተገለጠ፤ ቅዱስ ማቴዎስ ይህን እውነታ የመሲሑን ነገረ ልደት ከአይሁድና ከአሕዛብ የትውልድ ሐረግ ቈጥሮ በመምዘዝ፣ በመዘርዘርም መሲሑን ዘላለማዊ ነገር ግን በሥጋ ዕድሜ የተወሰነ ጊዜ ሊቈጠርለት እንዳለው (1ጢሞ. 2፥6) በመንፈስ ቅዱስ ተነድቶ ጻፈልን።  
   ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ስለሕጻኑና እናቱ ሲናገር፣ ሕጻኑን ቀዳሚና አቻ የሌለው በማድረግ ኹል ጊዜ ያቀርበዋል። በምዕራፍ ኹለት ላይ ብቻ ይህን እውነታ በጕልህ መመልከት እንችላለን፤ “ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩት”፣ “ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ”፣ “እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊት ያዘና …”፣ “ሕፃኑንና እናቱን ያዘና ወደ እስራኤል አገር ገባ”፣ (ማቴ. 2፥11፣ 13፣ 14፣ 21) በማለት በማናቸውም ስፍራ ላይ ከእናቱ በፊት ሕጻኑን በማስቀደም፣ ፊተኛ በማድረግ፣ በማግነን፣ በማላቅ ያስቀምጠዋል[በእርግጥስ ሕጻኑ ያልላቀ ማን ሊልቅ፣ መሲሑ ያልገነነ ማን ሊገንን፣ ኢየሱስ ፊተኛ ያልኾነ ማን ሊቀድም …?]።

Friday 4 January 2019

ቤተክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 6)

Please read in PDF
1.4.     ዐይን ያወጣ ጉበኝነት
·        ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል።
·        ሹም ሲቆጣ ማር ይዞ እደጁ፥ ደስ ሲለው ማር ይዞ እደጁ።
    በምሳሌነት ይህን ተረት አነሳን እንጂ ከዚህ ተመሳሳይነት ያላቸው ተረቶችና ምሳሌያዊ ንግግሮች በተወሰነ መልኩ በባህላችን ውስጥ ተሰንቅረው ለጉበኝነትና ለመታያ ስጦታ የሚሰጡት ኢ ሥነ ምግባራዊና ሞራላዊ ድጋፍ አለ።
    የእግዚአብሔር ቃል በግልጥ፦ “ፍርድን አታጣምም ፊት አይተህም አታድላ ጉቦ የጥበበኞችን ዓይን ያሳውራልና፥ የጻድቃንንም ቃል ያጣምማልና ጉቦ አትቀበል” (ዘዳግ. 16፥19) በማለት ይናገራል። አንድ ሹም ጉቦ ወይም መማለጃን የሚቀበለው እውነቱን ሐሰት፤ ሐሰቱን እውነት ለማለት ወይም ለማድረግ ነው። እውነቱን ሐሰት ስንል ጻድቁን ወይም እውነተኛውን እንበድላለን፤ ሐሰቱን ደግሞ እውነት ነው ስልን ኅጢአተኛውን በጻድቁ ላይ እናሰለጥናለን።