Thursday 28 December 2023

ገብርኤል መልአክ - የመሲሑ ምስክር

 Please read in PDF

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በስማቸው የተጠሩና በስም የታወቁ መላእክት ኹለት ብቻ ናቸው፤ እነርሱም ሚካኤል (ዳን. 10፥13፤ ይሁ. 9፤ ራእ. 12፥7) እና ገብርኤል (ዳን. 8፥16፤ 9፥21)። ከእነዚህ መላእክት ውጭ በስም ተጠቅሰው የሚታወቁ ሌሎች መላእክት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሉም። እኒህ መላእክት በቀደመው ኪዳን ሕዝብ ውስጥ እጅግ የታወቁና ስሞቻቸው በተደጋጋሚ የተጠቀሱ መላእክት ናቸው።

Wednesday 27 December 2023

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፳፮)

 Please read in PDF

1.5.    ወደ መጽሐፍ ቅዱስ መተርጎም፦ ለዚህ እጅግ አያሌ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። በኑዛዜና ቀኖና ውስጥ ከጠቀስናቸው ባሻገር፣ ሌሎች ጥቂት የመጽሐፍ ቅዱስን ክፍሎችን እንዴት ወደ መጽሐፍ ቅዱስ እንደ ተረጐመ እንጥቀስ።

1.5.1. “ … ከክርስቶስ መወለድ በኋላ ያለው የሰው ኹኔታ፣ በምልዓተ ኀጢአት ከደረሰበት ርኩሰት ነጽቷል፤ ተቀድሷል፤ ከድካሙ በርትቷል፤ ከውድቀቱ ተነሥቷል።” [1]