Sunday 29 May 2016

ለካ በተጣዱበት የሚሞቁ ምርጥ አርቲስቶች አሉን?¡¡¡


    አውቃለሁ ፤ ክርስትና የመገለጥ ጉዳይ እንጂ የእውቀት ጉዳይ አይደለም፡፡ ይህን የምለውም በግኖስቲካዊ አቋም ዕውቀትን ከሚያመልኩ ጐን በመሰለፍ ወይም አምርረው ከሚጠሉትም ጐራ ራሴን በመደመር አይደለም፡፡ ክርስትና በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ የሆነውን ቤዛነትና ውጅት ማመንና ይህንንም መንፈስ ቅዱስ በፍጹም መገለጥ የሚያስተምረን ሕያው እውነት ነው፡፡ ይህም የሚሆነው ላመኑትና ለተቀበሉት ብቻ ነው (ዮሐ.1፥12)፡፡

  ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን አምኖ መቀበል ማለት፥ በሕይወታችን ፣ በትዳራችን ፣ በሥራችን ፣ በሁለንተናችን እርሱን ማመንና በተገለጠ ቅዱስ ሕይወት እርሱን ጌታችንን በኑሮአችን መመስከር ማለት ነው፡፡ ጌታ ኢየሱስን ለማመንና ለመቀበልም ሆነ ለማገልገል ፍጹም መሞት ያስፈልጋል፡፡ በትክክል ሳንሞት በትክክል መኖር አንችልም ፤ በትክክል ሳንኖርም በትክክል መሞት አንችልም፡፡ መስቀል ባልፈተነው ጉብዝና እንደመኖር ባዶ ክርስትና የለም፡፡

Monday 23 May 2016

“የ‘ፌስቡክ’ ትውልድ” (ክፍል አንድ)

please read in PDF

    

 ማኅበራዊ ድኅረ ገጾች ለብዙ ዓመታት የተለያዩትን ቤተሰቦች ፣ ዘመዶች ፣ ወገኖች የመገናኘት ምክንያት ሆነው፤ ለንግዱ ማኅበረሰብ ሥራዎቻቸውን በቀላሉ እንዲያስተዋውቁና እንዲያሻሽጡ ፤ ለተጠቃሚውም ዝቅተኛ የገበያ ዋጋ ፣ በጥራትና በዋጋ የተሻለውን ለመምረጥ ፤ በማኅበረሰቡና በአገራት መካከል ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ግንኙነትን ለመፍጠር ፤ የአንዱን ማኅበረሰብ መልካም እሴት ለሌላው ለማስተላለፍ ፣ ለብዙዎች የሥራ እድል ለመፍጠር ፣ ስለተለያዩ ነገሮች የተለጠፉ “አስፈላጊ” የሆኑ መረጃዎችን “ለመጠቀም” ፤  “ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥” (ማቴ.24፥14) ተብሎ እንደተነገረ፥ ወንጌልን “ለዓለሙ ሁሉ” ለማሰራጨትና ለሌሎችንም ፋይዳዎች ያስገኙትን ያህል የዚያኑ ያህል (ምናልባትም በሚበልጥና በከፋ ሁኔታ) አሉታዊ ጎናቸውም እጅግ ሰፊና አሳሳቢ ነው፡፡

Saturday 14 May 2016

ብርሃን ትሆኑ ዘንድ


ያ አሮጌው አዳም ፍጥረትን አስረጀ
በልዞ ቸክኮ  ፤ በኃጢአት ሸለቆ ዘመናትን ፈጀ
አልታዘዝንምና፦ እኛንም አገኘ ፤

Tuesday 10 May 2016

“ለዚህም ነገር እኛ ሁላችን ምስክሮች ነን” (ሐዋ.2፥32)

   
   ደቀ መዛሙርት የተጠሩለት ዋና ዓላማ አንድና ግልጥ ነው፡፡ “መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥” (1ቆሮ.15፥3-4) የሚለውን ሕያው እውነት ለዓለሙ ሁሉ ማወጅና መመስከር ነው፡፡
   
          በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት መንፈስ ቅዱስ ገና ከጽንሰቱ ጀምሮ አብሮ ነበር (ሉቃ.1፥35) ፤ በአገልግሎቱ ጅማሬም መንፈስ ቅዱስ ፍጹም አልተለየውም (ሉቃ.4፥17) ፤ ሲጠመቅም እንደርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ ታይቷል (ማቴ.3፥16) ፤ በትንሣኤውም እግዚአብሔር የሞትን ጣር አጥፍቶለት (ሐዋ.2፥24) እንደቅድስና መንፈስ (ሮሜ.1፥4) ከሙታን መካከል ተነስቷል ፡፡

Thursday 5 May 2016

እውን ከጾምን ምንን ይሆን የተራብነው?


ጌታ ኢየሱስ ከጾመም በኋላ እንደሰውነቱ ተርቧል፡፡ “አርባ ቀን ከዲያብሎስ ተፈተነ። በነዚያም ቀኖች ምንም አልበላም፥ ከተጨረሱም በኋላ ተራበ” (ሉቃ.4፥2) እንዲል፡፡ ጾም የዝግጅት ጊዜ ነው ፤ የዝግጅት ጊዜም ስለሆነ ጌታ ወደአደባባይ አገልግሎት ከመውጣቱ በፊት ጾምን ጾመ፡፡ ከጾመ በኋላ ደግሞ መራቡን እናስተውላለን፡፡ በዓውዱ ያስተዋልን እንደሆን የተራበው መብልን ይመስላል፡፡ ዋናውና ትልቁ የጌታችን ረሃብና ጥም  ምግብና መጠጥ እንዳልሆነ ግን ቅዱስ ወንጌልን ስናጠና እናስተውላለን፡፡
   በአንድ ወቅት በሰማርያ፥ ደቀ መዛሙርቱ ምሳን ሊገዙ ወደከተማ ሄደው ቆይተው፥ ምሳን ገዝተው ሲመለሱ ጌታ ኢየሱስ ከአንዲት ውኃ ልትቀዳ ከመጣች ሴት ጋር ሲያወራ አገኙት፡፡ በአይሁድ ልማድ አንድ ረቢ (ወንድም ቢሆን) ከሴት ጋር (ሚስቱንም ቢሆን) በመንገድ ላይ አያናግርምና እርሷን ያውም ሳምራዊትን ሴት በማናገሩ ደቀ መዛሙርቱ ተደነቁ፡፡ ምሳ እንዲበላ በለመኑት ጊዜ “እርሱ ግን፦ እናንተ የማታውቁት የምበላው መብል ለእኔ አለኝ አላቸው” (ዮሐ.4፥32)፡፡ እነርሱ ከመምጣታቸው በፊት ከሴቲቱ ጋር የአዲስ ኪዳንን የአምልኮ መሠረታዊ ትምህርትን ሲያስተምራትና መሲሕነቱን እየነገራት ነበር፡፡ ከደቀ መዛሙርቱ አንዳቸውም ስለምን ከሴቲቱ ጋር እንደሚያወሩ ጌታንም ሆነ ሳምራዊቷን ለመጠየቅ የደፈረ አልነበረም፡፡