Monday 30 November 2020

ጽዮን፣ ታቦትን አይወክልም!

 Please read in PDF

መግቢያ

በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር አሳታሚነት፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዕሥራ ምዕት(አዲሱ ሚሊኒየም) ላይ “የራስዋን” አዲስ መጽሐፍ ቅዱስ አሳትማለች። መጽሐፉ በተለምዶ “ሰማንያ አሐዱ” ተብሎ የሚጠራ ቢኾንም፣ ነገር ግን አያሌ ግልጽ ስህተቶችን በውስጡ እንደ ያዘ ወይም እንዲይዝ ታስቦበት የታተመ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። በተለይም በግልጽ የተቀመጡና የታወቁ ሐረጋትን በመቀየር ድፍረት ያለበትን ስህተት ሠርቶአል። ከሠራቸው ስህተቶች አንዱም የእግዚአብሔርን ታቦት ለግል ዓላማቸው ከእግዚአብሔር ይልቅ ለማርያም[ለታቦተ ጽዮን] ለመስጠት በሚመች መንገድ ወደ ሴት ጾታ መለወጣቸው ነው።


Wednesday 25 November 2020

በኢየሱስ የሚያፍሩ የማርያም ባርያዎች!

 Please read in PDF

መግቢያ

ተአምረ ማርያምን የስህተት መጽሐፍ ከሚያሰኘው እልፍ ነገሮች አንዱ፣ “ፍጥረት ሁሉ እመቤታችንን ለማመስገን ተፈጠረ፣ የእመቤታችን ክብሯ ምስጋናዋ ሁሉ ተጽፎ ቢኾን ምን ብራና በቻለው ነበር፣ የቤተ ክርስቲያን ልጆች እርስዋን አክብሯት ለእናንተ ለኀጥአን መድኀኒታችሁ ናትና …” የሚሉ ሐረጋትን በመጠቀም፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ከምናውቃት ከኢየሱስ እናት ማርያም በተቃራኒ፣ እንግዳና ልዩ የኾነችውን፣ አምልኮ ወዳድዋን ማርያምን ለመሳል በብርቱ በመጣሩ ነው። ይህ ላይደንቅ ይችላል፤ ነገር ግን ወንጌል ተረዳን፣ መጽሐፍ ቅዱስ አነበብን፣ እንዘምራለን፣ እንሰብካለን፣ ዐሰረ ክህነት አለን … የሚሉቱ ከተአምረ ማርያም ያነሰ እውቀት መያዛቸው፣ ጌታችን ኢየሱስ በናዝሬት ሰዎች የተደነቀውን ያህል እኛም እጅግ እንደነቅባቸዋለን። አለማመናቸው በእውነት ያስደንቃል!

Tuesday 24 November 2020

Monday 16 November 2020

“ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንደዚሁ ትጠፋላችሁ” (ሉቃ. 13፥5)

 Please read in PDF

  ሉቃስ ወንጌላዊው በቅዱስ ወንጌሉ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ለመላለሙ የመጣ መድኀኒት” እንደ ኾነ በስፋት ይጽፍልናል (2፥14፤ 3፥3፤ 9፥52፤ 10፥33)። “ሥጋም የለበሰ ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ያይ” ዘንድ ሰው ኹሉ ንስሐ ይገባ ዘንድ ጌታችን ኢየሱስ በየመንደርና ከተሞች እየተዘዋወረ ማስተማሩን ደጋግሞ ይነግረናል። “መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥” እንዲል፤ (ሐዋ. 10፥38)።

ሉቃስ በወንጌሉ ትኵረት ከሰጣቸው ትምህርቶች አንዱ ደግሞ ንስሐና የክርስቶስን ፍጹም ርኅራኄ ነው፤ በተለይም ደግሞ ማኅበረ ሰቡ ፍጹም ስላገለላቸው ኀጢአተኞች፣ ቀራጮች፣ ሳምራውያን (7፥36፤ 9፥52፤ 10፥33፤ 15፥1፤ 19፥5)፣ ከራሱ ጋር ለተሰቀለው ወንበዴ (23፥39) ክርስቶስ ልዩ ፍቅርና እንክብካቤ እንዳሳየ ሉቃስ አምልቶ ይነግረናል። ሉቃስ፣ ኢየሱስ ለኀጢአተኞች ያሳየውን ርኅራኄ በሚያስደንቅ ዕይታ፣ አንጀት ስፍስፍ በሚያደርግ መልኩ ገልጦልናል። ዛሬም ድረስ ይህ እውነት ፈክቶና ደምቆ መታየቱ እንዴት ይደንቃል!?

Friday 6 November 2020

ሰዱቃዊ ጠባይ ከመያዝ ተጠበቁ!

 Please read in PDF

የሰዱቃውያንን ጠባይ ያጠኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች፦

1-   የመሲሑ ክርስቶስን መምጣት የማይቀበሉና የማያምኑ፣

2-   የሙሴን ሕግ ብቻ እንጂ የመዝሙራትንና የትንቢትን መጻሕፍት የማይቀበሉ፣

3-   ትንሣኤ ሙታንን፣ መላእክትንና መንፈስ ቅዱስን የማይቀበሉና መኖሩንም የማያምኑ(ማቴ. 22÷23-33)፣

4-   ባለጠጐችና በጊዜው በጣም የተሻለውን ቅንጡ ኑሮ የሚኖሩ፣ የካህናት ቡድን የኾኑ፣

Tuesday 3 November 2020