Friday 22 April 2022

የኢየሱስን እንጂ የቆስጠንጢኖስን መስቀል አልወደውም!

 Please read in PDF

መስቀል የክርስትና ማዕከልና ዋና ትምህርት ነው። ያለ መስቀሉ ክርስትና ክብር አልባ ትምህርት፣ ሕይወት አልባ ጉዞ ነው። መስቀሉን ማዕከል ያላደረገ ክርስትና፣ ከውኃ የወጣ ዓሳ ያህል አንዳች ትርጕም የለውም። ከውድቀት ዘመን ጀምሮ፣ የሰው ልጆች “የእግዚአብሔር ጠላትና ለእግዚአብሔር ሕግ የማይታዘዙ፣ ለመገዛትም የማይፈቅዱ” የነበሩትን ያህል (ሮሜ 8፥7)፣ እንዲታዘዙና እንዲመለሱ፣ በሕይወትም እንዲኖሩ ጥሪ የቀረበላቸው፣ በታረደውና በመስቀሉ ላይ በተሰቀለው ጌታ “አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” (ሉቃ. 23፥34) በሚለው፣ የመስቀል ላይ የጣዕር ድምጽ ነው።

Wednesday 20 April 2022

ስለ ወገኔ እንዲህ ብጸልይስ?

 Please read in PDF

ጌታና ቸር የኾንክ አባት ሆይ፤ በአገራችን ላይ ጦርነት እንዳለ፣ ዛሬም ድረስ ሰቆቃው ገና እንዳላበቃ፣ ምጡ እንዳልባጀ፣ ጭንቀቱ እንዳልሰከነ...  ታውቃለህ፤ ደግሞም ይህ ጦርነት የአንድ አገር ሰዎች ኾነን፣ ነገር ግን መዋደድ ተስኖን፣ መፈቃቀር አቅቶን፣ መቀባበል ባንችልበት ነውና እባክህን ትግራዮችንም፤ አማራዎችንም፤ ኦሮሞዎችንም፣ ቤኒሻንጉልንም፣ አፋርንም፣ ሶማሌንም … በጥይት እሩምታ ፍጃቸው፤ በአዳፍኔና በባዙቃ አደባያቸው፤ በጦርና በገጀራ አስወግዳቸው። ነገር ግን ስለ ቅዱሱ ስምህ፣ ስለ ተወደደው አባታዊ ርኅራኄህ ሕፃናቱ አይነኩ፤ ሴቶቹ አይበደሉ፤ አረጋውያኑ አይባዝኑ፣ ባልቴቶቹ አይቅበዝበዙ፤ አካል ጉዳተኞቹ አይሰቀቁ፤ አሮጊቶቹ በበጎ ይታሰቡ፤ ወጣቶቹ በቁመታቸው ልክ አይጋደሙ።

Sunday 17 April 2022

የኛ ዘመን አማኝ!

 Please read in PDF

ገበታ ዘርግተው ርግብ ሚሸቅጡ

የመሥዋዕቱን ዋጋ በብር ሚለውጡ

ጨካኝ ነጋዴዎች የነፍስ ደላሎች

አቅናን እባክህን!

 Please read in PDF

ይገባሃል ክብር መባል ሆሳዕና

ከመስቀሉ ስትሸሽ አልታየኽምና

Monday 11 April 2022

እግዚአብሔር፣ ማርያምን ፈርቶ?!

 Please read in PDF

እግዚአብሔር አምላክ እጅግ የተፈራ አምላክ ነው፤ ቅዱሳት መጻሕፍት ስለ መፈራቱ እንዲህ ይመሰክራሉ፤

   በምስጋና የተፈራህ፥ ድንቅንም የምታደርግ፥ በቅድስና የከበረ እንዳንተ ያለ ማን ነው?” (ዘጸ. 15፥11)

      ስሙ የተቀደሰና የተፈራ ነው።” (መዝ. 111፥9)

እግዚአብሔርን መፍራት የጥበብ ኹሉ መጀመሪያ ነው፤ ደግሞም እግዚአብሔርን መፍራት ከኹሉ ነገር ያወጣል፤ አማኝ በመታመኑም ከኹሉ ነገር ይጠበቃል፤ በሰላምም ይኖራል፤ (ምሳ. 1፥7፤ መክ. 7፥18)፤ ነገር ግን ሰውን ወይም ፍጡርን መፍራት ወጥመድን ያመጣል (ምሳ. 29፥25)። ሰዎችን ስንፈራቸው ሕይወታችንን እስከ መቆጣጠር ይደርሳሉ፤ እናም በኹለንተናችን በእነርሱ አስተያየትና አረማመድ ውስጥ እንድንዘፈቅ ፍጹም በመጫን ያጠምዱናል። እግዚአብሔርን መፍራት ግን ምንም ወጥመድ የለበትም፤ ሳኦል ከእግዚአብሔር ይልቅ ሰውን በመፍራቱ ምክንያት፣ ከንግሥና ዙፋኑ የሚያዋርደውን ታላቅ ስህተት ሠራ፤ “ሳኦልም ሳሙኤልን፦ ሕዝቡን ስለ ፈራሁ፥ ቃላቸውንም ስለ ሰማሁ የእግዚአብሔርን ትእዛዝና የአንተን ቃል በመተላለፍ በድያለሁ።” (1ሳሙ. 15፥24) እንዲል።