Friday 23 February 2018

“ቤተ ክርስቲያንን ያመለጠ ዕድል

      Please raed in PDF
   ቤተ ክርስቲያኑን በማገልግል ረገድ አፄ ዘርአ ያዕቆብን የሚወዳደረው ንጉሥ በተጻፈው በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ የለም፡፡ ለቤተ ክርስቲያኑ ከልቡ አሳቢ ከሆነ፥ ሲሆን ከደቂቀ ኤዎስጣቴዎስ ጋራ ያደረገውን ዕርቅ[1] ዓይነት ከደቂቀ እስጢፋኖስም ጋራ አድርጎ አብሮ ቢሠራ፥ አለዚያም እንዳላየ ቢያያቸው ኖሮ ምናልባት በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ተአምር ይታይ ነበር፡፡ ንጉሡ ደቂቀ እስጢፋኖስን ሲቀጣቸው ክርስቲያኖችን የሚጠሉ ወገኖች አግኝተው እስጢፋኖስን ሲቀጣቸው ክርስቲያኖችን የሚጠሉ ወገኖች አግኝተው እንዲያሠቃዩዋቸው፥ በዚያውም ክርስትናቸው ረክሶ በሰማይም እንዲኰነኑ ቤተ ክርስቲያን ከሌለበት ክርስቲያን ካልሆኑ ሕዝቦች መካከል ወስደው እንዲጥሏቸው ያዝዛል፡፡ ብዙ ጊዜ የፈለገው ሆኖለታል፤ የሰማዩ ኵነኔ በነሱ ላይ መድረስ አለመድረሱን ባናውቅም፥ እስላሞቹ ደም በማስተፋት “ቁጣውን አስተንፍሰውለታል፡፡”

Monday 19 February 2018

Namni nama malee Hafuraa miti! (kutaa 2ffaa)


Please read in PDF

Barsiistootn Sochii Amantii(Faith Mov’t) waa’e namaa maal jedhu?
    Barsisootni Sochii Amantii (Faith Movement) namni hafuura ta’u isaa akkanatti ibsan;
  “Waaqayyoon yeroo Addaam Uumu akkana jedheen, ati DNA kiyya qabda, ana irraa baate waan ta’eef; …” (Ti. Di. Jeeks)

“Yeroon Kitaaba Qulqulluu[1] dubbisuuYasuus “ani dha” bakka jedhu hundatti anis seeqachaa(gammadaa) “eyyee, anis dha jedha” jedheen deebisa” (Keenet Kooplaand)

“Hundi isa kan dhalchu gosa akka isaati. Ilmi fardaa farad, ilmi adurree adurree dha, … kan Waaqayyoo irraa dhalatuus akka Waaqayyoo dha, … “ (Jooys Meeyar)

“… Waaqayyoon hafuura nama ta’e umame biyya lafaa irraa qopheesse, … kan qophesse, kan uume keessa kaa’e, hafuurri foon keessa gale jechuu dha. Lubbuu jechuun qaama 3ffaa ykn waan akkasitii miti…. Kanaaf namni eenyu? Yoo jedhame, hafuura dha, lubbuu qaba, foon keessa bula ken jedhu deebi dha. Namni foon, lubbuu dha hin jettu, namni eenyu? Yoo jedhame, namni hafuura dha…” (Bagaashaw Dassalany)[2]

Thursday 15 February 2018

አንተ ባትወርድልኝ

ከመላእክት ዓለም ወደእንሰሳት በረት
ከመለኮት ሳታንስ ወደሰው ልጅነት

Tuesday 13 February 2018

ዘርፌ ከበደና የመዝሙር ምረቃዋ የተሰቀለውን ኢየሱስን አልገፋ ይኾን?

Pleas read in PDF

      ኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጉባኤያት፣ በንግሥ በዓላት፣ በባዛር ዝግጅቶችና በሌሎችም ላይ ስእላትን፣ ለስእለት የመጡትን እንሰሳትና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ማጫረትና ለሽያጭ ማቅረብ እንግዳ ድርጊት አይደለም። በተመሳሳይ ይዘት በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናትም በአብዛኛው በመጻሕፍትና በካሴት ምረቃ ላይ ማጫረት “የደራ” ተግባር እንደኾነ አንድ ወዳጄ አጫውቶኛል፡፡ ድርጊቱ ከመንፈሳዊ መልኩ ይልቅ ከንግድ ጋር የተያያዘ ስለኾነ፣ በዓለማውያንም ዘንድ ሲዘወተር ይስተዋላል። ጥቂት ምሳሌዎችን ብንጠቅስ፦ በባለፈው ወር ሊዮናርዲ ዳቪንቺ የሳለውን “የጌታ ኢየሱስን” ስእል ለጨረታ መቅረቡን ከወደአውሮጳ ተሰምቶ ነበር፤ እናም፣ አንድ ማንነቱ ያልታወቀ ሰው ገዛው ቢባልም፣ በኋላ ሲጣራ “ከወደሳውዲ አረቢያ ባለሃብቶች” አንዱ መግዛቱን ሲወሳ ነበር። ባለፈው ሳምንት ደግሞ በአገራችን በኢትዮጲያ ከዘፋኞች አንዲቱ፣ “አዲስ” የዘፈን አልበሟን ስታስመርቅ የራሷን ስእል(ፎቶ) በማቅረብ በብዙ መቶ ሺህ ብሮች መሸጧን ሰማን። እጅግ “ወደእኛ” ሲቀርብ ደግሞ፣ ከትላንት በስቲያ እሁድ በብዙ መልካም ዝማሬዎቿ የምናውቃት ዘማሪት ዘርፌ ከበደም፣ አዲስ የሠራችው መዝሙሯን ስታስመርቅ አንዲት የሲዲ መዝሙሯን በማቅረብ አጫርታ፣ በሺህ ብሮች መሸጧን በሩቅ እንሰማ የነበረውን በቅርብ ደግሞ አየን።

Tuesday 6 February 2018

Namni nama malee Hafuraa miti! (kutaa 1ffaa)


Please read in PDF
Seensa
    Jaarraawwan dheeraa duraan eegalee “Namni eenyu ykn maali?” gaaffii jedhuuf; deebiwwan adda addaa fi walfaallesan kennamaa turaniiru. Deebiwwan tokko tokkoo nama gara hooritti kan gad buusan yoo ta’an, tokko tokko immoo nama gara faallaa eenyummaa isaatti kan geesanii dha.[1]
   Hiika eenyummaa namaa ilaalchisee irra caalaan foon isaa wajjiin walqabsiisani hiika itti kennuun; namni jiruu fi jireenya biyya lafaa kanaa alatti akka hinqabane yoo ibsan; isaan kaan immoo Waqayyoo wajjiin walitti hidhuun waggootan kan dhuma hinqabnee fi jiraataa bara baraa godhuun kaa’u. Haata’uti Waa’e uumama namaa kan dubbachuu danda’u kan isa uume ykn argamsisee qofa dha.

Thursday 1 February 2018

“ኢትየጲያ እጆቿን ወደእግዚአብሔር ትዘረጋለች”፤ መቼ?

    Please read in PDF
ይህ ቃል ለዘመናት በኹሉም አብያተ ክርስቲያናት ለማለት በሚያስደፍር መልኩ፣ በተደጋጋሚነት ሲጠቀስ የነበረ ነው፡፡ ቃሉ በአብዛኛው ሲጠቀስና አገልግሎት ላይ ሲውል ያየነው በአዎንታዊና በበጐ ገጽታው እንጂ በተጠቀሰበት ዓውድ ልክ እንደሚገባው ኾኖ አይደለም፡፡ “ኢትዮጲያ እጆቿን ወደእግዚአብሔር ትዘረጋለች” የሚለውን ቃል ሰዎች ሲጠቀሙ ያየኹት፣ “ዘርግታለች ወይም ለእግዚአብሔር ተማርካለች” የሚለውን ቃል በማስገባት ነው፡፡
    ይህን ቅዱስ ቃል የተናገረው ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ነው፤ የሚገኝበትም ክፍል በመዝ.68፥31 ላይ ነው፡፡ ምዕራፉን ጠቅላላ ርእስ እንስጠው ብንል፣ “እግዚአብሔር የድኾች አባት ነው” ወይም “የድል መዝመር” ብለን ልንሰይመው እንችላለን፡፡ በዚህ የመዝሙር ክፍል ውስጥ ብዙ ነገሮች ተካትተዋል፡፡ እግዚአብሔር ተዋጊ ኾኖ ልክ እንደቀድሞ(ዘጸ.15፥3)እንዲመጣ (ከቁ.1-3)፣ ከ4-6 ደግሞ ማኅበሩ ለእግዚአብሔር በቀል የምሥጋና በዓልን እንዲያደርግ ሲጋበዝ፣ ተዋጊው እግዚአብሔር ባደረገው ነገር ላይ የተሰጠ ሰፊ ማብራሪያ (ከቁ.7-18)፣ ስለብድራቱ የቀረበ ውዳሴ (ቁ.19-20)፣ በውጊያው ውስጥ እግዚአብሔር ምን ዓይነት ፍርድ እንደሚያደርግ (ቁ.21-23)፣ ይህ ታላቅና ተዋጊው እግዚአብሔር ጦረኛ ኾኖ መገለጡን፣ “እግዚአብሔርን በጉባኤ፥ ጌታችንንም በእስራኤል ምንጭ” ማኅበሩ እንዲያመሰግኑት መጋበዙ (ቁ.24-31)፣ “አቤቱ፥ ኃይልህን እዘዝ፤ አቤቱ፥ ይህንም ለእኛ የሠራኸውን አጽናው” በማለት ማኅበሩ መጸለዩን፤ (ቁ.28-31) ያካትታል፡፡