Saturday 22 November 2014

ግብረ ሰዶማዊነትና የእኛ ዘመን አገልጋዮች


                          Please read in PDF                  

        ይህ ጽሁፍ በዚህ ብሎግ በመጀመርያ ሲወጣ ተቃዋሚዎች ገጥመውታል፤ በተቃውሞው ምክንያትም ለጊዜው ከዚህ ብሎግ ላይ ለማንሳትና ያለውን ነገር ለማጤን ጥረት አድርጌያለሁ፡፡ ነገር ግን ቁጣውና ተቃውሞው ለእግዚአብሔር ስላላደላና ኃጢአትን ስላልተቃወመ ምንም ሳልቀንሰው ሙሉ ጽሁፉን እንዳለ መልሼ አውጥቼዋለሁ፡፡ ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው ፊት አናደላም፤ የሚያስጨንቀን የቤተ ክርስቲያን ቅድስናና ሸክም እንጂ በእግዚአብሔር ምህረት ላይ ለሚዘብቱና ለክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን መነቀፍ ግድ ለማይላቸው አይደለም!!!
     ስለግብረ ሰዶም ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔር ጉልበት ቤተ ክርስቲያንን ስለሚያሳድፍ ስለየትኛውም ነውር ለክርስቶስ አድልተን ከመገሰጽ ዝም አንልም፡፡ ግብረ ሰዶም አገር እያካለለ ለመሆኑ የቅርብ ሌላ ማሳያ ብናመጣ፤ ሬድዮ ፋና “የአመቱ የፍቅር አሸናፊ ግጥም” ብሎ በግዮን ሆቴል በሸለመው ሽልማትና በራሱ ሬድዮ በትላንትናው ዕለት የለፈፈው ከሴት ለሴት የተጻፈ “የፍቅር ግጥምን” ነው፡፡ መቼም በአገራችን የፍቅር ግጥም ብሎ ከሴት ለሴት የሚጻፍ ይኖራል ብሎ ማሰብ ወይ የአገርን ባህል መናቅ፤ ወይ ግብረ ሰዶምን መደገፍ እንጂ ሌላ ትርጉም አይሰጠውም፡፡  ይህንና ሌላም እየሰማን ዝም ለማለት የተቀበልነው አደራ አይፈቅድልንም፡፡ መልካም ንባብ፡፡ 
 ስለግብረ ሰዶማዊነት በሁለት የተለያዩ ክፍሎች መጻፌና በሁለቱ ክፍሎችም ለጊዜው የነበረኝን ሃሳብ ማጠቃለሌን አልዘነጋውም፡፡ ነገር ግን አሁንም ግብረ ሰዶማዊነት የቤተ ክርስቲያንን ቅድስና ከማርከስ፤ ምድራችንን ለከፋ ጉስቁልናና ርኩሰት አሳልፎ ከመስጠት ያላቆመ ፍጹም ወደመስፋፋት የሄደ ክፉ ርኩሰት ነውና ዳግም ይህንን ርዕስ ማንሳት አስፈልጎኛል፡፡ ለዚህ እውነታ ብዙ የቅርብ ጊዜ ማሳያ ብቻ ማንሳቱ በቂ ይመስለኛል፡፡
    ድርጊቱ የተፈጸመው በምስራቁ የሃገራችን ክፍል ነው፡፡ የሠላሳ ሁለት አመት አጐት የአራት አመት የወንድም ልጁን በእረኝነት ሥፍራ በመሄድ ጫት እንዲቅም ያግባባዋል፡፡ ህጻኑ እንቢ ቢልም ያስገድደዋል፡፡ ጫት እንዲቅም ካስገደደው በኋላ ልጁ ራሱን መቆጣጠር ሲያቅተው ልጁን የግብረ ሰዶም ጥቃት ይፈጽምበታል፡፡ የልጁ የሰገራ ማውጫ ሙሉ ለሙሉ ይቀዳዳል፡፡ ከሆዱ የወጣው የውስጠኛው የሰገራው ክፍል ሙሉ ለሙሉ የልጁን ጠረን ይለውጠዋል፡፡ ልጁ ፍጹም ራሱን ስቶ ሲወድቅ ከወደቀበት ቦታ ተሸክሞት ከወላጆቹ ጓሮ አምጥቶ ጥሎት ይሰወራል፡፡ ከዚያ በኋላ ብዙም ሳይቆይ የልጁ ህይወት ያልፋል፡፡

Friday 14 November 2014

በድል ነሺው ስምህ …


                             Please read in PDF

በጐነት ለዛ አጣ፤
ወዳጅ ከወዳጅም ፥ ፍቅሩ ሆነ ለበጣ፤
መልክ ብቻ ሆኖ፤
እምነት ከኃይል ጦሞ …
ኪሳራ ገነነ፤

Tuesday 11 November 2014

የብርሃን መልአክ የሚመስሉ አገልጋዮች (ክፍል - ሁለት)



3. ደቀ መዛሙርትን ወደኋላ ይስባሉ(ቁ.30)

   ጌታ ኢየሱስ በወንጌል “መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።” ብሏል፡፡  (ማቴ.10፥38) እኛ ሁል ጊዜ ከክርስቶስ በኋላ ነን፡፡ ተፎካካሪ ስላልሆንን ከጐኑ ፤ ወይም የተሻልን ሆነን ከኋላችን የምናስከትለው አይደለንም፡፡ እርሱ ሰባሪ ነውና ሁል ጊዜ ከፊት የሚወጣ ነው፡፡ (ሚክ.2፥13) ተመርቆ የተከፈተው አዲስ፤ ህያው መንገድና (ዕብ.10፥19) ቀድሞም በመንገዱ የሄደበት እርሱ ስለሆነ እኛ የእርሱን ፋናና ፍለጋውን የምንከተል ነን፡፡ (1ጴጥ.2፥21) ይህ ጉዞ የዕለት ተዕለትና ያለምንም ማቋረጥ ልናደርገው የሚገባን ነው፡፡(ሉቃ.9፥23)

Friday 7 November 2014

የብርሃን መልአክ የሚመስሉ አገልጋዮች(ክፍል - አንድ)


                                          Please read in PDF
    
     የመከራው አይነቱና መጠኑ ይለያይ እንጂ ክርስትና ያለመከራ የኖረበት ዘመን የለም፡፡ የትላንት ቄሳሮች ክርስቲያኖችን በማረድ ፤ የኋላ መናፍቃን የእውነትን ወንጌል በማጣመም፤ ፖለቲከኞችም ድርሳኖቻቸውን አግዝፈው መጽሐፍ ቅዱስን “ሊያንኳስሱ” ፤ ህሊናቸውን የሳቱ ፈላስፎች በወንጌሉ ቃል ሊሳለቁ ፤ ሳይንሳዊ ምርምር (ሁሉም አይደለም) ሐለወተ እግዚአብሔርን ሊቃረን … መልከ ብዙ ስህተቶችንና መከራዎችን በክርስትና ውስጥና ላይ ተስተናግዷል፡፡ ይህ ግን ክርስቶስንና ቤተ ክርስቲያንን የተቃወሙትን አደከመ እንጂ፤ ቤተ ክርስቲያንን እንደትክል ድንጋይ በሙሽራዋ ጽናት ዛሬም ህያው ምስክር ሆና አለች፡፡
    ከዚህ የሚከፋው ነገር ግን፥ ከውጪ ሆኖ በግልጥ የሚዋጋው የጠላት አሠራር ሳይሆን በስውር “ሌላ ወንጌል ሳይይዙ”(ገላ.1፥7) እንደብርሃን መልአክ (2ቆሮ.11፥14) ተገልጠው ሊያናውጡ የሚወዱቱ ናቸው፡፡ በዘመናት የሰይጣን ውጊያ ልዩ ልዩ ነው፡፡ ትላንት ጣዖት አቁሞ ያሰግድ የነበረው፤ ዛሬ ያንን ስልት ትቶ ጣዖትን የብርሃን መልአክ አልብሶ በእያንዳንዱ ልብ አቁሟል፡፡ ሰው ዛሬ ከእግዚአብሔር ጋር ላለመገናኘት የራሱ “የብርሃን ምክንያት” አለው፡፡ ያንን “ብርሃናዊ ምክንያት” በጸሎትና በመንፈስ ቅዱስ ሃሳብ ብንመረምረው ግን ጣዖት እንጂ ሌላ ትርጉም የለውም፡፡ ምንም ነገር ቢሆን ለእግዚአብሔር የሆነውን ነገር እንዲሰርቅብን አልተፈቀደለትምና፡፡(ማቴ.10፥37)