Friday 29 April 2016

“ፋሲካ”ውን በኃጢአት ልንፈስከው ቀን ቀጥረን ይሆን?


እንኳን ለብርሐነ ትንሣኤው መታሰቢያ በዓል በሠላም አደረሳችሁ፡፡
      የእስራኤል ልጆች የብሉይ ኪዳኑን ፋሲካ በተለያየ ዘመን እንዴት እንዳከበሩት ስናስተውል እንዲህ የሚመስሉ ቁም ነገሮችን እናገኝበታለን፦
ü በሙሴ ዘመን፦ የመጀመርያው ፋሲካ እንዲፈጸም የተሰጠው ለሙሴ ሲሆን ይህም በፈርዖን ቤት የበኵር ልጅ ሲገደል፥ በቤተ እስራኤል ይህ መቅሰፍት እንዳይደርስና እንዲያልፋቸው (ፋሲካ ማለት ማለፍ ማለት ነውና) ይህም የዘለዓለም ሥርዓት እንዲሆናቸው ተሰጣቸው፡፡ (ዘጸ.12፥14) ለፋሲካው የሚቀርበው ጠቦት በግ “ነውር የሌለበት”(ዘጸ.12፥5) ነው፡፡ ይህ በግ የሚበላው በመራራ ቅጠል እርሾ ከሌለበት ቂጣ እንዲሆን ታዘዋል፡፡ በእነዚህ የበዓል ቀናት እርሾ ያለበትን ቂጣ የሚበላ፦ “ከመጀመሪያውም ቀን አንሥቶ እስከ ሰባተኛው ቀን እርሾ ያለበትን እንጀራ የሚበላ ነፍስ ከእስራኤል ተለይቶ ይጥፋ” (ቁ.15) የሚል ግልጥ ማስጠንቀቂያ አለ፡፡ ስለዚህም ከዚህና ከሌሎችም ማስጠንቀቂያዎች የእስራኤል ልጆች ራሳቸውን ይጠብቁ ነበር፡፡ (ዘኍል.9፥6)

Thursday 28 April 2016

ትዝታዬ ሁነኝ


                                         Please read in PDF

ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰቢያ በዓል እንኳን አደረሳችሁ፡፡


ሁሌ እራገማለሁ የአይሁድን ጥላቻ
ጌታ ኢየሱስን …
ለምን ጠሉት? ብዬ ሙግት ማንሳት ብቻ
ለምን ነው ይሁዳ? ለምን ነው ጲላጦስ?

Sunday 24 April 2016

ሆሳዕና - ንጉሥ ያለቀሰላት ከተማ (ሉቃ.19፥41)

Please read in PDF

“... ከተማይቱን አይቶ አለቀሰላት፥ እንዲህ እያለ፦ ለሰላምሽ የሚሆነውን በዚህ ቀን አንቺስ ስንኳ ብታውቂ፤ አሁን ግን ከዓይንሽ ተሰውሮአል። አንቺንም በአንቺም ውስጥ የሚኖሩትን ልጆችሽን ወደ ታች ይጥላሉ፥ በአንቺ ውስጥም ድንጋይ በድንጋይ ላይ አይተዉም፥ የመጐብኘትሽን ዘመን አላወቅሽምና።” (ሉቃ.19፥41-44)


    መጽሐፍ ቅዱስን በማስተዋል እንደመንፈስ ቅዱስ ተማሪ ቁጭ ብለን ስናጠና፥ ነቢዩ ኤርምያስ አልቃሻው ነቢይ መሆኑን እናስተውላለን፡፡ ኤርምያስን አልቃሻ ያሰኘው፥ የእስራኤልን መጥፋትና መማረክ ፤ የቤተ መቅደሱን መፍረስና የጐበዛዝቱን መውደቅ በተናገረ ጊዜ ሰሚ ማጣቱ ፤ የሕዝቡ አንገተ ደንዳናነት እጅግ ያበሳጨውና ያስለቅሰው ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት እጅግ ረጅም ጊዜ በማልቀሱ አልቃሻው ነቢይ ተብሎ ተጠርቷል፡፡ ነቢይ ሕዝብን ከእግዚአብሔር በአደራ ተቀብሏልና ሕዝቡ በነፍሱ ሳያርፍ፥ ሲቅበዘበዝ ፣ ሲንከራተት ... ሲያይ አብሮ መባዘኑ መንከራተቱ አይቀርም፡፡ እስኪመለሱም እጅግ በማዘን ይተጋላቸዋል ፤ በተመለሱም ጊዜ እጅግ ደስተኛ ነው፡፡ የነቢይ የዘወትር ደስታው የሕዝቡ በአምላኩ መንገድ መሆን ብቻ ነው፡፡   

Tuesday 19 April 2016

በጋምቤላ ፤ በሜድትራኒያን ዳርቻ … የሆነው፥ ለእኛ የ“ንስሐ ግቡ” ደወል ይሆን?




“አባቶቻችሁም እንደ ነበሩ አንገተ ደንዳና አትሁኑ ፤ እጃችሁንም ለእግዚአብሔር ስጡ፥ ለዘላለም ወደ ተቀደሰው ወደ መቅደሱም ግቡ፥ ጽኑ ቍጣውም ከእናንተ እንዲመለስ አምላካችሁን እግዚአብሔርን አምልኩ። አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ ነውና፥ ወደ እርሱም ብትመለሱ ፊቱን ከእናንተ አያዞርምና ወደ እግዚአብሔር ብትመለሱ ወንድሞቻችሁና ልጆቻችሁ በማረኩአቸው ፊት ምሕረትን ያገኛሉ፥ ደግሞም ወደዚህች ምድር ይመለሳሉ።” (2ዜና.30፥8-9)


    ከወደጋምቤላ እናት እስካዘለችው ልጇ ድረስ ተቀልታ በጠቅላላ ከ148 ሰዎች መታረዳቸውን ሰምተን ጆሮዋችን ሳያባራ፥ ከወደሜድትራኒያን ባሕር ዳርቻ ደግሞ ትውልደ ኢትዮጲያውንና ኤርትራውያን ይበዙበታል በተባለ የስደተኞች የባሕር ጉዞ ጀልባ ተገልብጦ ከ400 በላይ ሰዎች መሞታቸውን ተረዳን፡፡ የዛሬ ዓመት ገደማ ኢትዮጲያውያን በዚሁ በሜድትራኒያን ባሕር ዳርቻ በሰው በላው አይ ኤስ አይ ኤስ ዜጎቻችን እንደዋዛ እንደበግ ታርደው ደማቸው በከንቱ ከባሕር ጋር ተቀላቀለ፡፡

Sunday 17 April 2016

ኒቆዲሞስ - ከውኃውና ከመንፈሱ የመወለድ ምስጢር (ዮሐ.3፥5)


“እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም።” (ዮሐ.3፥5)

   ኒቆዲሞስ የማታ ተማሪ ቢሆንም መምሕር ተብሎም ተጠርቷል ፤ ምናልባት ቀን ቀን ሕዝብ በተሰበሰበበትና ጌታን ዙርያውን ሕዝብ በከበበበት ሁኔታ እንደልብ ለመወያየት ስለማይመች ወይም በማታው ክፍለ ጊዜ በደንብ እንወደደው ሊያወራውና ከእርሱ ሊማር ወይም የአይሁድ አለቃ ስለሆነ በቀን መምጣትን ስለፈራ ሊሆን ይችላል፥ ሌሊቱን በቋሚ ተማሪነት በመምጣት የተጋው፡፡ ባለ ሥልጣን እንደመሆኑ መጠን ሰው ሳይልክ ራሱ መምጣቱ ሊማር ፤ ሊረዳ ከልቡ መውደዱን ፤ የመንፈስ ጥማትም ያለበት መሆኑን እናስተውላለን፡፡ ከጌታ ለመማር እርሱ ድካምና ዝለት ፤ ሌሊትና ቀን የማይፈራረቅበት የዘላለም መምህር ነው፡፡ ሲያስተምር በቅንነት ነው፡፡ ከታወቁ ሊቃውንትና ፕሮፌሰሮች የሚማሩ እጅግ ይደነቃሉ ፤ ከእርሱ የሚማሩ ግን እጅግ የተወደዱ ናቸው፡፡

Friday 15 April 2016

አገርም፥ ይህን ያህል ይዘነጋል ለካ!




  መርሳት የተፈጥሮ ባህርያችን ነው ፤ ነገር ግን ጤነኞችና ኃላፊነት የሚሰማን ከሆነ ለዘወትር ልንዘነጋቸው የማይገቡን ነገሮች አሉ፡፡ በጦር ሜዳ ያለ ወታደር ትጥቅና የጦር መሣርያውን ፣ በሙሽርነት ያለች ሴት መጌጥና መዋብን ፣ በበሽተኞች የተከበበ ዶክተርና የሕክምና ባለሙያ ስለሚያክምባቸው የሕክምና መሣርያዎች ፍጹም ሊዘነጉ ከማይችሉ ጥቂት ነገሮች መካከል ናቸው፡፡ እነዚህንና ተመሳሳይ ነገሮችን መርሳት በሕይወት ጭምር አላስፈላጊ ዋጋ ያስከፍላሉ፡፡
   ከምንም በላይ ደግሞ ሕዝብን ለማገልገል በኃላፊነት የተቀመጥን ሰዎች ዘወትር ልመናችን እንደንጉሥ ሰሎሞን ብዙ ሃብትና ብዕል እንዲሰጠን ከመመኘት ይልቅ ሕዝቡን መምራት የሚያስችለንን ማስተዋልና ጥበብን እንዲሰጠን ቢሆን መልካም ነው፡፡ ሰሎሞን ይህንን ስለለመነ (1ነገ.3፥11)፥ “እግዚአብሔርም ለሰሎሞን እጅግ ብዙ ጥበብና ማስተዋል በባሕርም ዳር እንዳለ አሸዋ የልብ ስፋት ሰጠው።” (1ነገ.4፥29) ብሎ ቃሉ ይነግረናል፡፡ ልበ ሰፊነት ብዙ የሚመረምርና የሚያሰላስል ልብ ስለሆነ በዝንጋኤ የማይጠቃ አስተዋይ ልብ ነው፡፡

Sunday 10 April 2016

ገብር ኄር - ለክርስቶስ ባሮች እንጂ ሎሌዎች አይደለንም!

    
  “ገና ያልተሰናሰናለው” ዘመናዊው መናፍቅነት የሆነው፥ ድኅረ ዘመናዊነት ወጣቱን ትውልድና “አዳዲሶቹን አማኞች” እያነሆለለበትና ኃጢአትን ያለገደብ ለማለማመድና ለማስፈጸም ከሚጠቀምበት አንዱ ማቀንቀኛ ሃሳቡ፥ “ሰው ነጻ ፍጡር ፤ ለማንም የመገዛት ግዴታ የለበትም ፤ ተገዝቶም አያውቅም” የሚል የጸና አቋም አለው፡፡ ይህ አባባል ሁለት ነገሮችን ሊናገሩበት ያሰቡ ያስመስላቸዋል ፤ (1) ድኅረ ዘመናዊነትን በልካቸው ለብሰው የታዩት አብዛኛዎቹ ምዕራባውያን ከፈሪሃ እግዚአብሔር ተፋተው “በፊታቸው መልካም መስሎ የታያቸውን በማድረግ፥ ለምናደርገው ነገር ሁሉ ኃላፊነቱን የፈጠረን ይውሰድ የሚል ኅሊና ቢስ ምክንያት ሲያቀርቡ ፤ (2) እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሲፈጥረው የሰጠውን የምርጫ ነጻነት አጣመው ይተረጉሙታል፡፡

Wednesday 6 April 2016

... የዋጠውን እንመነው!



አልማዝ ወርቅ እንቁውን፣ በኲራቱ ያደበሰ፤
ዘረ አዳምን አስጎንብሶ ፣ ብርታት አቅሉን ያፈረሰ፤

Sunday 3 April 2016

ደብረ ዘይት - ጌታ ይመጣል!



     መናፍቃን ከሚክዷቸው የክርስትና መሠረተ ትምህርት አንዱ የክርስቶስን በክበበ ትስብእት ፤ በግርማ መለኮት ዳግመኛ መምጣት ነው፡፡ የክርስቶስ ዳግም መምጣት ትምህርት ክርስትናና አስተምኅሮው የተመሠረተበትና የቆመበት ዋና ዓለቱ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የዳግመኛ መምጣትን ትምህርት ስናነሳ በአብሮነት የሙታንን ትንሣኤ ትምህርት በአንድነት ማንሳታችን የግድ ነው፡፡ ሁለቱ ትምህርቶች ሰፋፊና በየራሳቸው መቆም የሚቻላቸው ቢሆኑም፥ ተያያዥና የማይነጣጠሉ ዋና ዓምዶች ናቸው፡፡
       ቅዱስ ሐዋርያ ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦
“በጌታ ቃል የምንላችሁ ይህ ነውና፤ እኛ ሕያዋን ሆነን ጌታ እስኪመጣ ድረስ የምንቀር ያንቀላፉቱን አንቀድምም፤ ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን። ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ።” (1ተሰ.4፥15-18) (ለአጽንዖት የተሠመረበት የእኔ ብቻ ነው)