Sunday 28 October 2018

ከ“ቄስ” በላይ መኮንንና ከኢዩ ጩፋ ጀርባ የቆመ የዘረኝነት ግንብ

Please read in PDF

   በዘመናችን ባለው ክርስትና ውስጥ፣ እንደ ዘረኝነትና መናፍቅነት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ የተሰፋለት ነውር ኃጢአት ያለ አይመስልም። ኹለቱም መንፈሳዊ ካባ ለብሰው፣ ራሳቸውን ሸሽገው፣ ሾልከው ከመካከላችን ገብተው አሉ። ከኀጢአት ኹነኛ ባሕርያት አንዱ እንዳይታወቅ ራሱን መሸሸግ ነው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ባስተማረው የዘር ምሳሌ ላይ ጠላት እንክርዳድን የዘራው፣ “ሰዎቹ ሲተኙ” ነው፤ (ማቴ. 13፥25) ይህም ማለት ጠላት ዲያብሎስ መልካሙ እርሻ መልካም ብቻ እንደ ኾነ እንዲዘልቅ ፈጽሞ አይፈልግም ማለት ነው።

Saturday 27 October 2018

ከመጽሐፌ፣ ዘለላ ቁም ነገር



 የጻፍኩት መጽሐፍ በጠቅላላ ስምንት ምዕራፎች አሉት፤ የገጽ ብዛቱ ደግሞ ከመጻፌ ምክንያት እስከ መግቢያ ያለውን ሳያካትት፣ 311 ነው፤ የመጽሐፉ ይዘት የእምነት እንቅስቃሴ አማኞች ስለሚያምኑባቸው ዋና ዋና ኢ ክርስቲያናዊ አስተምህሮ በስፋት ያትታል፤ ከዚያ ውስጥ አንዱ ደግሞ የመጽሐፍ ቅዱስ አረዳዳቸው ጠማማና ኢ ዐውዳዊ መኾኑ ዋነኛው ነው፤ ለዚህ “ዘለላ ቁም ነገሬ” እንደ አንድ ማሳያ የተጠቀምኹት፣ ኤሴክ ዊሊያም ኬንየን በአንድ መጽሐፉ ዮሐ. 3፥16 ላይ “… በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና፤” የሚለውን ቅዱስ ቃል ሲያብራራ እንዲህ ይላል፤ “እግዚአብሔር አብ ዓለምን ስላፈቀረ አንድያ ልጁን ሰጥቶአል። ኢየሱስ ክርስቶስም ዓለምን እንዲሁ ስላፈቀረ ራሱን አሳልፎ ሰጠ። እኔም አኹን ዓለምን ስላፈቀርኩ ራሴን አሳልፌ ሰጥቼአለሁ። ምንም ዐይነት ሂስና ስደት ይምጣ ልቤ በዓለም ላይ ምሬትን እንዲያስተናግድ አልፈቅድም። በእነዚህ ሰዎች ላይ ጊዜዬን በከንቱ አጠፋሁ ለማለት ሲዳዳኝ በፊልጵስዩስ በጳውሎስና ሲላስ ላይ የደረሰውን አስታውሳለሁ” ይለናል፤ (የእምነት እንቅስቃሴ - የዛሬዪቱ ቤተ ክርስቲያን ፈተና፤ ገጽ 38-41)

Wednesday 24 October 2018

“እንደ ኦሮሚያ ክልል ቤተ ክህነትን ማቋቋም እፈልጋለሁ”


  ማሳሰቢያ - ረጅም ንባብ ነው!

እነ አባ ገዳ ተሾመ እንዲያው ዝም ብለው ብቻቸውን፣ “የኦሮሚያ ሲኖዶስ ይቋቋም” ለማለት አይደፍሩም፤ ደግሞም ሥልጣንም የላቸውም። ነገር ግን የራሷ “የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች እጅ” እንዳለበት እርግጠኛ ኾኖ መናገር ይቻላል። ለዚህ ደግሞ የነ“ቀሲስ” በላይ እጆች ረጅም ብቻ ሳይኾኑ፣ እሬቻዊ አምልኮ በግልጥ ከክርስትና ጋር ለመስፋት የሚጥሩ ናቸው። “ቄስቻው” በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም ይንቀሳቀስ እንጂ ለቤተ ክርስቲያኒቱ እንጥፍጣፊ ፍቅርና ለክርስትና ደንታ እንደሌለው፣ የዛሬ ሦስት ዓመት በOBS የኦሮሚኛ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ላይ በ“harka fuune” (ቤት ለእንቦሳ) በሚለው ዝግጅት ላይ ከጋዜጠኛ አብዲ ገዳ ጋር “ረዥም” ቃለ መጠይቅ ማድመጥ በቂ ማሳያ ነው።  “የኦሮሚያ ሲኖዶስ የመቋቋም ጥንስስም” ጅማሮው የሰነበተ መኾኑን ማስተዋል አይከብድም፤ ይህን ቃለ ምልልስ ከሰማሁት በኋላ ሊያስተምርና ሊያወያይ እንደሚችል ስላሰብኩበት ተርጉሜው ለማቅረብ ወደድኹ። ይህን ቃለ ምልልስ አንብበው፣ ቃለ ምልልሱ በኋላ “ኦርቶዶክሳዊ ሃሳብ ነው” የሚሉ ይኖሩ ይኾንን? ብዬ መጠየቅ እፈልጋአለሁ፤ አይደለም የምትሉ ደግሞ እንግዲያው “ዘርን ወይም አንድን ክልል ማዕከል ያደረገ ሲኖዶስ” ጥንስሱ ዛሬ እንዳልኾነ፣ አባ ገዳ ተሾመም ኾኑ ሌሎች ይህን እንዲሉ አነሳሽ ኀይላት ከጀርባ እንዳሉ ማሳያ ይኾናል በማለት ነው። የ“ቄስቻው”ንም ማንነት በዚያውም መመልከት ተገቢ ሳይኾን አይቀረወም፤ መልካም ንባብ እላለሁ።
ጋዜጠኛው የቀሲስ በላይን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያላቸውን የሥራ ድርሻ ከተናገረ በኋላ በቀጥታ ወደ ጥያቄ ያመራል።

Saturday 20 October 2018

የዘፍጥረት አጭር ዳሰሳ





ከወንድሜ አዲስ ጋር የኦሪት ዘፍጥረትን የመጀመርያዎቹን ምዕራፎች እንዲህ አብረን አጥነተን ነበር!

Friday 19 October 2018

ቤተ ክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 1)

Please read in PDF

መግቢ
   “ … በቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ላይ ሂስ ማድረግ እንደ ክህደት ስለሚቈጠር ብዙ አስተያየት አልዳበረም። ይህ ባህል ቅዱስ መጽሐፍን ተመራመሩ የሚለው መሠረተ ሐሳብ ተመራመርና እመን ከሚለው ንድፈ ሐሳብ በተቃራኒ እመን ግን አትመራመር ከሚል ንድፈ ሐሳብ ላይ ይመሠረታል።”[1]



      በእርግጥ ዶ/ር ዲበኩሉ ዘውዴ ያቀረቡት ይህ ሐሳብ፣ “እንደ ኢትዮጵያ ልምድ ስለ ፍትሐ ነገሥት ዝግጅትና የትርጉም ሥራ ላይ አብርሃም ወልደ ሐናናጥያን ምንም ሚና እንዳልተጫወተ እየታወቀ አለመተቸቱንና እንደ ወረደ መቀበላችንን በግልጥ ለመናገር ወይም ለመተቸት በማሰብ ነው። እውነታው ግን ለፍትሐ ነገት ብቻ ሳይኾን፣ በጠቅላላው አሁን ያለችውን ቤተ ክርስቲያን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ማለትም አስተምህሯዊ ችግሯን፣ አምልኳዊ ጉድለቷን፣ ሥነ ምግባራዊ ውድቀቷን … በጐላና በተረዳ ጎኑ የሚያጸባርቅ ነው።

Sunday 14 October 2018

ሥራ ፈቶችና ክፉ ሰዎች በደብረ ዘይቷ ቢሾፍቱ!


Please read in PDF

“ … አይሁድ ግን ቀንተው ከሥራ ፈቶች ክፉ ሰዎችን አመጡ ሕዝብንም ሰብስበው ከተማውን አወኩ፥ ወደ ሕዝብም ያወጡአቸው ዘንድ ፈልገው ወደ ኢያሶን ቤት ቀረቡ፤ …” (ሐዋ. 17፥5)
   በሐዋርያው በቅዱስ ጳውሎስ ኹለተኛ ሐዋርያዊ ጉዞ ላይ እጅግ አስደናቂና አሳዛኝ፣ ስደትና ደስታ፣ መከራና ዕረፍት፣ ድብደባና እርካታ ተስተውሎበታል። ቅዱስ ጳውሎስ በሄደበት ኹሉ የሚሰብከውን ወንጌል አሜን ብሎ የተቀበለው አንዳች አካል አልነበረም፤ ከእጅግ ጥቂቶች በቀር፤ የመዳንና የጸጋውን ወንጌል ቅዱስ ጳውሎስ የሰበከው ብዙ ተቃዋሚዎችና አሳዳጆች እረፍት እየነሡት ነው። ከሚሰብከው ወንጌል ጎን ለጎን ተመጋጋቢ ስደትና መከራ፣ እስርና እንግልት አለ! በተሰሎንቄ ከተማ የገጠመው እንዲህ ያለ ነገር ነው።

Saturday 13 October 2018

መጽሐፌን ያሳተምኩበት ደስታዬ ተፈጸመ!

  በአንዳንድ የስልክ ጥሪዎች ውስጥ የሚሰሙ ድምጾች ለዘላለሙ ከልብ ታትመው ይቀራሉ! 2009 . አንድ ሰንበት ሙሌ የተባለ ውድ ወዳጄ አንዲት እህት እርዳታ እንደምትሻ በስልክ ነግሮኝ፣ ስልኳን አቀብሎኝ እንዳገኛት ድልድይ ኾነን። የሄድኩት አንዲት ብቻዋን፣ ተስፋ ቆርጣ ራስዋን ለማጥፋት ዝግጅት አጠናቅቃ የመጨረሻ ኑዛዜዋን ልትነግረኝ ወዳለች አንዲት እጅግ ከሲታ ግን እጅግ ልጅ ወደ ኾነች ሴት ነው።

Friday 12 October 2018

ኮሽ ʻማይል መንግሥት!

Please read in PDF

ኮሽ ʻማይል መንግሥት፣ ስናፍቅ ስናፍቅ፤
ሰውነቴ አለቀ፣ ነፍሴም በመሳቀቅ…

Saturday 6 October 2018

አንተን ካየሁ ወዲያ

Please read in PDF

በፍርሐት ቆፈን ተይዞ
አልጋው በድካም ተከቦ
በሠርጉ እያለቀሰ