Wednesday 26 October 2016

ስለሁለተኛው ዛፍ

Please read ion PDF

ዛሬ ካነበብኩት መጽሐፍ እናንተም እንድትካፈሉ ወደድሁ፤ እናም ታነብቡት ዘንድ ይኸው ጋበዝኳችሁ፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ምሪት ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡ አሜን፡፡
መሪ
     አንባቢ ሆይ! በዚህ መጽሐፍ ከመጀመርያ እስከመጨረሻ ወደ ምሥራቅ  ሔድሁ፤ ወደምዕራብ ተመለስሁ፤ ወደሰሜን ሔድሁ፤ ወደደቡብ ተመለስሁ እያለ ተጽፎ ይገኛል፡፡ ምሥራቅ ሲል መጻሕፍተ ሐዲሳት ማለቱ ነው፡፡ ምዕራብ ሲል መጻሕፍተ ብሉያት ማለቱ ነው፡፡ ሰሜን ሲል የሊቃውንት መጻሕፍት ማለቱ ነው፡፡ ደቡብ ሲል አዋልድ መጻሕፍት ማለቱ ነው፡፡ ዓለም ያለ እንደሆመ ግን መጻሕፍትን ሁሉ ማለቱ ነው፡፡ ይህንም ካስታወቅሁ በኋላ ምሥራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ የሚለው ሀገር እንዳይመስላችሁ፡፡ እግዚአብሔር የልጁን የክርስቶስን ብርሃን በልባችሁ ውስጥ ያብራላችሁ፡፡ አሜን፡፡ ፪ጴጥ.፩፥ ፲፱፡፡
ዕራፍ ፪
ስለሁለተኛው ዛፍ
    ከዚህም በኋላ ወደምሥራቅ ሀገር ዞርሁ፡፡ በዚህም ሀገር፤ ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስ፣ ዮሐንስ፣ የሚባሉ ሰዎች ጌቶች ሆነው ይኖራሉ፡፡ ወደእነርሱም ደጅ የማይደርስ ሰው የለም፡፡
    እኔም ወደ እነርሱ ቤት ስሔድ በመንገድ ዳር አንድ ዛፍ አገኘሁ፡፡ ይህም ዛፍ በቁመትም፣ በመልክም፣ በፍሬም ያንን በመጀመርያ ያየሁትን ዛፍ ይመስላል፡፡ ዮሐ.፲፬፥፱፡፡

Wednesday 19 October 2016

Thursday 13 October 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል አምስት)

መጽሕፍ ቅዱስና ዘረኝነት
መጽሐፍ ቅዱስ ዘረኛነትን በግልጥ ይቃወማል፡፡ ምክንያቱም ፦
1.    ሁላችን ከጥንት አንድና እኩል ነበርን ፤ ነንም!
    እግዚአብሔር ከጥንት የሰው ልጆችን ያየው በአንዱ ሰው በአዳም በኩል ነው፤ የሰው ልጅ በኃጢአቱ የወደቀውና የተበላሸው በአንዱ በአዳም በኩል ነው፤ (ሮሜ.5፥12)፡፡ እንዲሁ ወደአዲስ ኪዳንም ብንመጣ እግዚአብሔር አለምን ሁሉ በምህረት አይኑ ያየው በአንድ ልጁ በኩል ነው ፤ ማለትም እንደአንድ ቤተ ሰብ የቆጠረን በደሙ በተጠራነው ጥሪ ነው፡፡
    በክርስቶስ አንድ ወደሆንነበት ቅድስት ሕብረት ለመሰባሰብ መስፈርቱም ማንነትና ዘር ሳይሆን አብርሃማዊ እምነት መያዝ በቂ እንደሆነ ታላቁ መጽሐፍ ይነግረናል፡፡ “እምነት የእግዚአብሔር ሥጦታ ነው፤ ከመንፈስ ቅዱስም ይገኛል፤ (ገላ.5፥23 ፤ ኤፌ.2፥8 ፤ 2ተሰ.2፥13)፡፡ ሰው በእምነት ይጸድቃል፤ (ሮሜ.3፥28 ፤ ገላ.2፥16) ነገር ግን በእምነት ከክርስቶስ ጋር ስለሚተባበር፥ እግዚአብሔርን ሥራ መሥራት ይጀምራል (ኤፌ.2፥8-10) ስለዚህ ሰው እውነተኛ አማኝ መሆኑ የሚጣወቀው በሥራው ነው”፡፡ [1]

Saturday 8 October 2016

ኢትዮጲያ ሆይ! ላሁኑ ብቻ ያይደለ፥ ላለፈውም ጥፋትሽ ማቅ ለብሰሽ ንስሐ ግቢ!!!


   Please read in PDF

  አቤቱ የሰማይ አምላክ ሆይ፥ ለሚወድዱህና ትእዛዝህን ለሚያደርጉ ቃል ኪዳንንና ምሕረትን የምትጠብቅ፥ ታላቅና የተፈራህ አምላክ ሆይ፥ እኔ ባሪያህ ዛሬ በፊትህ ስለ ባሪያዎችህ ስለ እስራኤል ልጆች ሌሊትና ቀን የምጸልየውን ጸሎት ትሰማ ዘንድ ጆሮህ ያድምጥ፥ ዓይኖችህም ይከፈቱ፤ በአንተ ላይም ያደረግነውን የእስራኤልን ልጆች ኃጢአት እናዘዝልሃለሁ፤ እኔና የአባቴም ቤት በድለናል። እኛም በአንተ ላይ እጅግ ክፉ ሠርተናል ለባሪያህም ለሙሴ ያዘዝኸውን ትእዛዝና ሥርዓት ሕግም አልጠበቅንም። አሁንም ብትተላለፉ በአሕዛብ መካከል እበትናችኋለሁ፤ ወደ እኔ ብትመለሱ ግን ትእዛዜንም ብትጠብቁ ብታደርጓትም፥ ከእናንተ ሰዎች እስከ ሰማይ ዳርቻ ድረስ ምንም ቢበተኑ ከዚያ እሰበስባቸዋለሁ፥ ስሜም ይኖርበት ዘንድ ወደ መረጥሁት ስፍራ አመጣቸዋለሁ ብለህ ለባሪያህ ለሙሴ ያዘዝኸውን ቃል እባክህ አስብ። እነዚህም በታላቅ ኃይልህና በብርቱ እጅህ የተቤዠሃቸው ባሪያዎችህና ሕዝብህ ናቸው። ጌታ ሆይ፥ ጆሮህ የባሪያህን ጸሎት፥ ስምህንም ይፈሩ ዘንድ የሚወድዱትን፥ የባሪያዎችህን ጸሎት ያድምጥ፤ ዛሬም ለባሪያህ አከናውንለት፥ በዚህም ሰው ፊት ምሕረትን ስጠው።” (ነህ.1፥5-11)


      ልብ የሚሰብር ጸሎት የጸለየው የእግዚአብሔር ሰው ቅዱስ ነህምያ ነው፡፡ ነህምያ የስሙ ትርጓሜ “እግዚአብሔር ያጽናናል” ማለት ነው፡፡ በእውነትም ሕይወቱና ንግግሩ እግዚአብሔር ሕዝቡን ሊያጽናናበት የተጠቀመበት ምርጥ ሰው ነው፤ ነህምያ፡፡  ይህ ቅዱስ የእግዚአብሔር ሰው እጅግ የተወደደ፥ ለእኛም ብዙ ምሳሌና ልንማርበት የሚያስችል የቅድስና ሕይወት የነበረው ነው፡፡

Wednesday 5 October 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል አራት)

Please read in PDF
የዘረኛ ሰዎች ባሕርያት
1.    ላውን የሚንቁ
      ዘረኛነት ባህርይው ራሱ “የእኔ ነገር ትልቅ ነው” የሚል ነገር በውስጡ አለበት፡፡ ንቀት ”እኔ ከሌላው እሻለለሁ ወይም እበልጣለሁ” የሚል ክፉ ሃሳብን ያዘለ ነው፡፡ ጀርመናውያን በይሁዲዎች ላይ ከመነሳታቸው በፊት ሲመለከቷቸው የነበረው በንቀት ነበር፡፡ በአገራችንም ያለውን እውነት ብናይ አንዱ ብሔር ሌላውን ብሔር ሲንቅ ያየንበት፤ የምናይበትም ጊዜ ብዙ ነው፡፡ በአንድ ወቅት የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ ለሥራ ጉዳይ ወደአንድ ክልል ሄዶ ነበር፤ በዚያም መኪናችን ቆሽሻ ነበርና ልናሳጥብ ወደአንድ መኪና ማሳጠቢያ ገባን፤ የመኪናችንን ታርጋ ብቻ አይተው በሚጠየፍ ማንነት ነበር አጣቢዎቹ የተመለከቱን፤ ሊያጥቡልንም ፈቃደኞች ስላልነበሩ ትተን ሄድን፡፡ በጥቆማ ግን ወደሌላ ሥፍራ ሄደን አሳጥበናል፡፡ ያጠበልን ልጅም ግን “የታርጋው አከባቢ ነዋሪ” እንደነበር በኋላ ላይ ሰማን፡፡