Monday 27 April 2015

ደማቸው ድምጽ አለው!

                                                   
                                                             Please read in PDF 
                       
   

ከሩቅ የሚሰማ ፣ ከአድማስ ባሻገር፤
ከምድር ዳርቻ ፣ ከቀላያቱ ዳር፤
ሰው ከማይኖርበት ፣ ከዚያ ምድረ በዳ፤
በረሃብና ጥም ፣ ሥጋቸው ቢጎዳ…   

Wednesday 22 April 2015

“ጌታ ሆይ፥ በISIS ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው”




በድጋሚ በግፈኛው ISIS ለተሰው ክርስቲያን ኤርትራውያን ፣ ኢራቃውያን ቤተሰቦች ጌታ መንፈስ ቅዱስ መጽናናትን እንዲያድላቸው ብርቱ ጸሎታችን ነው!!!
    የአንዲት ሕያው ቤተ ክርስቲያን ልዩና የሁል ጊዜ መገለጫ፥ “የእግዚአብሔርን ቃል ለሁሉ በማዳረስ ማስፋትዋና የደቀ መዛሙርትን ቁጥርና እጅግ የሚታዘዙትንም ማብዛቷ ነው፡፡” (ሐዋ.6፥7) የባለበት ሂድ ወይም የእየቀጨጩ ዕድገት ጤናማነቱ ተፈጥሮዐዊም ፤ መንፈሳዊም አይደለም፡፡ በብዛትም በጥራትም ማደግ የጤናማ ተፈጥሮዐዊና መንፈሳዊ ዕድገት መገለጫ ነው፡፡ ወንጌሉ ሕያው ነውና ተበትኖ ፤ ተሰብኮ እንደዋዛ አይቀርም ፤ ሕያው ፍሬንም ያፈራል እንጂ፡፡
     ክርስትና ገና ጉዞውን በጀመረበት ቀደምት ጊዜያት፥ በአንድ የስብከት ርዕስና በአንድ ብርቱ ተአምራት ስምንት ሺህ የሚጠጉ አማኞች ወደአንድ መቶ ሐያው የጌታ ቤተሰብ ተጨመሩ፡፡ ሥራውን ሠሪው መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ የቁጥሩ አጨማመር ከመደመርም ከብዜትም ይልቃል፡፡ እኛ የቀደምንበት አገልግሎት ጠላትን አለጊዜው ያጎለምሳል ፤ ጌታ የቀደመበት አገልግሎት ግን ጠላት ተኩላ እያለ ሥራውን ያሠራል፡፡(ማቴ.10፥16)

Monday 20 April 2015

“ISIS” በድርጊቱ እኛን ምን ያስተምረናል?

              
                          Please read in PDF
                             
           

አስቀድመን በድርጊቱ እጅግ ላዘኑ የሟች ቤተ ሰቦችና ክርስቲያኖች ሁሉ የመጽናናትን መንፈስ አጽናኙ መንፈስ ቅዱስ እንዲያድላቸው እንመኛለን፡፡

     አለሙ እጅግ በክፋት እንደተያዘ (1ዮሐ.5፥19) ፤ ክፉዎችም ምድርን ሊያስጨንቋት እንደሚችሉ ታላቁ መጽሐፍ በግልጥ ይነግረናል፡፡ (ማቴ.24፥21) ክፉዎች ምድርን የሚያስጨንቋት በሦስት ብርቱ ምክንያቶች ይመስለኛል ፦
1.     የእግዚአብሔር ሕዝብ ከእግዚአብሔር ሲለይ፤
2.    ህዝቡ መለየቱን ሳያውቅ ንስሐ ሳይገባ ሲቀር ፤
3.    ያመንነው ወንጌል ጠላትን እጅግ ያስጨነቀው እንደሆን፡፡

Saturday 18 April 2015

እንጭጭ ክርስትና!


                      Please read in PDF       

ጸሎት እወዳለሁ ባ'ምላኬ ፊት መቆም፤
ምጽዋትም ሰጣለሁ ድኀ ለመደጎም፤
አብዝቼ ጾማለሁ ከምግብ ውኃ ርቄ፤

Saturday 11 April 2015

“የተሰቀለው … ተነስቶአል ፥ በዚህ የለም፤” (ማር.16፥6)



Please read in PDF

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ!!!
     የሙታን ትንሳኤ ትምህርት ክርስትና ከቆመባቸው መሠረታውያን ዶግማውያን ትምህርቶች ከሆኑት አንዱና ዋናው ትምህርት ነው፡፡  (1ቆሮ.15፥13 ፤ ዕብ.6፥2) መናፍቃን ከሚመዘኑበት መመዘኛ አንዱ ለትንሳኤ ሙታን ባላቸው የአስተምህሮ አቋም ነው፡፡ የትኛውም አማኝም ሆነ የእምነት አቋም ትንሳኤ ሙታንን በግማሽም ቢሆን ባጠቃላይ ቢክድ በቀደመው ዘመን ከነበሩት መናፍቃን እንደአንዱ መቆጠሩ ምንም የማያሻማ ነው፡፡ ሐዋርያው ለዚህም ነው ፦ “ትንሣኤ ሙታንስ ከሌለ ክርስቶስ አልተነሣማ ፤ ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት ፤ ደግሞም፦ ክርስቶስን አስነሥቶታል ብለን በእግዚአብሔር ላይ ስለ መሰከርን ሐሰተኞች የእግዚአብሔር ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፤ ሙታን ግን የማይነሡ ከሆነ እርሱን አላስነሣውም።” (1ቆሮ.15፥13-15) በማለት አጽንቶ የተናገረው፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ለዚህ በአንቀጸ ሃይማኖቷ “የሙታንን ትንሳኤ እናምናለን” በማለት በግልጥ የምትመሰክረው፡፡

Wednesday 8 April 2015

በኢየሱስ ላይ የተሤረ ሤራ (ሉቃ.22፥3-6)

        
                              Please read in PDF


      የተወደደው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕውር ስላበራ ፣ ለምጻም ስላነጻ ፣ አንካሶችን ስላስኬደ ፣ ደንቆሮችን እንዲሰሙ ስላደረገ ፣ ሽባ ስለተረተረ ፣ ጉንድሾችን ስላዳነ ፣ ጎባጣ ስላቃና ፣ ሙታንን ስላስነሳ ፣ አጋንንትን ስላወጣ (ማቴ.9፥25 ፤ 11፥5-6 ፤ 15፥30-31) ፣ በድካም መንፈስ ተይዘው ለሚሰቃዩት ዕረፍትን ስላደለ (ሉቃ.13፥11) ፣ ኃጢአተኞችን ስለተቀበለና ከእነርሱም ጋር ስለበላ (ሉቃ.15፥2)

Sunday 5 April 2015

ሆሳዕና መባል ይገባዋል!!!



                                                Please read in PDF


       ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባቱና ለእኛ የታዘዘበትን የገዛ ዘመኑን (1ጢሞ.2፥7) በመፈጸም ወደአባቱ ለመሄድ በመወሰኑ ምክንያት ለመጨረሻ ጊዜ ከኢያሪኮ (ማቴ.20፥29 ፤ ማር.10፥46 ፤  ሉቃ.19፥1) “ወደ ኢየሩሳሌምም ከደብረ ዘይት አጠገብ ወዳሉቱ ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ” ሄደ፡፡ ጌታችን ወደኢየሩሳሌም የወጣው አይሁድ እንደሚገድሉት ፤ በእርሱም ላይ እንደተነሳሱ እያወቀ ነው፡፡ (ማቴ.20፥17-19 ፤ ማር.10፥32 ፤ ሉቃ.9፥22 ፤ 44 ፤ 18፥31) ነፍሱን በፈቃዱ ስለበጎቹ ያኖረው ጌታችን (ዮሐ.10፥16) ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ ነው ስለእኛ የሞተው፡፡