Wednesday 27 June 2018

“ነገር ግን ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንዲሁ ትጠፋላችሁ” (ሉቃ. 13፥3)

   ይህንን ቃል የተናገረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ለመናገር ምክንያት የኾነው ደግሞ፣ የአይሁድ ራሳቸውን ንጹሕ አድርገው፣ ሌላውን ግን ፍጹም በደለኛ፤ ኃጢአተኛ አድርገው ማቅረባቸውን በታላቅ የተግሳጽ ቃል በመንቀፍ ነው። አይሁድ ራሳቸውን ንጹህና የተሻሉ አድርገው ለማቅረብ በሌላው ሰው ላይ የደረሰውን ነገር እንደ ታላቅ ማስረጃ አድርገው አቀረቡ። እናም፣ “ጲላጦስ ደማቸውን ከመሥዋዕታቸው ጋር ስላደባለቀው ስለ ገሊላ ሰዎች አወሩለት” (ቁ.1)። ጲላጦስ ይህን ነገር ለምን እንዳደረገ መጽሐፍ ቅዱስ ምክንያቱን አይነግረንም። ነገር ግን ጲላጦስ ይህን ነገር ሥልጣኑን ለማሰንበት ወይም የሮማን ሕግ ስለመሻራቸው ሲል አድርጐት ሊኾን ይችላል፤ በጭካኔው ወደር የለሽ ነበርና።
  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰዎቹ ያወሩለትን ነገር፣ “እነዚህ የገሊላ ሰዎች ይህ ስለ ደረሰባቸው ከገሊላ ሰዎች ሁሉ ይልቅ ኃጢአተኞች የሆኑ ይመስሉአችኋልን?” (ቁ.2) በማለት፣ እጅግ ሞጋች ጥያቄን በማቅረብ መለሰላቸው። ደግሞም በተጨማሪ፣ “ወይስ በሰሌሆም ግንቡ የወደቀባቸውና የገደላቸው እነዚያ አሥራ ስምንት ሰዎች በኢየሩሳሌም ከሚኖሩት ሁሉ ይልቅ በደለኞች ይመስሉአችኋልን?” (ቁ.4) በማለት ያልተብራሩና እጅግ ግልጽ ያልኾኑ ድርጊቶችን ብቻ ተከትለው ፍርድን ለሚሰጡ ወገኖች ምክንዩ ጥያቄን አቀረበላቸው።

Wednesday 20 June 2018

ደቂቀ እስጢፋኖሳውያንና የ“ዲያቆን” ዳንኤል ክብረት የክፋት ሸፍጥ (ክፍል ፭)

Please read in PDF
በእስጢፋኖሳውያን ላይ የደረሰው መከራ
ካለፈው የበለጠ
34. ለየብቻ እየነጠላቸው በእስር መልክ ወደ እስላም ሃገሮች ሁሉ በመበተን[1] አንዳንዶችን በባርነት ሸጧቸዋል፤ በዚያም በጽኑ ጸዋተወ መከራ ውስጥ እንዲያልፉ አስደርጓቸዋል፤[2] [3]
“ ... የመንግሥቱ ምሥራቃዊ ወደ ሆነው ወደ እስላሞች ሀገሮች ይበትናቸው ጀመር። እዚያ በእሥራት፥ በግንድና በማነቆ (እያቆራኙ) ያስጨንቋቸው ነበረ። ደግሞ በማራቆት ሲቀልዱባቸው የአስኬማ ልብሳቸውን እየገፈፉ፥ አቧራ በላያቸው ላይ እያቦነኑ፥ የራስ ጠጉራቸው ሲላጩ እየነጩ፥ ያለምንም ምሕረት በበትር እየደበደቡ፥ ደግሞ በጦር ጫፍ አካላቸውን እየጓጐጡ፥ በእንደዚህ ያነ ሁኔታ ሲያሰቃዩዋቸው ብዙዎቹ ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ።” [4]
35. የላይና የታች ከንፈራቸውን በመግፈፍ ጥርሳቸውን ባዶ አስቀርቷቸዋል፤[5]
36. ስርናቸው አሰብሮ ደም በአፍንጫቸው እንዲጠጡ አስደርጓቸዋል፤[6]
37. ጢምና ጠጒራቸውን ያለ ውኃ በደረቁ አሸልቷቸዋል፤ አስነጭቷቸዋል፤[7]
38. አካላቸውን በጦር ወይም በስለት እንዲወጋ አድርጓል፤ ወግቶ በተበሳው ጠባሳ ስፍራ ጠጠር አስወትፏል፤[8]
39. ከቤተ መንግሥቱ በሚወጣ የሽንትና የሠገራ መተላለፊያ ውስጥ እንዲተኙ፣ ቈሻሻ እንዲፈስባቸውና እንዲከመርባቸው አስደርጓል፤[9]

Saturday 16 June 2018

ደቂቀ እስጢፋኖሳውያንና የ“ዲያቆን” ዳንኤል ክብረት የክፋት ሸፍጥ (ክፍል ፬)


በእስጢፋኖሳውያን ላይ የደረሰው መከራ
   “እብለክሙ ኦ ሕዝበ ክርስቲያን ምዕመናኒሃ ለማርያም ድንግል በክልኤ” ኵሉ ብዕሲ ዘተወክፈ ኪያሆሙ፥ ወዘተሳተፈ ምስሌሆሙ ወዘአንበሮሙ ውስተ ቤቱ ወኀበ ቤተክርስቲያን በውስተ ምድረ ርስቱ እሙኒ ሥዩም ይሠዐር ወይትበርበር ቤተ ንዋዩ፥ ወምድረ ርስቱ ይኩን ለባዕድ።
  ሊቃነ ካህናትኒ ወንቡራነ እድ ወኵሎሙ ሥዩማነ ቤተ ክርስቲያን ወመነኮሳትሂ ወኵሎሙ ሕዝብ ለእመ ተረክቡ እንዘ እኀብኡ ኪያሆሙ፥ ፈድፋደ ኩነኔ ላዕሌሆሙ። ሢመቶሙ ወምድረ ርስቶሙ ይኩን ለካልዕ እስመ ኮኑ ሱቱፋነ ምስሌሆሙ።
  ወእሙንቱሰ ደቂቀ እስጢፋ በአማን አይሁድ እሙንቱ እለ አብዩ ሰጊደ ለማርያም ድንግል በክልኤ ወለ መስቀለ ዋሕድ ወልድ ለእሙንቱሰ ኵነኔሆሙ ሞት።
   ወዘረከቦሙሂ ይኵንኖሙ በፅኑዕ ኩነኔ ወቀቲልሰ ኢይቅትሎሙ፤ አላ ይብጽሖሙ ውስተ ኩርጓኔነ ከመ ንሰማዕ ቃሎሙ። ወከመ ይኩን ፍትሕ ላዕሌሆሙ ወዘተረክበ። ብዕሴ እንዘ ይብሎ ሰላም ለእስጢፋዊ መክፈልቲ ምስለ እለ ተወክፋዎሙ ለደቀቂ እስጢፋ።”
የዚህ አማርኛ ትርጉም፦
“በኹለቱም ጊዜያት ድንግል የምትሆን የማርያም ምዕመናን የኾናችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ሆይ እንዲህ እላችኋለሁ። “ማናቸውም ሰው ሁሉ ደቂቀ እስጢፋን የተቀበለ ከእነርሱ ጋር የተባበረ በቤቱ ውስጥም ያኖራቸው ወይም በቤተ ክርስቲያኑና በርስቱም ምድር ያኖራቸው ቢገኝ፥ ሹመት ያለው ከኾነ ከሹመቱ ይሻር፥ ቤቱም ይዘረፍ ገንዘቡ ኹሉና ያለውም የምድሩ ርስት ለባዕድ ይሁን።
ሊቃነ ካህናት፥ ንቡረ ዕድ የቤተ ክርስቲያን ሹማምንትና መነኮሳትም ሁሉ ሕዝቡም ሁሉ እነርሱን ሲደብቋቸው ከተገኙ በእነርሱ ላይ ከፍ ያለ ቅጣት ይፈጸምባቸዋል። ሹመታቸውና የምድር ርስታቸው ለሌላ ይኹን። ከእነርሱ ጋር ተባብረዋልና ነው።
እነዚህ ደቂቀ እስጢፋ ግን ለድንግል ማርያምና ለአንድ ልጅዋ መስቀል መስገድን እምቢ ያሉ ናቸው፥ በእውነት አይሁድ ናቸው። የእነርሱ ቅጣት ሞት መሆን አለበት። ያገኛቸው ሁሉ በጽኑ መከራ ይቅጣቸው። ቃላቸውን ሰምተን በአደባባያችን ሸንጐ እንድንፈርድባቸው ወደ አደባባያችን ያምጣቸው እንጂ መግደልን ግን እርሱ ራሱ አይግደላቸው። እንደዚሁም ከደቂቀ እስጢፋ የሆነውን ሰው አግኝቶ ሰላምታ የሰጠው ሰው ሁሉ ዕድል ፈንታው ደቂቀ እስጢፋን ከተቀበሉ እንደሚደረግባቸው ይኾናል።”[1]  
   የእስጢፋኖሳውያንን መከራ መናገር በራሱ ያምማል፤ አሰቃቂነቱም ኹለንተናው በዲያብሎስ በተወረሰ ሰው የሚፈጸም እንጂ ሰብአዊ የኾነ ሰው እንኳ እንዲህ ሊያደርግ ፈጽሞ አይችልም። ሰው ለሰው ለመራራት ሰውነትን ማየቱ ብቻውን ይበቃዋል፤ ሰው በእንሰሳ ላይ እንኳ የማይፈጸም አሰቃቂ ተግባርን ከፈጸመ ግን ከሰውነት አንሷል ብሎ ደፍሮ መናገር ይቻላል። ታላቁ መጽሐፍ፣ “ጻድቅ ሰው ለእንስሳው ነፍስ ይራራል፤ የኀጥኣን ምሕረት ግን ጨካኝ ነው” (ምሳ. 12፥10) እንዲል፣ እውነተኛ መንፈሳዊ ልብ ያለው ሰው እንኳ በእግዚአብሔር መልክ ለተፈጠረው ሰው ለእንሰሳ እንኳ ይራራል። እናም ለእንሰሳ መራራት የሚቻለው ሰው፣ ለሰው መራራት ከተሳነው መንፈሳዊነቱ ደባይቷል ማለት ነው።

Thursday 14 June 2018

አያሌ ዲያስፖራ ዛሬም ጥሙ፣ ረሃቡ፣ ናፍቆቱ ግብረ ሰዶማዊነት ነውን?!



    ጥቂት ያይደለው ዲያስፖራው ኢትዮጵያዊ ማንነቴ ግብረ ሰዶማዊ ነው ይላል፤ የክፋት ጥጋችን መገለጫው ይህ ነው፤ እሳትን ከሰማይ አዝንም ልመናችን ይህ ነው፤ ነውር ይከበርልን፤ ዕድፈት ይጽደቅልን፤ ርኩሰት ይደንገግልን፤ ከእንሰሳነት ማነስ ይረጋገጥልን የሚል ዓመጸኝነት በምድራችን እንዲነግሥ እንዲህ ተግተው የሚሠሩ አሉ፤ ምድርን ካላረከሱ የማያርፉ፤ ግልሙትናና ሴሰኝነት፤ አመንዝራና ዝሙት ያላረካቸው ትውልድና ተፈጥሮን ካልተቃረንኩ ብለው ይሞግታሉ፤ ግብረ ሰዶማዊነት እንደ ቅድስና ሕጋዊ ይኹንልን፤ ተገፍተናልና አቁሙን የሚሉ ተማኅጽኖዎች እያየሉ መጥተዋል።

Tuesday 12 June 2018

Namni nama malee Hafuraa miti! (kutaa 4ffaa)


 Kitaaboota Qulquloota yemmuu qorannuu Kakuu Duraanii keessattis ta’e kan Haarayaa keessatti hiikni isaani kan wal fakkaatu ta’u ni hubanna. Kutaan Haal qara waliigala Seera Umamaa; Namni Waaqayyo irraa malee namni ofii isaatiin Waaqayyo akka hintaane, Maddi namaatifi argamni namaas Waaqayyo irraa malee namni akka Waaqayyo durummaa(eternal)kan hinqabne ta’u ifatti ni kaa’u. keessattu jechootni “Bifa fi fakkaatti” jedhan hiikni isaani faalla’e (faalla ta’e) hiikama.

Monday 4 June 2018

ደቂቀ እስጢፋኖሳውያንና የ“ዲያቆን” ዳንኤል ክብረት የክፋት ሸፍጥ (ክፍል ፫)

Please read in PDF
ንጉሥ አለ መስገድ ከጥበብ መጉደል ነውን?

“ … የደረሰባቸው ነገር የደረሰባቸው በኹለት ምክንያት ነው፤ አንድ አባ እስጢፋኖስ ጥበበኛ ባለ መኾኑ ምክንያት ነው፤ ነገሥታቱ ላይ የነበረውን ስህተት ብቻ ከመንቀስና ጳጳሳቱ ላይ ብቻ የነበረውን ስህተት ከመንቀስ ይልቅ እነዚህ ዓይነት የሥነ መለኮት ክርክሮቹንና ነገሥታቱ ላይ ያሉ ተቃውሞዎች ኹለቱን አንድ ላይ ቀላቀላቸው፤ እነዚህ ኹለቱ ሲቀላቀሉ ጠላት አፈሩበት ማለት ነው …” (ዳንኤል ክብረት)

  ዳንኤል ክብረት፣ ለእውነተኞቹ ቅዱሳንና ሰማዕታት ያለውን ንቀትና የራሱን የታሪክ አልኰስኳሽነት በዚህ ንግግሩ ያለኃፍረት በአደባባይ ይገልጣል። ሰማዕታት፣ አላውያንና ጨካኝ ነገሥታትን፣ ገዢዎችን ፊት ለፊት መቃወማቸው የጥበብ መጉደል መንገድ እንደ ኾነ ሊሰብከን ይፈልጋል። “ስገዱልን” የሚሉ ፍጡራንን በመቃወም የሚመጣውን መከራና ከባድ ሰቆቃ ከነገረ መለኮት ጋር የሚቀላቀል “የአላዋቂ ጥበብ” አድርጐ ለማቅረብ ርምጥምጥ ሃሳቦችን ያቀርባል።
  ዳንኤልን፣ እስኪ እኒህን ጥያቄዎች እናንሳለት፤ ሦስቱ ሕጻናት ንጉሥ ናቡከደነጾር በዱራ ሜዳ ላይ ላሠራው ጣኦት፣ “… የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን … ባያድነን፥ አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ” በማለት ፊት ለፊት በግልጥ መቃወማቸውና ከእሳት መጣላቸው ጥበበኛ ባለ መኾናቸው ነውን? (ዳን. 3፥17-18)፣ መርዶክዮስ ለአጋጋዊው ለሐመዳቱ ልጅ ሐማ አንገቱን ሰብሮ ባለ መስገዱ ምክንያት በሱሳ ግንብ ሥር ባሉ አይሁድ ኹሉ ላይ ሞት ማስፈረዱ ከጥበብ መጉደል ነውን? (አስ. 3፥2፤ 15)፣ ዮሐንስ ወንጌላዊ ለንጉሥ ድምጥያስ አልሰግድም በማለቱ በፈላ ዘይት ተቀቅሎ በፍጥሞ ደሴት መጣሉና በዚያ ለብዙ ዓመታት በእስር መቆየቱ ጥበበኛነት ባይታይበት ነውን? ቅዱስ ፓሊካርፐስ በትራጃን ዘመነ መንግሥት ንጉሡ ስገድልኝ ሲለው፣ “ሰማንያ ስድስት ዓመት ሳገለግለው አንድም ቀን ያልበደለኝን ጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን አልበድልም” ብሎ በሕዝብ አደባባይ በእሳት ተቃጥሎ በሰማዕትነት መሞቱ ጥበበኛ አለ መኾንን፤ ከነገረ መለኮት ክርክር ጋር ቀላቅሎ [ተምታቶበት] ነውን? አግናጢዮስ ምጥው ለአንበሳ፣ አረመኔውን ንጉሥ ሊሠማ ባለመውደድ ለአንበሶች የምግብ ሲሳይ የኾነው በውኑ ጥበብ ጐድሎት ነውን? በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከ286 [አንዳንዶች ከ96 ዓ.ም ጀምሮ ያደርጉታል] ዓ.ም እስከ 315 ዓ.ም ድረስ ዘመነ ሰማዕታት ወይም የቤተ ክርስቲያን የስደት ዘመን እየተባለ ይጠራ በነበረበት ዘመን እነዚያ ድንቅ የቤተ ክርስቲያን ከዋክብት የታረዱት፣ ሰም ተቀብተው በሮማ አደባባዮች እንደ ጧፍ ቀልጠው የነደዱት፣ ለአንበሳ የተጣሉት፣ ቆዳቸውን እንደ በግ የተገፈፉት፣ በመንኩራኩር የተፈጩት … አንደኛና ዋነኛው ምክንያታቸው እኮ ለአላውያን ነገሥታት አንሰግድም፣ አንንበረከክም፣ በፊታቸውም አንደፋም በማለታቸው እንደ ነበር የዳንኤል ዐይኖች ምነው ማስተዋል ተሳናቸው? … ነው ወይስ ይህን የታሪክ ክፍል አልመረመረም?! ብለን እንድንጠይቅ ያስገድደናል።

Friday 1 June 2018

ደቂቀ እስጢፋኖሳውያንና የ“ዲያቆን” ዳንኤል ክብረት የክፋት ሸፍጥ (ክፍል ፪)

Please read in PDF
   

   በየዘመናቱ ለቤተ ክርስቲያን እንቆረቆራለን፤ ለእርሷ ዘብ ቆመናል፤ ጠበቃዋ ነን … የሚሉ ሰዎች ቤተ ክርስቲያን በመጻሕፍቶቿ ያልሸገገችውን ሕያው የታሪክ እውነትና የጥቁአንን [የተጠቁትን] የወንጌል ምስክርነት፣ እውነተኛ ሕይወታቸውንም ሊሸፋፍኑ፤ ሊያድበሰብሱ፤ የክፋት ልባቸውን ያለ መከልከል ገልጠው ሲያሳዩና አኹንም ሲያደርጉት ዕያየን ነው። ዳንኤል ክብረት፣ እስጢፋኖሳውያንን “መናፍቅ” ናቸው ለማለት የሚተጋውን ያህል፣ የተፈጸመባቸው ሰቆቃና መከራ ቅንጣት ታህል እንደ ማይሰቀጥጠው ንግግሮቹ ያሳብቃሉ። ለነገሩ መሞት፣ መዋረድ፣ ክፉን በክፉ አለማሸነፍ፣ መነቀፍ ሳይኾን መግደል፣ መሳደብ፣ መደብደብ … እንደ ሃይማኖትና መንግሥተ ሰማያት እንደ ሚያስወርስ “ምግባር ወይም ጽድቅ” በሚቆጠርበት የበዛ ማኅበረሰብ ባለበት፣ ዳንኤል ተቃራኒውን ቢያስብ ወይም ቢያስተምር እንጂ የደረሰባቸው ግፍ ባይገደው ምንም የሚያስደንቅ ነገር አይደለም።

ደቂቀ እስጢፋኖስ ግድያ ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምኅሮ አንጻር እንዴት ይታያል?
    ይህን ርዕስ ማንሳት ቀላልና ምንም የማያደክም ሊኾን ይችላል፤ ምክንያቱም መግደል ግልጽ ኀጢአት ነውና፤ ነገር ግን ሰዎች መግደልን “ቅዱስና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ፍቅድ ሥልጣን እንዳለው” ለማድረግ የማይተረት ተረት፤ የማይደረት ድሪት የለም። “መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ” (ማቴ. 22፥29) እንዲል፣ ከእግዚአብሔር ቃል ውጭ በመውጣት የምንወድቀውና የምንስተው እግዚአብሔር የተናገረንን በትክክል ሳናውቅ ስንቀር ነው። ሰውን መግደል ስህተት፣ ኀጢአት፣ ዓመጽ እንደ ኾነ እናውቃለን፤ ለሃይማኖታችን ክብር ወይም የሚቃወመንን ስንገድል እንኳን ሰው፣ እግዚአብሔር ራሱ እንዲቃወመንና ተዉ እንዲለን አንፈልግም፤ ለሃይማኖታችን በምናደርገው ማናቸውም ነገር እግዚአብሔር ራሱ የእኛ ሎሌ [የሃሳባችንና የድርጊታችን ተካፋይ] እንዲኾን እንፈልጋለን።