Friday 25 August 2023

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፩)

 Please read in PDF

ስመ ሥላሴ ለአማኞች የነገር መጀመሪያም፤ የነገር መጨረሻም ነው፤ “በስመ አብ …” ብሎ የጀመረ አማኝ፣ “ስብሐት ለአብ …” ብሎ መጨረሱ እውነትም፤ እምነትም ነው። ለዚህ ደግሞ ቅዱሳት መጻሕፍት ታላቅ ዋቢ፤ ምስክርም ናቸው። “ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።” (2ቆሮ. 1፥2) ብለው ጀምረው፣ “የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።” (2ቆሮ. 13፥14) ብለው መጨረሳቸው እምነትም፤ የእምነታችን ልምድም ነው።

Wednesday 23 August 2023

አጵሎሳውያንም፤ ጳውሎሳውያንም ወደ ኢየሱስ ኑ!

 Please read in PDF

በዘመናችን አገልጋዮችን ማበላለጥ፣ አንዱን አገልጋይ “ጌታ” ሌላውን “ምንዝር” አድርጐ ማቅረብ ልክ እንደ ጳውሎስ ዘመን ያገጠጠ እውነት ነው። አማኞች የማንም እንዲኾኑ አልተጠሩም፤ በክርስቶስ የተዋጁ አማኞች የክርስቶስ ብቻ እንዲኾኑ የእግዚአብሔር የዘለዓለም ፈቃዱና ዕቅዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ፤ ቀና በሚመስል አመለካከት “እኔ የእገሌ ነኝ” የሚሉትን “እሰይ አበጃችሁ” ሲል አንመለከትም።

Tuesday 22 August 2023

የክርስቶስን ትንሣኤ ጥቅሞች

 Please read in PDF

ከሙታን መካከል ስለ መነሣቱ፣ ቅዱሳት መጻሕፍት በምልዓት የሚመሰክሩት ስለ አንዱ ብቻ ነው፤ እርሱም ክርስቶስ ኢየሱስ። ከክርስቶስ በቀር ከሙታን መካከል የተነሣ እንደ ሌለ ከቅዱሳት መጻሕፍት ባሻገር፣ ሌሎችም መጻሕፍትም በድፍረት ይመሰክራሉ፤ “ስለዚህም ጌታ … በፈቃዱ ሞተ፤ ከተነሣም በኋላ ዳግመኛ አይሞትም፤ ከትንሣኤው በኋላ ግን ጌታ ይህን አልተናገረም፤ ከሰውም ወገን ማንንም ተነሥ፤ ከመቃብር ውጣ አላለም፤ ዳግመኛ እስከሚመጣባት ቀን ድረስ ለሰዎች ኹሉ አንድ ኾነው በሚነሡበት ቀን ሙታን ይነሣሉ አላቸው።” (ሃይማኖተ አበው ዘኤጲፋንዮስ፤ 1988 ዓ.ም፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ ምዕ. 59 ክፍል 13 ቊ. 49 ገጽ 209)።

Saturday 19 August 2023

የጻድቅን ነፍስ የሚሹ ደም አፍሳሾች!

Please read in PDF

“ዶክተር” መስከረም ትባላለች፤ በደቂቀ እስጢፋኖሳውያን ዙሪያ ስለ ተናገረችው “ፈጠራ ክስ” እጅግ ጥቂት ነገር ማለት ወደድኹ። ... ከጥንት ጀምሮ ደቂቀ እስጢፋኖሳውያን ላይ የማያባራ የስም ማጥፋትና የዓመጽ ውሸት ይሰነዘራል። ምናልባት ግን እንደ ማኅበረ ቅዱሳንና ተከታዮቻቸው፣ ደቂቀ እስጢፋኖስን የሚፈራና በእነርሱ ታሪክ ራሱን አስገብቶ ጻድቅ ሊያደርግ የሚሻ ያለ አይመስለኝም። እስጢፋኖሳውያን ትምህርታቸው የጠራ፣ ሕይወታቸው የተመሰከረ ለመኾኑ ለዘመናት ተዳፍኖ፣ እግዚአብሔር በጊዜው በገለጠው ገድላቸው ላይ በትክክል ሰፍሮ አያሌ አጥኚዎችንና ኦርቶዶክሳውያንን እጅ በአፍ አስጭኖ አስደንቆአል።

Friday 18 August 2023

ከኢየሱስ በቀር!

 Please read in PDF

የሙሴ ፍለጋ የኤልያስ ናፍቆት

የአበው ነቢያት ረሃብና ጥማት …

Sunday 6 August 2023

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፳፭)

Please read in PDF

በባለፉት ጊዜያት፣ የ“መድሎተ ጽድቅ” ጸሐፊ፣ የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን በተደጋጋሚ የሚቃወምበትንና የሚጥስበትን መንገድ እያሳየን መቆየታችን ይታወሳል። ዛሬም ጸሐፊው እንዴት ባለ መንገድ የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን እንደሚጥስና እንደማያከብር ማሳየት እንቀጥላለን።

1.4.    አዋልድ[1] መጻሕፍትን እንደ መጻሕፍተ መለኮታውያት ማቅረብ ወይም ቅዱሳት መጻሕፍትን በአዋልድ መጻሕፍት ለመተርጐም ማሰብ፦ የ“መድሎተ ጽድቅ” ጸሐፊ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ከዚህ ቀደም እንደ ተናገርነው፣ የሕይወት ቃልን በብቻነቱ መያዙን አይስትም፤ ግን ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ ያሉት የሕይወት ቃላት ለማዳን፣ የዘላለም ሕይወት ለመስጠት፣ እውነተኛ የቅድስናና የማናቸውም መልካም ነገሮች ኹሉ መለኪያና መመሪያዎች ለመኾናቸው በቂዎች ናቸው ብሎ አያምንም።