Friday 28 June 2013

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ትህትና

   የእግዚአብሔርን ሠሪነትና ሃለዎትን ለመንፈሳችን ከምናስረግጥበት አንዱና ዋናው ትልቅ ሥራ ጸሎት ነው፡፡ ደስታችንንና ሐዘናችንን፣ ምሬታችንናና ጣዕማችንን፣ ከፍታችንንና ውርደታችንን … በሁኔታና በችግር ታጥረን እንኳ የምንናዘዝበት የማይረሳ ርዕስ ጸሎት ነው፡፡ ጸሎት ለመጸለይ ደጅ መዝጋት ያስፈልጋል፡፡ ሁሉ ነገራችንን በሩን ዘግተንበት፥ የልባችንን እልፍኝ ከፍተን ከእግዚአብሔር ጋር የምናወራበት ቃል ጸሎት ነው፡፡ ልብን አዋርዶ በእግዚአብሔር ፊት ለመጸለይ እንደውኃ የሚፈስስ የተሰጠ ሕይወት ይጠይቃል፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ለመሰጠትና ለመፍሰስ ደግሞ የመጀመርያው በር ትህትና ነው፡፡ ትህትና መቅለስለስና መሬት መሬት እያዩ “መሽኮርመም” አይደለም፡፡ ትህትና ራስን ንቆ ባዶነትን መርጦ መንፈስን በጌታ እግዚአብሔር ፊት ማዋረድ ነው፡፡   

Monday 24 June 2013

ኪዳን አለኝ እኔ

Please read in PDF - kidan alegn ene

ንፋሱን ቀስቅሰው
ሞገዱን አናውጠው
ቀስትህን ገትረው
ሰይፍህን ሰይፈው

Wednesday 19 June 2013

ቀድማችሁ ተሰሩ

አብርሃም ተስፋውን በብዙ ሊቀበል
ብዙ አሥርት ዓመታት ፍፁሙን ታግሷል
ሕዝቡን እንዲመራ ቅዱሱ ሲጠራ

Monday 17 June 2013

የተረሳን ለሚያስቡ

Please read in PDF

አውቃለሁ ዘመኔን፥ ከንቱ ያለፈውን፤
በስርቆት በዝሙት፥ በስካር በዘፈን፤
በአድመኝነት ቁጣ፥ በክርክር ቅናት፤
በሽንገላ ፍቅር፥ በርኩሰት መዳራት …

Sunday 2 June 2013

ንስሐውም ይሁን…


ለአደባባይ ኃጢአት
ሌላም ለበደለ በሚገድል ስህተት
ትውልድ ለሚሻገር ለማያቆም ግድፈት
እልፍ ላሰናከለ