Saturday 25 January 2020

“እኔነቴ”ን ልውደድ!

Please read in PDF

ራሴን አልወድም
አንተ ባየኸኝ ልክ “እኔ እኔን” አላይም
እናማ ጌታዬ!

Wednesday 22 January 2020

ንቀት (ክፍል ፯)

ለምን ግን እንናናቃለን?
   አንዳንዶች በመልካቸው ብቻ ይናቃሉ፤ ለምሳሌ፦ በዓረብ ማኅበረ ሰብ ውስጥ ያሉ ጥቁር ዓረቦች፣ ጥቁር ስለኾኑ ብቻ የተናቁ እንደ ኾኑ ይናገራሉ፤[1] አንዳንድ “ቤተ እምነቶች” ንቀትን የማበረታታት ትምህርቶች አላቸው፤ ለምሳሌ፦ ከእነርሱ ቤተ እምነት ውጪ ያሉትን ወይም የቤተ እምነታቸውን ቀኖናና ዶግማ የማይቀበሉትን ማናቸውንም ቤተ እምነቶች መናቅ እንደሚገባቸው ያምናሉ፤ ልክ አብዛኛዎቹ የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናት ወይም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አንዳቸው ሌላውን እንደሚንቁ። እንዲያውም እንደ እስልምና[2]፣ ጅሖቫ፣ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት፣ የእምነት ቃል አገልግሎት፣ ሞርሞንና ተመሳሳይ “ቤተ እምነቶች”፣ ማንኛውም ሰው የእነርሱን ቤተ እምነት ቀኖናና ዶግማ ካልተቀበለና ከእነርሱ ውጭ ካለው ማናቸውም ኅብረት ጋር፣ ኅብረት ቢያደርግ “ከርኩሱ ዓለም ጋር ግንኙነት እንዳደረገ ወይም እንደ ተካፈለ” አጥብቀው ያስተምራሉ።

Sunday 19 January 2020

በጥምቀቱ ከኀጢአተኞች ጋር ተቈጠረ!

Please read in PDF
 
   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጠመቁን ነገር በየዓመቱ በኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት “ታስቦ” ይውላል፤ መታሰቡ “መልካም” ቢኾንም፣ የሚታሰብበት መንገድ ግን ፈጽሞ ከመጽሐፍ ቅዱስ መራቁ፣ እጅግ የሚደንቅ የሚያሳዝንም ነው። በአገራችን “በዓለ” ጥምቀት አብዛኛውን ጊዜ ከመንፈሳዊ ነጸብራቅነቱ ይልቅ፣ ባሕላዊና ʻሃይማኖታዊ ሥርዓት መከናወኛ ብቻ ኾኖ ሲከበርʼ እናስተውላለን። ጭፈራ፣ ሽለላ፣ ʻታቦትʼ እጀባ፣ ሎሚ ውርወራ፣ የአዳዲስ ልብስ ማሳያና … ሌሎችም ተግባራት፣ ልኩንና ገደቡን በጣሰ መልኩ የሚቀርቡት በዚሁ በጥምቀት “በዓል” ቀን ነው። ቤተ ክርስቲያን ወደ ኢየሱሳዊ መንፈሳዊነት ፍጹም አለማዘንበልዋ እንዲህ ላለ ሰፊ ተላላነት ተላልፋ መሰጧን ማስተዋል አያዳግትም።

Thursday 9 January 2020

ጠላቱን ወዳዱ!

Please read in PDF
አዳም!
የሞተው በኀጢአት የተንኮታኮተው፣
ከሰውነት ማማ አዘቅት የወረደው

Monday 6 January 2020

የእግዚአብሔር ቅንአት!

Please read in PDF
የእግዚአብሔር ቅንዓት ይህን ያደርጋል።”
   ነቢየ ልዑል ኢሳይያስ፣ ሕጻኑ ወንድ ልጅ ጌታ ኢየሱስ ከርስቶስ ለእኛ በውድ ስጦታነት እንደ ተሰጠ ይነግረናል። “ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤” በማለት አብ ብዙ ስጦታዎችን ለእኛ ሰጥቶናል፤ ኢየሱስን የሚያህል ስጦታ ግን አልሰጠንም፤ ወደ ፊትም አይሰጠንም፤ የተሰጠን የትኛውም ስጦታ ከኢየሱስ አይበልጥምና። አስቀድሞ በራሱ መልክና ምሳሌ ፈጥሮን፣ የራሱን መልክና አምሳል በእኛ በማኖር ክብሩንና ጽድቁን፣ ዕውቀቱንና አለመሞትን ለኹላችን አድሎናል። እግዚአብሔር ሰውን ቅዱስ አድርጎ በመፍጠሩም፣ ከሌሎች ፍጡራን በተለየ መልኩ፣ ሰው የእግዚአብሔርን ቅድስና ተካፋይ ኾነ።