Tuesday 31 December 2019

ንቀት (ክፍል ፮)

Please read in PDF

ሌሎችን በመናቃቸው ምክንያት የወደቁ ሰዎች

  መጽሐፍ ቅዱስ አያሌዎች ሌላውን በመናቃቸው ምክንያት መውደቃቸውንና መንኮታኮታቸውን በግልጥ ያስተምረናል፤ በዓለም ላይ ከተከናወኑ ጥቂት ያይደሉ ታሪኮች ውስጥ እንኳ፣ ገናና የተባሉትንና ያልተጠበቁትን ሲያዋርድ ተመልክተናል፤ አንብበናል። በተለይም “ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር” የተጻፈልን ሕያው የእግዚአብሔር እስትንፋስ የኾነው መጽሐፍ ቅዱስ፣ በንቀታቸው ምክንያት ስለወደቁት ሰዎች እንዲህ ያስተምረናል፦
1.    የጎልያድ ንቀት
  መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ጎልያድ የጦር ትጥቅ እንዲህ በማለት ይናገራል፤ “… የጌት ሰው ጎልያድ፥ ቁመቱም ስድስት ክንድ ከስንዝር የሆነ፥ ዋነኛ ጀግና መጣ። በራሱም የናስ ቍር ደፍቶ ነበር፥ ጥሩርም ለብሶ ነበር፤ የጥሩሩም ሚዛን አምስት ሺህ ሰቅል ናስ ነበረ። በእግሮቹም ላይ የናስ ገምባሌ ነበረ፥ የናስም ጭሬ በትከሻው ላይ ነበረ። የጦሩም የቦ እንደ ሸማኔ መጠቅልያ ነበረ፤ የጦሩም ሚዛን ስድስት መቶ ሰቅል ብረት ነበረ።” ጎልያድ እንዲህ ያለ አለባበስ በመልበሱና የውጊያ ትጥቅን በመታጠቁ፣ ከፍልስጥኤማውያን ኹሉ አንደኛ አድርጎታል፤ በዚህ ሳይበቃ እስራኤልንና ንጉሡ ሳኦልንም ጭምር በማንቀጥቀጡ የሚደርስበት ፈጽሞ አልተገኘም።


Wednesday 18 December 2019

“በክርስቶስ” - የመከር ሰዓት የመዝሙር መንፈሳዊ መከር!

Please read in PDF
ንደርደር
   መዝሙር ከሰማየ ሰማያት ከመላእክት ዓለም ወደ እኛ ተንቆርቁሮ ፈስሶ፣ ያራሰን ሰማያዊ ጠልና የምንመገበው መና ነው፤ መላእክት የዘላለም ደስታቸው ትዳርና ምድራዊ ብእል አይደለም፤ “እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ” እንደ ተባለው እንዲሁ፣ እኛም በፍጻሜአችን መንፈሳዊ አካል ስንለብስ፣ መንፈሳዊ ቅኔና መዝሙር ተቀኚና ዘማሪ ነን፤ “እነሆ፥ የእግዚአብሔር ድንኳን በሰዎች መካከል ነው ከእነርሱም ጋር ያድራል፥ እነርሱም ሕዝቡ ይሆናሉ እግዚአብሔርም እርሱ ራሱ ከእነርሱ ጋር ሆኖ አምላካቸው ይሆናል፤” በተባለው በበጉ ሰማይ ላይ ፣ የማያቋርጥና የማያባራ አስደማሚና አስደናቂ ምስጋናና ዝማሬ አለ!!!

Monday 16 December 2019

ጌታን አትስቀሉ!

Please read in PDF
ሞት ክፋት ጭንገፋ
ርስቱ እንዳይሰፋ
ኃጢአት እድፈት ርኩሰት
ነግሠው እንዳይገዟት

Thursday 12 December 2019

ንቀት (ክፍል ፭)

Please read in PDF

እግዚአብሔርን የሚንቁ ይናቃሉ!

   እግዚአብሔር ኹሉን በሉዓላዊ ሥልጣኑ ተቈጣጣሪና ገዢ አምላክ ነው፤ ደግሞም ራሱን ዝቅ አድርጐ የሰውን ልጅ ውድቀቱን፤ ውርደቱን ሳይጸየፍና ሳይንቅ በፍቅሩ የቀረበ ገናና ተወዳጅ አምላክ ነው፤ አስቀድሞ እኛን ሲፈጥረንና ከወደቅንም በኋላ ወደ እኛ የቀረበበት፤ ወደ እርሱም እኛን የሳበበት ዋነኛ ምክንያቱ ክብሩን እንድንገልጥ ነው። ከዚህ በተቃራኒ ብንቆም ግን በግልጥ የተነገረ ቃል አለ፤ “ያከበሩኝን አከብራለሁና፥ የናቁኝም ይናቃሉና” (1ሳሙ. 2፥30)።




Tuesday 3 December 2019

ንቀት (ክፍል ፬)

Please read in PDF
የአይሁድና የሳምራውያን መናናቅ
    ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር በመጣበት ጊዜ የአይሁድና የሳምራውያንን ኹኔታ ወንጌላዊው ዮሐንስ እንዲህ በማለት ይገልጠዋል፤ “አይሁድ ከሳምራውያን ጋር አይተባበሩም ነበርና።” (ዮሐ. 4፥9)። በጥንት ታሪክ ሳምራውያን ከአይሁድ ጋር አንድ ነበሩ፤ ነገር ግን ከአሦር ምርኮ በኋላ፣
   “የአሦርም ንጉሥ ከባቢሎንና ከኩታ ከአዋና ከሐማት ከሴፈርዋይም ሰዎችን አመጣ፥ በእስራኤልም ልጆች ፋንታ በሰማርያ ከተሞች አኖራቸው፤ ሰማርያንም ወረሱአት፤ በከተሞችዋም ተቀመጡ። በዚያም መቀመጥ በጀመሩ ጊዜ እግዚአብሔርን አይፈሩትም ነበር፤ እግዚአብሔርም አንበሶች ሰደደባቸው፥ ይገድሉአቸውም ነበር። ስለዚህም ለአሦር ንጉሥ። ያፈለስኻቸው፥ በሰማርያም ከተሞች ያኖርኻቸው የአገሩን አምላክ ወግ አላወቁም፤ የአገሩን አምላክ ወግ አላወቁምና አንበሶችን ሰድዶባቸዋል፥ እነሆም፥ ገደሉአቸው ብለው ተናገሩት። የአሦርም ንጉሥ። ከዚያ ካመጣችኋቸው ካህናት አንዱን ውሰዱ፤ ሄዶም በዚያ ይቀመጥ፥ የአገሩንም አምላክ ወግ ያስተምራቸው ብሎ አዘዘ። ከሰማርያም ካፈለሱአቸው ካህናት አንዱ መጥቶ በቤቴል ተቀመጠ፥ እግዚአብሔርንም እንዴት እንዲፈሩት ያስተምራቸው ነበር። በየሕዝባቸውም አምላካቸውን አደረጉ፥ ሰምራውያንም በሠሩት በኮረብታው መስገጃዎች ሕዝቡ ሁሉ በሚኖሩበት ከተሞቻቸው አኖሩአቸው። … ከመካከላቸውም ለኮረብታው መስገጃዎች ካህናት አደረጉ፥ በኮረብታውም መስገጃዎች ይሠዉ ነበር።  እግዚአብሔርንም ሲፈሩ ከመካከላቸው እንደ ፈለሱት እንደ አሕዛብ ልማድ አምላካቸውን ያመልኩ ነበር። እስከ ዛሬ ድረስ እንደ ቀደመው ልማድ ያደርጋሉ፤ እግዚአብሔርንም አይፈሩም፥ እግዚአብሔርም እስራኤል ብሎ የጠራውን የያዕቆብን ልጆች እንዳዘዛቸው ሥርዓትና ፍርድ ሕግና ትእዛዝም አያደርጉም።  ” (2ነገ. 17፥22-29፤ 33-34)

Wednesday 20 November 2019

ንቀት (ክፍል ፫)

Please read in PDF
ጌታ ኢየሱስ ማንንም አልናቀም!
  “… በተስፋ የተጠበቀው መሲሕ ሌላ ዐይነት ክብር፣ ማለትም የትሕትናን ክብር ለብሶ ነበር በመካከላቸው የተገኘው። አባ ኔቪል ፈጊስ የተባሉ ካህን እንደ ተናገሩት፣ ‘እግዚአብሔር ታላቅ ነው የሚለው የሙስሊሞች እወጃ እውነትነቱ ጉልህ በመሆኑ ያለልዕለ ተፈጥሮአዊ ህልው እገዛ ሰው ሊረዳው ይችላል። እግዚአብሔር ትንሽ ነው የሚለውን ግን ኢየሱስ ለሰው ልጆች ያስተማራቸው እውነት ነው’ …”[1]
   ጌታ ኢየሱስ ወደ ምድር የመጣበት መንገድ እጅግ አስደናቂና ልብን በመደነቅ የሚመላ ነው። የመጣበት መንገዱና ዓላማው ለብዙዎች የሚጥምና የሚጣፍጥ አይደለም፤ በአዲስ ኪዳንም አገላለጥ ጠባብ መንገድ፣ የግመል መርፌ ቀዳዳ ታህል፣ እስከ መስቀል ሞት መታዘዝ፣ የራስ ክብርንና መብትን መተው፣ ባልንጀራን እንደ ራስ መውደድ … በሚል ውብ ሕይወትና ዝንባሌዎች የተመላ ነው።

Wednesday 13 November 2019

ንቀት (ክፍል ፪)

Please read in PDF
እግዚአብሔር አይንቅም!
   እግዚአብሔር አምላክ በክብር የተከበበና በፍቅር የተትረፈረፈ አምላክ ነው፤ እግዚአብሔር ፍጥረትንም ሲፈጥረው በድንቅና በግሩም ክብር ነው፤ “ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ፤ ሥራህ ድንቅ ነው፥ ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች።” (መዝ. 139፥14) እንዲል፣ ሰው በግሩም፤ በድንቅ አድናቆት ተመልቶ የተፈጠረ ነው። መዝሙረኛው እንዲህ ሲል የፈጠርከውን ሰው የምታውቀው አንተ ነህ፤ እኔንም የፈጠርኸኝ አንተ ነህና በሚገባ ታውቀኛለህ፤ ምክንያቱም በእናቴ ማኅፀን ያበጃጀኸኝና በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ ንቁ ኾነህ የተንከባከብኸኝ አንተ ነህ እያለ ነው፣ ያህዌ ኤሎሂምን!

Friday 8 November 2019

አቤንኤዘር

Please read in PDF

አቤንኤዘር አቤንኤዘር መዝሙራችን
ድል አይተናል ተዋግቶልን ረዳታችን
ቅኔ አምጡ ተንጓደዱ በምስጋና
ከሳሽ ወድቋል ጌታ ቀኙን ልኳልና

Monday 4 November 2019

ንቀት (ክፍል ፩)

Please read in PDF
መግቢያ

    ቅዱስ ጳውሎስ ዘርዝሮ ካልጨረሳቸው(ገላ. 5፥19-21) እና ተዘርዝረው ከማያልቁት የሥጋ ሥራዎች አንዱ ንቀት ወይም ሰዎችን መናቅ ነው፤ የሥጋ ሥራዎችን እንዘርዝራቸው ብንል ዳርቻው ኹሉ እንደማይበቃቸው እናውቃለን፤ ነገር ግን ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀሉ ኃይል እኒህንና ሌሎችንም ኃይላት ደካማ በሚመስል መንገድ ሰብሮና በመስቀሉ ጠርቆ አስወግዶአቸዋል። አለቅነት፣ ሥልጣን፣ ኃይል፣ ጌትነት ኹሉ በክርስቶስ ጌትነትና ኃይል ተሽሮአል፤ (ኤፌ. 1፥20-21፤ 3፥10፤ ፊልጵ. 2፥9)። ክርስቶስ በመስቀል ሞቱ የተወደደና ቅዱስ ሕይወት እንኖር ዘንድ በደሙ ፉጨት ጠርቶናል።

Wednesday 30 October 2019

“ሂዱና … ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው።” (ማቴ. 28÷19)

Please read in PDF
   የቤተ ክርስቲያን የመጀመርያና የመጨረሻው ዋነኛ ራዕይና ተልዕኮ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል ለፍጥረት ሁሉ ማድረስና ደቀ መዛሙርት አድርጎ ወደመንግስቱ መሰብሰብ ነው። ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር የመንግሥት ወንጌል ከማገልገል በቀር ሌላ ምንም ተልዕኮ፤ የምትዋደቅለትም ዓላማ የላትም። በስደት ዘመን ሰማዕታት፤በሰላም ዘመን መምህራንና መጋቢዎችን፣ ድንቅ አማኞችን ቤተ ክርስቲያን ያፈራችው በእውነተኛው ዘር በክርስቶስ ህያውና ቅዱስ ዘር በሆነው ቃሉ ነው።

Thursday 24 October 2019

ገና አልተመለከታችሁምን? (ማር. 8፥17)

Please read in PDF
ይህ ጽሑፍ በ2008 ዓ.ም አጋማሽ ላይ በአንድ ሌላ የጡመራ መድረክ ላይ በብዙዎች የተነበበ ነው! መልእክቱ ዛሬም ደማቅ ስለ ኾነ በድጋሚ እንዲቀርብ ኾኖአል!
       ቃሉን የተናገረው በወርቀ ደሙ የዋጀንና ያዳነን መድኅን አለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ደቀ መዛሙርቱ በፈሪሳውያንና በሄሮድስ እርሾ ክፉ ኃጢአት በመዋጥ እንዳይጠፉ ባስጠነቀቃቸው ጊዜ፣ እነርሱ ግን ከማስተዋል ዘግይተው እንጀራ ባለመያዛቸው እንደ ተናገረ አስበው ተነጋገሩ። ጌታ ያየላቸው ዘላለማዊውን ዐሳብ ነው። እነርሱ ግን ገና በሥጋ አዕምሮ ነበሩና ስለ ቍሳዊውና ተበልቶ እዳሪ ስለሆነው እንጀራ አሰቡ። እርሱ ስለመንፈሳዊው ነገር ይነግራቸዋል እነርሱ ግን የሚናገራቸውን እንኳ በወግ አያስተውሉም።

Saturday 19 October 2019

በልብ መጠበቅ

Please read in PDF

ነገርን በልብ ስለ መጠበቅ በመጽሐፍ ቅዱስ በአንድ ምዕራፍ ኹለት ጊዜ የተነገረላት እናት የኢየሱስ እናት ቅድስት ማርያም ናት። ቅድስት ድንግል ማርያምን በተመለከተ ከኹለት ልዩ ልዩ አካላት የሚሰነዘሩትን ነገሮች በጥሙና ለሰማ ሰው ዲያብሎስ ሐሳቡ የተሳካለት ይመስላል። (አንዱ ቤት ከአምላክ እንድትስተካከል አድርጎ፣ ሌላው ቤት ደግሞ ፈጽሞ እንድትጠላ በማድረግ)። ኹለቱም ወገኖች ከመጽሐፍ ቅዱስ አድራሻ ለመራቃቸው እማኙና የመጀመርያው ማስረጃ ያው ታላቁ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። (ስለነዚህ ወገኖች ሌላ የብዕር ቀጠሮ ልያዝና በቀጥታ ወደ ዛሬው ዐሳቤ ላቅና)።

Sunday 6 October 2019

ሾላኮቹ (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF
ምን እንድርግ?
   በባለፉት ጊዜያት እጅግ መልካም ነገሮችን በማንሣት በዚህ ርእስ ሥር ስናጠና ቆይተናል፤ ሾላኮችን ጠባያቸውንና ኹለንተናዊ ባሕርያቸውን አንስተንም ተመልክተናል፤ ከዚህ በመቀጠል ደግሞ እኛ ምን ማድረግ እንደሚገባን በማንሣት የእግዚአብሔርን ቃል እንጫወታለን።
1.      ወደ ቃሉ እንመለስ፦ የሾላኮቹ ያላሳለሰ ተግባራቸው እኛን ከቃሉ መነጣጠል ነው፤ ወደ ቃሉ ልንመለስና ዘወር የምንልባቸውን ማናቸውንም ምክንያቶችና መንገዶችን ጨርሰው ነው የሚዘጉት። ብንመለስ እንኳ ለገዛ ራሳቸው እንዲመች አድርገው ቃሉን ያጣምማሉ እንጂ በትክክል እንድንመለስ አያደርጉም፤ አይፈልጉምም።

Friday 4 October 2019

እሬቻን የማላከብርበት ክርስቲያናዊ ምክንያቴ

Please read in PDF
መግቢያ

   ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ “የፖለቲካው ጡዘት አገራዊ መልኩን በመልቀቁ፣ ብሔርና ሃይማኖት ተደጋፊ” ከመኾን ጋር ተያይዞ፣ የበአላትን ፉክክር ሃይማኖታዊ መልክ ሲያለብሱ እየተመለከትን ነው። ይህ ደግሞ ውል አልባ የኾነ መጠዛጠዝንና መገፋፋትን፣ “እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ!” የሚል ሥጋዊ መቀናናትን ሲያስከትልና ትውልድ የሚመርዙ ተግባራት “ሃይ ባይ” ማጣታቸውንም እንድንመለከት አድርጎናል። ልክ እንደ ዘመነ መሣፍንት፣ “በዚያም ዘመን በእስራኤል ዘንድ ንጉሥ አልነበረም፤ ሰውም ሁሉ በፊቱ መልካም መስሎ የታየውን ያደርግ ነበር።” (መሣ. 16፥7) ተብሎ እንደ ተነገረው፣ የትኛውም ሰውና ብሔር መልካም መስሎ የታየውን ከማድረግ ከልካይ የሌለበትና እግዚአብሔር የተገፋበት የተናቀበት ዘመን ላይ ነን።

Friday 27 September 2019

Lallaba gowwummaa (1Qoro. 1:21)

Please read in PDf
  Waaqayyoon ilma namaa cubbuudhaan bade jiru gara qulqullumaa fi qajeelumaatti deebisuuf; ilma isaa tokkicha Goofta Yasuus Kiristoos gara biyya lafaatti ergee jira. Ilmi isaa tokkichaan haalli inni gara biyya lafaatti ittiin dhufe bayyee kan nama haawachisuufi gammachiisu miti. Tasumaa karaan itiin dhufe kabajaa fi jaalatamummaa biyya lafaa barbaadu hundaaf faallaa ta’eti.



Wednesday 25 September 2019

ሾላኮቹ (ክፍል ፭)


Please read in PDF
ሾላኮች በምን ይታወቃሉ?
   አማኞች ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን በማመናቸው የክርስቶስ ሕይወትና ትምህርት የሚያንጸባርቅ ሕይወት ሊኖሩ ተጠርተዋል፤ ጌታችን ኢየሱስ ቅዱሳን ደቀ መዛሙርቱን እንደ ተናገረው፣ “ልትሄዱና ፍሬ ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ።” (ዮሐ. 15፥16) እንዳለው፣ ደቀ መዛሙርት ፍሬ ሊያፈሩና በፍሬአቸውም ኖረው ሊታዩ ተጠርተዋል። ፍሬ ኹለንተናዊ መገለጫ ነው፤ ጠባያችን፣ አስተሳሰባችን፣ ንግግራችን፣ ድርጊታችን … ኹሉ የፍሬያችን መገለጫ ወይም የኖርንበት መታያችን ነው።


Monday 23 September 2019

ሾላኮቹ (ክፍል ፬)

Please read in PDF
 ባለፈው በተመለከትነው ክፍል ሾላኮቹ ማንን ያስታሉ? ብለን በቀዳሚነት ከቅዱሳት መጻሕፍት ጠቅሰን  “ውነትን ማወቅ የማይወዱ ሞኞች ሴቶችን” እንደሚያስቱ ተመልክተናል፤ ዛሬ ደግሞ የዚኹን ቀጣይ ክፍል እንዲህ እንድታነቡት ጋብዛችኋለሁ፤ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ፤ አሜን።
2.      ዳዲስ አማኞችን፦ አዳዲስ አማኞች ለቃለ እግዚአብሔር ጥማት የተጋለጡ ናቸው፤ ከቃለ እግዚአብሔር ጋር የተያያዘ ማናቸውንም ትምህርቶች ለመስማት ይቸኩላሉ። በተለይም ሾላካ መናፍቃን የሚጠቅሷቸውንና እውነተኛ መምህራን የሚጠቅሷቸውን እውነተኛ ትምህርት ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ጋር በማነጻጸር የትኛው እውነተኛና የትኛው ደግሞ ሾልኮ እንደ ገባ የመለየትና የማስተዋል እንከን አለባቸው።

Wednesday 18 September 2019

ሾላኮቹ (ክፍል ፫)

Please read in PDF

   በባለፉት ኹለት ክፍሎች የመናፍቃንን የሾላካነት ጠባይ መመልከታችን አይዘነጋም፤ ከዚያ በመቀጠል ዛሬም እንመለከታለን፤ የጌታ ጸጋና ሰላም ከኹላችሁ ጋር ይኹን፣ አሜን፡፡
4.      ዩነትን ወይም እንግዳ ዘርን ለመዝራት፦ ጌታችን ኢየሱስ እንክርዳድ ዘሪው ክፉ፣ ማንም ሳያየው በሌሊት ወይም ጨለማን ለብሶ በመሹለክ ተግባር እንዳደረገው ነግሮናል፤ ጠላት እንክርዳድ የዘራው በዚያው መልካሙ ዘር በተዘራበት እርሻ ላይ ነው፤ አበቃቀሉም ኹለቱም በአንድነት በቀሉ፤ የስንዴውም የእንክርዳዱም አበቃቀላቸው ተመሳሳይና አንዱን ከሌላው ለመለየት እጅግ አዳጋች እንደ ኾነ፣ “እንክርዳዱን ስትለቅሙ ስንዴውን ከእርሱ ጋር እንዳትነቅሉት አይሆንም” (ማቴ. 13፥29) ከሚለው ከጌታችን ኢየሱስ ንግግር እናስተውላለን።

Wednesday 11 September 2019

መጨመሩን ሳይኾን

Please read in PDF

አዲስ ዐመት መጣ ዘመን ተጨመረ
ፊተኛው አረጀ አዲስ ተሞሸረ                                                               
ይህ ለእኔ አይደለም ላመንኩት በልጁ  ... 

Monday 2 September 2019

ሐዋ. 2 ላይ የብሔርተኞቹ ሸቃጭነት!



በቃሉ ውስጥ ባዕድ ዐሳብ ቀላቅሎ ማቅረብና መሸቀጥ ለመጽሐፍ ቅዱስ እውነት የማይታዘዙ ሰዎች ኹነኛ መገለጫ ነው (2ቆሮ. 2፥17፤ 4፥2)፤ ከሰሞኑ የተነሡት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም፣ ዝቅ ብለውና ወርደው “በክልል ደረጃ፣ በአንድ ብሔር ስም” ክርስትናን “እንመስርት” ባዮቹ አካላት፣ እጅግ ድፍረት በተሞላበት ንግግር መጽሐፍ ቅዱስን ጠቅሰው፣ ይህን እኩይና እቡይ ድርጊታቸውን እንደሚደግፋቸው ሲጠቅሱ ሰምተናቸዋል፤ በቋንቋና በብሔር ክርስትናን ለመደራጀት እንደሚፈቅድላቸው ከጠቀሱት ጥቅስ አንዱ ደግሞ  የሐዋርያት ሥራ ኹለትን ነው።

Friday 30 August 2019

የቄሳር ተላላኪ “ቀሳውስት” - ሠርግና ምላሽ



ቤተ ክርስቲያን ከመንግሥት ጋር “ተቃራኒ” በነበረችባቸው ዘመናት፣ ማለትም ነገሥታት ጸረ ክርስትና አቋም ይዘው ተነሥተው በነበሩባቸው ዘመናት፣ ቤተ ክርስቲያን ከሩቅ የሚታይ አብረቅራቂ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋን ተጐናጽፋ ነበር፤ ከአንድ መቶ ሃምሳ ዓመታት በላይ ከኔሮን ቄሣር እስከ ዲዮቅልጥያኖስ የዘለቀው ጽኑ የመከራ ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንደ ቦኸር በዐለት ላይ ተከላት እንጂ፣ ፈጽሞ ካመነችው እውነትና ከመንፈስ አንድነቷ አላነወጣትም፤ አልከፋፈላትም፡፡ መከራ ማጥሪያዋ ብቻ ሳይኾን መጽናኛዋም ጭምር ነበር፡፡

Tuesday 27 August 2019

ሾላኮቹ (ክፍል ፪)

Please read in PDF
2.   መስረቅ፦ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጐች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤” በማለት ሲናገር ሾላኮቹ ራሳቸውን በማመሳሰልና በመደበቅ የተካኑ መኾናቸውን እየነገረንም ጭምር ነው፤ (ዮሐ. 10፥1)። ሌባ በባሕርይው ተደብቆ ወይም ሾልኮ እንጂ በግልጽ መግባትን አያውቅም። ይህንም የሚያደርገው ተቀዳሚ ዐላማው የእርሱ ያልኾነውን ነገር፣ ለራሱ ጥቅምና ፍላጎት ለመስረቅና ለመውሰድ ነው።

Monday 19 August 2019

ከኢየሱስ በቀር!

Please read in PDF
ሙሴ ቢናገርም ኤልያስ ቢያወራም፣
ጴጥሮስ ሦስት ዳስን ለመሥራት ቢነቃም፣
ከክብሩ ነጸብራቅ ከመንግሥቱ በቀር

Monday 12 August 2019

ሾላኮቹ (ክፍል ፩)

Please read in PDF
   መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ ቃል ሐራጥቃ[1] የኾኑ መናፍቃንን ጠባያቸውን ሊገልጥ በሚችል መንገድ፣ ሾላኮች ወይም ወደ ቤቶች ሾልከው የሚገቡ በማለት ይጠራቸዋል፤ (ገላ. 2፥4፤ 2ጢሞ. 3፥6፤ ይሁ. 4)። ቅዱስ ጳውሎስ ወደ እግዚአብሔር አደባባይና ወደ አማኞች የሚገቡት እንደ ሰላይ ነው ይለናል፤ ጌታችን ኢየሱስ ደግሞ ከአማኞች ጋር ልዩነት የሌላቸው እስኪመስሉ ድረስ “እንደ ተኩላ” (ማቴ. 7፥15) ነው ይለናል፤ ሰላይ መመሳሰልን ገንዘብ ያደርጋል፤ ተኩላም ኹለ ነገሩ ከበግ ጋር አንድ ዓይነት መኾንን ይመርጣል፤ ይህን ተፈጥሮአዊ ተመሳስሎታቸውን የሚጠቀሙት ግን የሚፈልጉትን ለማግኘት ወይም በጭካኔያቸው ለመንጠቅና በግን በሕይወቱ ቦጫጭቀው ለመብላት ነው።

Saturday 3 August 2019

የእምነት እንቅስቃሴ አማኞች መጽሐፍ ቅዱስን በዐውድ አያውቁትም!

Please read in PDF
ዐውድ አንድን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ለመረዳት ወሳኝ ነው፤ ዐውድን አለመረዳት ጠቅላላ የመጽሐፉን ዐሳብ አለመረዳት ነው፤ መንፈስ ቅዱስ ቀድሞ የተናገረውን ያብራራልናል ይገልጥልናል እንጂ፣ አዲስ መገለጥም ኾነ ኢየሱስ ከተናገረው የተለየ የሚነግረን ምንም ነገር የለውም፤ ይህም በዐውድ ውስጥ ልንረዳው እንችላለን ማለት ነው፡፡ ከመንፈስ ቅዱስ ቀጥሎ፣ ዐውድ የቀደመው መልእክት ለዝንተ ዓለም ዘመን ዘለቅ ኾኖ እንዲሻገር ኹነኛ አጥር ነው ማለት እንችላለን፡፡

Monday 29 July 2019

ወርሰህ ክበርበት

Please read in PDF
እኔ …
ኹል ጊዜ ስሑት ፍጹም የማልረባ
ዘወትር በደጄ ኃጢአት የሚያደባ

Monday 22 July 2019

ከክርስቶስ ይልቅ “ቄሣርን” አወዳሽ “ነቢያት”! (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF
“ወንጌላውያን” ነቢያትና ቤተ መንግሥታዊ ማስታወቂያነታቸው
  “ወንጌላውያን” ነቢያትና ጥቂት የማይባሉ ኦርቶዶክሳውያን አገልጋዮችም ጭምር ቤተ መንግሥቱ በሕዝብ ዘንድ ዕውቅና ያገኝ ዘንድ ተግተው “እያገለገሉ” ይመስላል፤ ለዚህም ለምሳሌ፦ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ መወቀስ አይገባቸውም እስከሚለው ጥግ የሄዱ አገልጋዮችን አይተናል፤ እንዲያውም ቤተ ክርስቲያን ከቤተ መንግሥት ባነሰ ማንነት መኖሯን ራሳቸውን ጭምር በመስደብ ያቀረቡትን ሰምተናቸዋል። ለዚህም ለከት አልባ በኾነ መንገድ ግልጥ ፖለቲካዊ ቃላትን በመጠቀም ሲወርዱ ተመልክተናቸዋል።
ለምሳሌ፦
-       “አርበኝነት በደሙ የተዋሐደው” ኢትዮጲያዊነት፣
-       ሃያ ሰባት ዓመታት መብታችን ተጥሶ … ፣
-       የኢትዮጵያ … የጠላቶቿ ድንጋይ አቀባዮች (የማርሲሉ ዮናታን አክሊሉ)፣
-       ኢትዮጵያን እግዚአብሔር በቃል ኪዳን ጠብቆአታል፣
-       የጠቅላዩ ዙፋን የተቀባና በእግዚአብሔር ፈቃድ የተከናወነ ነው፤(ኢዩ ጩፋ) የሚሉትንና ሌሎችንም መጥቀስ ይቻላል።

Tuesday 16 July 2019

ከክርስቶስ ይልቅ “ቄሣርን” አወዳሽ “ነቢያት”! (ክፍል - 2)

Please read in PDF
ጸያፍ ድፍረት
   ራሱን ከወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት እንደ አንዱ እንደ ኾነ የሚቈጥረው፣ የ“Christ Army” ቴሌቪዥን ባለቤት ኢዩ ጩፋ፣ ስሙንና ክብሩን በሚናኝበት በገዛ ቲቪው ላይ “ለጠቅላይ ሚኒስቴሩ ጻፍኩት” ባለውና በገዛ ቲቪው ላይ “ሲደሰኩር”፣ ለኢየሱስ የሚነገሩትን ምሳሌዎች በመላ ወስዶ ለጠቅላዩ ሲናገር እንሰማዋለን፤ እንዲህ ይላል …
“ … ዕውቀትህ አስገራሚ ነው፣ ንግግርህም ይፈውሳል፤ እንደ ነቢይ ትተነብያለህ፣ እንደ መምህር አስተማሪ፣ እንደ አባት መካሪ ነህና ዕድሜ ይጨምርልህ፤ አባት ነህና እንደ አብርሃም፣ ንጉሥ ነህና እንደ ዳዊት፣ ነቢይ ነህና እንደ ሙሴ፣ ካህን ነህ እንደ ኢያሱ፣ ጠቢብ ነህ እንደ ሰሎሞን፣ ደፋር ነህ እንደ ጳውሎስ፣ ታጋሽ ነህ እንደ ኢዮብ፣ ቆራጥ ነህ እንደ ሩት፣ ባለ ራእይ ነህ እንደ ዮሴፍ … እነዚህን ኹሉ ነህና …”
  ከሰማኹት በኋላ ጆሮዬ ጭው ብሎአል፤ ደንግጬ ከመናገርም ከመስማትም ተቆጥቤ፣ ነገሩን ነፍሴ ተጸይፋውም በተደጋጋሚ “በኢየሱስ ስም እንዲህ ያለ ክፉ ነገር ከእኔ ይራቅ!” ብዬአለሁ። የመሸታ ቤት አዝማሪ እንኳ ይህን ያህል ገንዘብ ለከፈለው ወርዶ አያወድስም!!!


Saturday 13 July 2019

ከክርስቶስ ይልቅ “ቄሣርን” አወዳሽ “ነቢያት”! (ክፍል - 1)

Please read in PDF
መግቢያ
   በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መካከለኛ ዘመን ታሪክ፣ የቤተ መንግሥትን አስነዋሪ ድርጊት ፊት ለፊት ከተጋፈጡት መካከል በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን የተነሡት ደቂቀ እስጢፋኖሳውያን፣ በአጼ ፋሲል ዘመን የተነሡት መነኮሳት፣ አባ ፊልጶስና አኖሬዎስ ዘጸጋጅን ተጠቃሽ ናቸው፤ እኒህ አባቶች የነገሥታቱን አመንዝራነት፣ ፍትህ አልባነት፣ ድኃ ገፊነት፣ እጆቻቸውን በደም መታጠብ ፊት ለፊት የተጋፈጡና በሕይወታቸው ተወራርደው ዋጋ የከፈሉ ናቸው።
   እስጢፋኖሳውያን ዘርዐ ያዕቆብ እጁን ከቤተ ክህነትና ከቤተ ክርስቲያን እንዲያነሣ ደጋግመው ሞግተዋል፤ ቤተ መንግሥትና ቤተ ክህነት ጋብቻ ሊፈጽሙ አይገባም በማለት ይናገሩ የነበሩት የመጀመሪያዪቱ ቤተ ክርስቲያን አማኞችና አባቶች ሳይሳሱ ፊት ለፊት ተጋፋጭና ተሟጋችም ነበሩ፤ በቤተ ክርስቲያን በትር ዙፋናቸውን ያጸኑ አያሌ ነገሥታት ኢትዮጵያ የነበራትን ያህል፣ ነገሥታት በቤተ ክርስቲያን በትር ዙፋናቸውን ማጽናታቸውን እንዲያቆሙ የተጋደሉ አያሌ አባቶችንም[መጨረሻቸው መሥዋዕትነት ቢኾንም] ነበሩ።



Friday 12 July 2019

የዓምዳዊ ስምዖን ጸሎት

በመስቀል ላይ ሳለህ ራስህን ዘንበል(ዘለስ) ያደረግህ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ወደ አንተ ምስጋና አሳርግ ዘንድ ለሞተውና ላዳነኝ ምስጋና ይሁን እያለች ነፍሴ በአምላካዊ በገና ታመሰግን ዘንድ የነፍሴን ራስ ከፍ ከፍ አድርግ፡፡
ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በመስቀል ላይ የሞትክ፥ በሞትህም ሞት ድል የሆነ አንተ እንደ አባትህ ሕያው ስትሆን በሥጋ ሞትን የምትቀበል ሁነሃልና፡፡ ሞትንም የምታጠፋ አንተ ነህና፤ አንተስ መቼም መች አንተ ነህ፤ አንተም የሕይወት አካል ነህ፡፡