Wednesday 29 September 2021

ተሐድሶ ትርጉሙና ሕይወቱ!

 Please read in PDF

ተሐድሶ፣ “ሐደሰ” ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን፣ ትርጕሙ “አዲስ አደረገ” የሚለውን ትርጕም ታሳቢ ያደርጋል። በተገብሮ (Passive) “ተሐድሰ” ከሚለው ቃል ደግሞ፣ “ተሐድሶ” የወጣ ሲኾን፣ ትርጕሙ “አዲስ ኾነ” ማለት ነው። ስለዚህም ስያሜው ድርጊትን እንጂ ተቋማዊነትን ወይም አደረጃጀትን ፈጽሞ አያመለክትም።


Saturday 25 September 2021

“ቶ”

 Please read in PDF

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ፣ በአንገታቸው የመስቀል ምልክትን የሚያስሩ ብዙዎች፣ “ቶ” ምልክት ያለውን በአንገታቸው ማሰርን በአደባባይ እየተመለከትን ነው። “ቶ” ምልክት ያለው ብቻ ሳይኾን፣ ሌሎችም እንግዳ ድርጊቶች ሲከሰት፣ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶና በሌሎችም አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት ሲከናወን ዝም ማለት አልያም አንዳችም ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቦ፤ ነገሩ ከእንቁላል ወደ ጫጩት እስኪያድግና ብሎም እስኪጐለምስ ችላ ማለት እንግዳ ተግባርም አይደለም።


Thursday 16 September 2021

“ኑ! ወደ ኦርቶዶክስ[ዊነት] እንመለስ!” (የመጨረሻ ክፍል)

 

ካለፈው የቀጠለ …

ዛሬ ኦርቶዶክስ ማን ነው?

“ተዋሕዶ ሳይኾን ስሙ ሃይማኖቱ

ኦርቶዶክስም ሳይኾን ባህሉና ትምህርቱ

ሰርቆና ቀምቶ የሰው ስም በከንቱ

ሰው ኹሉ አለስሙ ምነው መጠራቱ”[1]


Tuesday 14 September 2021

“ኑ! ወደ ኦርቶዶክስ[ዊነት] እንመለስ!” (ክፍል ፩)

 Please read in PDF

ኦርቶዶክስ[ዊነት] ምንድር ነው?

“ኦርቶዶክስ ማለት ኦርቶ ርቱዕ፤ ዶክስ ባህል ሐሳብ፣ ኅሊና፣ ስብሐት፣ ምስጋና ይኾናል፤ በተገናኝ ርቱዐ ሃይማኖት ማለት ነው። … ኦርቶዶክሳዊ ማለት ደግሞ የኦርቶዶክሳዊ ወገን እውነተኛ ቅን፣ በሃይማኖቱ ሐሰትና ስህተት ጽነት የሌለበት።”[1]



Friday 3 September 2021

ተያይዘው የወደቁ ወንድማማቾች (2ሳሙ. 2፥16)

Please read in PDF


ሳኦል የእግዚአብሔርን መንገድ ባለመከተሉ ምክንያት፣ እግዚአብሔር ዳዊትን “በትይዩ” ንጉሥ አድርጎ ቀባው። ለእግዚአብሔር ቃል ያልታዘዘውና እግዚአብሔርን ፈጽሞ ባለመፈለግ ባዛኙ ሳኦል፣ የዳዊትን መሾም ሲያውቅ፣ ዳዊትን ለመግደል የቻለውን ኹሉ ከማድረግ አላረፈም። በሜዳ፣ በምድረ በዳ፣ በዋሻ፣ በተራራ … ባገኘው ሥፍራ ኹሉ አሳድዶ ሊገድለው እጅጉን ፈለገው። ነገር ግን ዳዊትን መግደል ሳይቻለው፣ “ፍልስጥኤማውያን የሞቱትን ለመግፈፍ በመጡ ጊዜ ሳኦልና ሦስቱ ልጆቹ በጊልቦዓ ተራራ ላይ ወድቀው አገኙአቸው። የሳኦልንም ራስ ቈርጠው የጦር ዕቃውን ገፍፈው ለጣዖታቱ መቅደስ ለሕዝቡም የምስራች ይሰጥ ዘንድ ወደ ፍልስጥኤማውያን አገር ሁሉ ሰደዱ።” በማለት እንዴት ባለ አስቀያሚ ሞት እንደ ሞተ ይነግረናል፤ (1ሳሙ. 31፥8-9)።