Sunday 28 February 2016

ወንድሜ ማን ነው? (የመጨረሻው ክፍል)

ከማይጠፋ ዘር ተወልደን ወንድማማች የሆንበት ምስጢር
     ጌታ ኢየሱስ ከባሕርይ አባቱ ከአብ የተወለደ ፍጹም ልጅ ነው፡፡ በእርሱ ልጅነት እኛ ደግሞ ልጆች ተብለናል፡፡ በዓመጽና ባለመታዘዝ ፊተኛው አዳም የእግዚአብሔር ልጅነትን ሲያጣ ሁለተኛው አዳም እግዚአብሔር ወልድ እንደልጅ ፍጹም በመታዘዝ (ዕብ.5፥8) ሁላችን ለእግዚአብሔር ልጆች እንሆን ዘንድ እርሱ በኵር ሆነ፡፡ እኛ ወደአባቱና ወደእርሱ ክብር የምንገባው የእርሱን “አማኑኤልነት” አብነት አድርገን ነው፡፡ የቀደመው አዳም ከኃጢአት የተነሳ ለሞት ወልዶን ነበርና፡፡
    ከማይጠፋ ዘር ስለመወለድ ወይም ስለዳግም ልደት ስንናገር በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መፈጠርን ወይም ፍጹም መለወጥን የሚያሳይ ነው፡፡ መፈጠር የሚለው ቃል አዲስ ማንነትን ማግኘትን ያሳያል ፤ ከዚህም የተነሣ ከእግዚአብሔር የሆነ የዘላለም ሕይወት ሠርጾ በአማኙ ልብ ውስጥ ይገባል፡፡ (ዮሐ.3፥16 ፤ 2ጴጥ.1፥4 ፤ 1ዮሐ.5፥11) አማኙም በእምነት ጌታ ኢየሱስን ተቀብሎታልና ፍጹም የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል (ዮሐ.1፥12 ፤ ሮሜ.8፥16 ፤ ገላ.3፥26) ፤ አዲስ ሰውነትን (2ቆሮ.5፥17 ፤ ቈላ.3፥9) የዘላለም ሕይወት (1ዮሐ.5፥20) ያገኛል፡፡

Tuesday 23 February 2016

ኤርትራን ምን ነካት?

  
 ምንም እንኳ ቀን ሰባራ ሆኖ ካርታና ድንበር ቢለያየንም፥ መሳ ለመሳ ሆነን ባንተያይም አንድ ወንዝ አብረን ጠጥተናል ፣ ተጋብተናል ፣ ተዋልደናል ፣ ግማሽ እናቶቻችን እዚያ ግማሽ እናቶቻቸው እዚህ ፣ ግምሽ ወንድሞቻችን እዚያ ግማሽ ወንድሞቻቸው እዚህ ፣ ግማሽ ልጆቻችን እዚያ ግማሽ ልጆቻቸው እዚህ አሉ ፤ የጋራ መልካም እሴቶች ፤ የሃይማኖት አሻራዎች አሉን ፤ ተመሳሳይ መልክና ተመሳሳይ ታሪክ ፤ ተመሳሳይ ድኅነትና ቀና የማያስብልና የሚያሳፍር አስቀያሚ የጦርነት ገጽታዎች አሉን፡፡ ኤርትራውያን ከኢትዮጲያውያን ጋር የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ብቻ ሳይሆኑ ምናልባት እንደጀርመን የልዩነት ግንቦቻቸውን አፍርሰው “ወደፊት አንድ ሊሆኑ ከሚችሉ ሕዝቦች መካከል” አንዱ ሊሆኑም ይችላሉ፡፡

Friday 19 February 2016

“እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውን አየ” (ዮና.3፥10)

   
    ታላቂቱን የአሦርን መናገሻ ከተማ ነነዌን የመሠረተው፥ በእግዚአብሔር ፊት ብርቱ አዳኝ የነበረው የኩሽ ልጅ ናምሩድ ነው፡፡ (ዘፍጥ.10፥11) የከተሞች መመሥረት የክፋትና የኃጢአት ዝንባሌዎችና ተጽዕኖዎች ሁሉ በአንድነት ለመገኘት ዋና ምክንያት ሆኗል፡፡ እዚህ ላይ መጠንቀቅ ያለብን የከተማ ችግር ሰዎች በብዛት ሆነው በአንድ ላይ በመኖራቸው ምክንያት ሳይሆን፥ በአእስራኤልና በአህዛብ ከተሞች እናይ እንደነበረው የጦርነት ምሽጎችና መሣሪያዎች፥ እንዲሁም ያለእግዚአብሔር ከመኖር ዐመጸኝነትና አለመታዘዝ ማዕከልነት ውስጥ መመንጨቱ ነው፡፡ ነቢዩ አሞጽ፥ “በአዛጦን አዳራሾችና በግብጽ ምድር አዳራሾች አውሩና ፦ በሰማርያ ተራሮች ላይ ተሰብሰቡ፥ በውስጥዋም የሆነውን ታላቁን ውካታ፥ በመካከልዋም ያለውን ግፍ ተመልከቱ በሉ፡፡ ግፍንና ቅሚያን በአዳራሾቻቸው የሚያከማቹት ቅን ነገርን ያደርጉ ዘንድ አያውቁም፥  … ” (አሞ.3፥9-10) በማለት በከተማ የሚሠራውን ነገር በግልጥ ያስቀምጣል፡፡

Sunday 14 February 2016

ቲያንስ - የማይዋደዱትንና ባላንጣዎቹን “አገልጋዮች” እንዴት አፋቀረ?

  
Please read in PDF
 መጽሐፍ ቅዱስ ጌታ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በሥጋ ከተገለጠበት ጊዜ ጀምሮ ያለውን ዘመን የመጨረሻው ዘመን በማለት ያስቀምጠዋል፡፡ ለዚህም ነው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ የጌታን መምጣት ቶሎ እንደሚሆንና የቀረበ መሆኑን ደጋግሞ የሚናገረው፡፡ (ሐዋ.2፥17 ፤ 1ጢሞ.4፥1 ፤ ዕብ.1፥1 ፤ 1ዮሐ.2፥18 ፤ ራእ.1፥1 ፤ 3 ፤ 22፥6-7 ፤ 10 ፤ 20)በዚህ የመሲሑ ዘመን በሆነው በዘመን መጨረሻ ከሚሆኑት ነገሮች አንዱ ገንዘብ የሚያመልኩና የሚያፈቅሩ ሰዎች የሚበዙ መሆናቸውን ታላቁ መጽሐፍ ይነግረናል፡፡
    የእግዚአብሔር መንፈስ፥ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ለዚህ ነው ከዘመናት በፊት ሐዋርያትን አንቅቶ መጽሐፍ ቅዱስን ሲያጽፋቸው የአገልጋይን ዋና መመዘኛ፥ “ራሱን የሚገዛ (1ጢሞ.3፥2 ፤ ቲቶ.1፥8 ፤ 2፥2 … ገንዘብን የማይወድ ፣ ተገቢ ባልሆነ መንገድ ለጥቅም የማይሮጥ(ረብ የማይወድ) [1] (1ጢሞ.3፥3 ፤ 8 ፤ ቲቶ.1፥7) በማለት የጠቀሰው፡፡ ጌታችንም ደቀ መዛሙርቱን ለአገልግሎት ባሠማራበት ወቅት የሚያስፈልጋቸውን ማንኛውም ነገር ሁሉ፥ የሚመሰክሩላቸው ሰዎች በሚያደርጉላቸው ልከኛ እርዳታ ላይ ፍጹም መደገፍ እንዳለባቸው እንጂ የራሳቸውን ነገር መያዝ እንደሌለባቸው አስጠንቅቋቸዋል፡፡ (ማቴ.10፥8-11)

Tuesday 9 February 2016

ክርስቲያን ያልሆኑት ኦርቶክሳውያን ወይስ ምህረተ አብ?! (ክፍል ሁለት)

Please read in PDF
እግዚአብሔርም መንፈስ በውኃ ላይ ሰፍፎ ነበር።” ማለት ምን ማለት ነው?
    የመጀመርያው የመጽሐፍ ቅዱስ “ነገር ግን” በዚህ ሥፍራ ተጠቅሷል፡፡ “የእግዚአብሔርም መንፈስ በውኃ ላይ ሰፍፎ ነበር።” በሚለው ቃል፥ “የእግዚአብሔርም” በሚለው ቃል ውስጥ “ም”፥ ነገር ግን ተብላ ልትጠቀስ ትችላለች፡፡ ምክንያቱም ፍጥረት ገና ሲፈጠር የነበረው ገጽታ አስፈሪና እጅግ ውስብስብ ነበር፡፡ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ መጥቶ በውኃ ላይ በረበበ ጊዜ ይህ አስፈሪ ገጽታ ተወገደ፡፡ ስለዚህም የምድርን ጥልቅ ሥፍራ ሁሉ ውጦት የነበረው ጨለማ የሥርዓት ባለቤት የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል ፍጹም በመጠባበቅ ላይ መሆኑን ገላጭ ሃሳብ እንደሆነ እናምናለን፡፡

Monday 1 February 2016

ደሙን ካንተ ይሻል!


እንሰሳት አራዊት ፤
አዋቂ ሕጻናት ፤
ምድር ተገልብጣ ፣ ልትተኮስ በʼሳት ፤
አመድ ብናኝ ልትሆን ፣ በፍህም ቀጠሮ ፤
ደስታዋ ሊሰበር ፣ በዋይታና ሮሮ …