Monday 28 November 2016

Tuesday 22 November 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል ስምንት)

ታዲያ ሃይማኖታዊ ብሔርተኝነት ምንድር ነው?
   የብሔርተኝነትን ትርጉም ይዘን ሃይማኖታዊ ብሔርተኝነትን ስንተረጉመው፥ “ለአንድ ተመሳሳይ ወይም በአንድ ውስን ሥፍራ ወይም በአንድ መልክአ ምድራዊ  ክልል ውስጥ ለሚኖሩ፥ በሃይማኖታዊ ግንኙነቶች መተሳሰር፥ በአንድ ቋንቋ መጠቀም[በሃይማኖት ጥላ መሰባበሰብ]፥ በጋራ ታሪካዊ ሂደት ውስጥ የወል ሥነ ልቦናዊ ገጽታዎችና በሃይማኖታዊ አመለካከቶች መያያዝን ያመለክታል ... ”  ብለን በአጭሩ መተርጐም ይቻለናል፡፡
    ምናልባትም ለሃይማኖታዊ “ብሔርተኝነት” ከዚህ የተሻለ ትርጉምን ልናመጣለትም አንችልም፡፡ [1] እንግዲህ የብሔርተኝነትን ትርጉም አንስተን ከሃይማኖት ጋር ለማሻረክ መሞከር፥ በራሱ ብዙ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገሮችን እንድንፎርሽ ያደርገናል፡፡ በክርስቶስ የተመሠረተው ክርስትናችን ለጠቅላላው ዓለም[ሰው] መፍትሔ እንጂ “በሃይማኖት ወገንተኝነት” ላይ በማነጣጠር ወይም እንዲህ ባለው ነገር ላይ መሠረት በመጣል ፈጽሞ አይደለም፡፡

Wednesday 16 November 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል ሰባት)

Please read in PDF
ለመሆኑ፦
ሃይማኖታዊ “ብሔርተኝነት” ምንድር ነው?
  “ ... የሃይማኖት ብሔርተኝነት መነሻው አገራችን በሰማይ፤ ኑሮዐችን በዓለመ ነፍስ ከመሆኑ ላይ ነው፡፡ የሃይማኖት ብሔርተኝነት ሲባልም ሃይማኖትን በሃይማኖት እናት፣ አባትና ብሔር አድርጐ መውሰድ ወይም በአጭሩ የሃይማኖት ወገንተኛ ማለት ነው፡፡ ከዚህም የተነሣ የሃይማኖት “ብሔርተኝነት” ወንዝ- ጐጥና ዘውግ ዘለል መሆኑን ያስፈልጋል፡፡ የሃይማኖት “ብሔርተኝነት” በቤተ ክርስቲያናችን የነበረና የቆየ ማእከለ አንድነት እንጂ አዲስ ክስተት አይደለም፡፡ [1]
   ... የሃይማኖት “ብሔርተኝነት” እያጸጸ መምጣቱንና ውስጡ ጥቅመኝነት ሆኖ ሽፋኑ ወንዛዊ- ጎጣዊ- ዘውጋዊ የሆነ ብሔርተኝነት መሠረት እየያዘ መሆኑን ነው፡፡ እናም መጪውን ጊዜ ለቤተ ክርስቲያን የተሻለና በጐ ከማድረግ አኳያ የጊዜውን አበው፣ ሊቃውንትና ምእመን በሃይማኖት “ብሔርተኝነት” ዋጅቶ ከወንዛዊ- ጐጣዊ- ዘውጋዊ ብሔርተኝነት ደዌ መፈወስ አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው፡፡
   ... ቤተ ክርስቲያን በቀጣይ ከባድ ግን ልትወጣው የምትችለው ፈተና አለባት፡፡ በቃላት የሚፈታና የሚነገር ሳይሆን በተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚፈተነው፡፡ ከዚህ አኳያ ቀጣዩ ጉዞ በሃይማኖት “ብሔርተኝነት” እጅ ለእጅ መያያዝንና  ጠንካራ አንድነትን የሚጠይቅ ነው፡፡ ለምን አልተጣሉም? ለምን አልተከፋፈሉም? የሚሉ አጽራረ ቤተ ክርስቲያን አርፈው የሚቀመጡበትም ሁኔታ እንደሌለ መገንዝብ ይቻላል፡፡ ... ብፁዓን አበውም፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንም ምእመናንም ይህን አውቀው በሃይማኖት “ብሔርተኝነት” ጠንክሮ መጓዝ ይጠበቅባቸዋለን እንላለን፡፡” [2]

Friday 11 November 2016

ዘረኛነት - ብሔርተኛነት - የዘመናችን ፈተና (ክፍል ስድስት)

አማኞች፦ ከእኛ ምን ይጠበቃል?
    “አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና”፤ (ገላ.3፥28) የሚለው ቃል ከክርስቶስ ጋር አንድነት በዘር፣ በማኅበራዊ ኑሮ ደረጃና በጾታ ልዩነት ገደብ የሌለበት መሆኑን በግልጥ ያሳያል፡፡ ክርስቶስ የመሠረታት አዲስ ኪዳናዊት ሕብረት ልዩ የሚያደርጋት ይህ ነው፤ ምንም ምን ልዩነት በሰው ልጆች መካከል ፈጽሞ አያደርግም፡፡ “በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና”፤ (ሮሜ.10፥12)፥ የሚለው ቃል ደግሞ፥ ጌታን ለማመንና በእርሱ ለመዳን ምንም የዘር ቅድመ ሁኔታ አለመቀመጡን እናያለን፤ (1ቆሮ.12፥13 ፤ ኤፌ.2፥15 ይመልከቱ)፡፡

Thursday 3 November 2016

ወዳንተ ቃል ቀዬ


የፍቅር እንጎቻ የእምነት እንጀራ፥
የቸርነት ዳቦ የምሕረት መና፥
ጨለማ ʻማይነካው የዘላለም ጸዳል፤

Tuesday 1 November 2016

“ … የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ”(ኤፌ.4፥3)

ከአንድነት ወደመንፈስ አንድነት እንመለስ!
      ቤተ ክርስቲያን የአይሁድና የሳምራውያን፤ የአሕዛብም ድምር ውጤት ናት፡፡ ይህ ፍጹም የመንፈስ አንድነት የተገኘው እንዲያው ዝም ብሎ ሳይሆን የወልደ አምላክ የክርስቶስ ኢየሱስን ሞትና የደም ዋጋ የጠየቀ፥ በእርሱም የደም ቤዛነት በተደረገ ዕርቅ የተገኘ ነው፡፡ አንድነቱ ተራ ወጥነት ያለው አንድነት ወይም ተመሳሳይነት ማለት አይደለም፡፡ አንድ የመሆን አንድነት በራሱ ከውጫዊ ተጽዕኖ የሚመጣ የጫናና የፍጹም ውጥረት ዳርቻ ነው፡፡ በአንድነት ውስጥ አንድ ያልሆኑ ልቦች ብዙ ናቸው፡፡
    የመንፈስ አንድነት ግን ከመንፈስ ፍሬዎች አንዱ የሆነና ከአንድነት የተለየ መልካም ነገር ነው፡፡ የብዙዎች አንድነት ቅድመ መርኅን መሠረት ያደረገ ነው፡፡ ስለዚህም አብረው ያሉ፣ የተስማሙ፣ የማይለያዩ፣ የማይከዳዱ፣ የማይነጣጠሉ … ይመስላሉ እንጂ፥ ፈጽመው አንድ አይደሉም፡፡ ትልልቅና የማይፈርሱ የሚመስሉ አንድነቶች እንዴት እንደፈረሱ እስኪደንቀን ድረስ ፈጽመው ስም አጠራራቸው እስኪጠፋ ፈርሰዋል፡፡