Wednesday 25 January 2017

ጌታ ኢየሱስ ለምን ተጠመቀ? (ክፍል ሦስት)

Please read in PDF
3.    ሰው ኃጢአትና ውድቀት ጋር ራሱን ይደምር ዘንድ ይህ ሃሳብ በመንፈስ ቅዱስና በቃሉ ማስተዋል ካልሆንን በቀር፥ ብዙዎች ተሰነካክለው እንደወደቁበት ልንሰነካከልና ልንወድቅበት እንችላለን፡፡ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ትስብእትነት ላይ ብዙዎች መጽሐፍ ቅዱሳዊውን እውቀት ባለመያዛቸው ምክንያት ከጥንት ዘመን ይስት እንደነበር ዛሬም ብዙዎች ሲስቱ እያየን ነው፡፡

Friday 20 January 2017

ጌታ ኢየሱስ ለምን ተጠመቀ? (ክፍል ሁለት)

Please read in PDF
2.   ገረ ሥላሴን ለማብራራትና ለዓለም ሁሉ ለመግለጥ፦ ትምህርተ ሥላሴ በመጽሐፍ ቅዱስ በምልዐት የተብራራ ትምህርት ነው፡፡ በተለይም ትምህርቱ በግልጥ የተሰበከው፤ በጉልህ የታየውና የተረዳው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሲሐዊ መገለጥ[በጥምቀቱ] ጊዜ ነው፡፡

Wednesday 18 January 2017

ጌታ ኢየሱስ ለምን ተጠመቀ? (ክፍል አንድ)

    ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመሲሕነቱን አገልግሎት በግልጥ የጀመረው በጥምቀቱ ዋዜማ ነው፤ በነቢዩ ኢሳይያስ አንደበት መሲሑ እንደተነገረው፥ “የአዋጅ ነጋሪ ቃል፦ የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ፥ ለአምላካችንም ጐዳና በበረሀ አስተካከሉ፡፡ ሸለቆው ሁሉ ከፍ ይላል፥ ተራራውና ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይላል፤ ጠማማውም ይቃናል፥ ስርጓጕጡም ሜዳ ይሆናል፤ የእግዚአብሔርም ክብር ይገለጣል፥ ሥጋ ለባሹም ሁሉ በአንድነት ያየዋል፥ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና” (ኢሳ.40፥3-5) ተብሎ የተነገረው ትንቢት በተፈጸመ ማግስት ነው፡፡

Friday 13 January 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል ሦስት)


  6. ውነተኛ ሯጭ ምትክ ሯጮችን ያዘጋጃል፦ እውነተኛ የክርስትና ሕይወት ሯጭ፥ ልክ እንደእርሱ እውነተኛውን ሩጫ የሚሮጡ ምትክ ሯጮችን ማዘጋጀት አለበት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ አለ፥ “መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፥ ይህንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል፥ ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለም፤” (2ጢሞ.4፥7-8)፡፡
    ቅዱስ ጳውሎስ የሮጠበትን የፊተኛውን ዘመን እውነተኛ ሩጫ በትክክል ካስታወሰ በኋላ፥ እርሱ ሮጦ በድል እንዳጠቃለለ እንዲሁ፥ ሌሎቹም እንዲነሣሱና እንዲሮጡ ይጋብዛል፤ ደግሞ የጋበዘ ብቻ አይደለም፤ እንደጢሞቴዎስና ቲቶ ያሉትን እውነተኛ ሯጮችን ተክቶ ሩጫውን ፈጽሟል፡፡ በዚህ ዘመን ከሚታዩ አስከፊ የደቀ መዝሙርነት ገጽታ አንዱ እውነተኛ የሩጫውን ተካፋዮች ለክርስቶስ ከማብዛት ይልቅ ሰዎችን በራስ ዙርያ ወደማከማቸት የሚሮጠው ሩጫ መብዛቱ ነው፡፡

Wednesday 11 January 2017

እረኞች ዘመሩ

Please read in PDF
ጠቢባን ፍጻሜ ጥበባቸው
ሊቃውንት የመደምደሚያ ቃላቸው
የነቢያት ትንቢት ዖሜጋ
የመዳን ጥንተ መሠረት አልፋ

Thursday 5 January 2017

“ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት … ተወልዶላችኋልና”(ሉቃ.2፥11)

   Please read in PDf
የዳዊት ከተማ ቤተ ልሔም ናት፤ የስሟ ትርጓሜም “የእንጀራ ቤት” ማለት ነው፡፡ በያዕቆብ ዘመን “ኤፍራታ” ተብላ ትጠራ ነበር፤ ቤተ ልሔም የብዙ ባለታሪክ ቅዱሳን አባቶች አገር ናት፤ የኢብጻን፣ የቦዔዝ፣ የእሴይና የዳዊት ከተማ ናት፤ (መሳ.12፥8 ፤ ሩት.2፥4 ፤ 1ሳሙ.17፥12)፡፡ ዳዊት ንጉሥ ስለመሆኑ በሳሙኤል እጅ በቤተ ልሔም ተቀባ፤ (1ሳሙ.16፥13)፡፡ በነቢዩ በሚክያስ አንደበትም፥ “አንቺም ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ከአንቺ ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል፤”(ሚክ.5፥2) ተብሎ እንደተነገረው በዚህችው በዳዊት ከተማ ቤተ ልሔም ክርስቶስ ኢየሱስ ተወለደ፤ (ሉቃ.2፥4)፡፡

Monday 2 January 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ“አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል ሁለት)

2.  ጫውን በአገባቡ ወይም ዓይኑን ከመሙ[ከመሮጫው መስመር] ሳይነቅል መሮጥ፦ የሯጭ የዘወትር ተግባር ነው፤ ከመስመሩ ዓይኑን ፈጽሞ መንቀል የለበትም፡፡ ከመሙ ወጥቶ ሮጦ ቢያሸንፍ እንኳ አሸናፊነቱ ይሰረዛል፡፡ የዕብራውያን ጸሐፊ ይህንን ወደክርስትና ሕይወት ሩጫ በመቀየር፥ “የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤”(ዕብ.12፥2) በማለት ገልጦታል፡፡
   በሩጫው ዓይናችንን ፈጽሞ ከጌታ ልናነሳና ምድራዊ ነገሮች ላይ [እጅግ ጠቃሚ ቢሆኑም እንኳ] ልናደርግ አይገባንም፡፡[1]  ክርስቶስን በትክክል እያየን ሩጫችንን ልንሮጥ ይገባናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ክርስቶስን ልክ በፊታችን እንደተሳለ እንዳናየው የሚያደርግ አዚም ሊኖር ይችላል፤ ልክ የገላትያ ክርስቲያኖች፥ “የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?” (ገላ.3፥1) እንደተባሉ፥ እኛም የአዕምሮ ችግር ሳይኖርብን ክርስቶስን መረዳት ሲሳነን፥ ለእርሱ ሥራ ቸለተኞች ስንሆንና ሩጫችንን እርሱን ፊት ለፊት ባለማየት ስንመላለስ ወዳለማስተዋል አዚም ውስጥ ልንገባ እንችላለን፡፡