Thursday 30 May 2019

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል አራት)

  2.  ክርስቶስ ኢየሱስን ሕይወት አይታለች፦ ጌታችን ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ የእርሱን ሕይወት ከእርሱ ጋር ውለው፤ አድረው እንዲያዩ ደግሞም አብረውት እንዲኖሩ ፈቅዶአል፤ (ዮሐ. 1፥40)። ከዚህም ባሻገር ጌታችን ኢየሱስ ራሱ ሌሊቱን ሙሉ ሲጸልይ ካደረ በኋላ ደቀ መዛሙርቱን ሲመርጥ “ከእርሱም ጋር እንዲኖሩና ለመስበክ እንዲልካቸው፥” ወዶ እንደ ኾነ ቅዱሳት መጻሕፍት በግልጥ ይመሰክራሉ፤ (ማር. 3፥13-14)።
   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኀጥአንን ተቀባይ መኾኑን ቅዱሳት መጻሕፍት ደጋግመው ገልጠዋል፤ ግብዞችንና አስመሳዮችን፣ የሕይወት ቲያትረኞችን እጅግ ይጠየፍ የነበረው ጌታ ኀጥአንን ግን በአደባባይ ሳይታዘባቸው ተቀብሏል፤ አብሮአቸው ተመግቦአል፤ ሳይጠየፋቸው በአንድነት ከእነርሱ ጋር አሳልፎአል። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከኀጢአተኞች ጋር ማሳለፉ ለብዙዎች አይሁድ የማይዋጥላቸው ተግባር ነበር፤ ምክንያቱም በግልጥ እንደ ሕጉ መለየትና መወገዝ እንጂ ተቀባይነትን ማግኘት አለባቸው ብለው ያምኑ አልነበረምና።

Friday 24 May 2019

ብንያያዝማ

Please read in PDF

አብዝተን ሳንሮጥ ሳንደክም ገና
በጥቂቱ ትጋት በብዙ ስንፍና …

Monday 20 May 2019

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል ሦስት)

 Please read in PDF

3. ማርያም መግደላዊት፦ የክርስቶስ ከሙታን ትንሣኤ መካከል በእውነት መነሣት የክርስትና ዋና ማዕከል ነው፤ በመስቀል ላይ ቤዛ ኾኖ መሰቀሉ በእውነት ለኃጢአተኞች መኾኑና የቤዛነት ክፍያውም መረጋገጡን የሚያበስረው ከሙታን መካከል መነሣቱ ነው፤ “እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ” ክርስቶስ ከሙታን መካከል ተነሥቶአል፤ (ሮሜ 6፥4፤ 7፥6፤ ሐዋ. 2፥24፤ 2ቆሮ. 5፥17፤ ኤፌ. 4፥22፤ ቈላ. 3፥10)። ጌታ ኢየሱስ ከሙታን መካከል ባይነሣልን፣ “ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት፤ እስከ አሁን ድረስ በኃጢአታችሁ አላችሁ” (1ቆሮ. 15፥17) እንደ ተባለ፣ ከኃጢአታችን ሳንላቀቅ እስከ አኹን እንደ ተጣባን፣ የሙጥኝ ብለን እየኖርን አለን ማለት ነው። ክብር ይኹንለትና እርሱ ግን የኀጢአት ዋጋችንን በሥጋው መከራ በመስቀል ላይ ደሙን አፍስሶ ከፍሎልን፣ ዋጋችንም የጸደቀና የተረጋገጠ መኾኑን በትንሣኤው አጽንቶልናል።



Tuesday 14 May 2019

መሐንዲሱ ኢየሱስ

Please read in PDF

የተዝረከረከ ቀበዝባዛ ሕይወት
ሥርዐት አልባ ኑሮ መውጣትና መግባት
የተንቀዠቀዠ ያልተደላደለ

Wednesday 1 May 2019

“መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል” (ዮሐ. 10፥11)

Please read in PDF
   ወንጌላዊው ዮሐንስ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እረኝነት እጅግ አድምቆ ከሚያሳዩ ትምህርቶች አንዱንና ሰፊውን ጠቅሶ ጽፎልናል፡፡ ምዕራፉ ስለ እረኝነት ብዙ ነገር የምንማርበት ቢኾንም፣ አንዱን ዘለላ ብቻ መዝዘን ለመማማር ወደድን፤ እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ የማኖሩን ወይም አሳልፎ የመስጠቱንና ስለ በጎቹ ማናቸውንም ዋጋ ከፍሎ የሚያድን ስለ መኾኑ የተነገረውን አንድ አንቀጽ፡፡
    በምድረ እስራኤል እረኝነት የተወደደ ተግባር ነው፤ በተለይም የበግ እረኝነት፡፡ በብሉይ ኪዳንም ኾነ በአዲስ ኪዳን ብዙ ጊዜ ከእረኝነት ጋር በተያያዘ በጎች ሲጠቀሱ፣ መልካም እረኞችም ለበጎቻቸው ባላቸው እንክብካቤና ጠባቂነት፣ ታዳጊነትም ሲመሰገኑ እናያለን፤ ልክ እንዲሁ ደግሞ ምንደኛና ሙያተኛ እረኞችም ለሚጠብቋቸው እረኞች ባላቸው ተላላነትና ዝንጉነት፣ እንዲሁም ጥቅመኛ ብቻ ስለ መኾናቸው እየተነሳ ሲወቀሱና ሲዘለፉ፣ ፍርድንም ሲቀበሉ እንመለከታለን፡፡