Saturday 27 April 2019

የኢየሱስ የቀብር ሥነ ሥርዓት (ዮሐ. 19፥38-42)

Please read in PDF
 ኢየሱስን በዚያ አኖሩት (ዮሐ. 19፥42)
   ወንጌላዊው ዮሐንስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ኹሉን አዋቂና ተቈጣጣሪ አድርጐ ያቀርበዋል፤ (ዮሐ. 2፥25፤ ኢየሱስ እንደሚሞት ያውቃል (ዮሐ. 12፥23፤ 13፥1)፣ እንዴት እንደሚሞት ያውቃል ( 12፥33)፣ መች እንደሚሞት ያውቃል (ዮሐ. 17፥1)፣ መከራውን ኹሉ ብቻውን መቀበል እንደሚፈልግ ፈቃዱን ገልጦአል (18፥4)፣ ጊዜው ሳይደርስ እንዳይሞትም ያውቃል (11፥54)፤ ኢየሱስ ሥጋን የለበሰ ደካማ መሲሕ ኾኖ ቢገለጥም ነገር ግን ኹሉን አዋቂና ተቈጣጣሪ ጌታ ነው። በእርግጥም የሞተው በአጋጣሚ አይደለም፣ እያወቀና ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ ስለሚወደንና ስለሚያፈቅረን ነው።


Monday 22 April 2019

እጅግ ረክሷልና!!!

Please read in PDF
ዓመት ሙሉ ታስሮ ባመቱ መፈታት
ወራት ሙሉ ወድቆ አንድ ቀን መነሳት
ለጊዜው መቆጠብ ለወራት መፈንጨት
በፋሲካ ሰሞን አማኝ አማኝ መሽተት

Wednesday 17 April 2019

በሮተር ዳሙ ካቴድራል - ጣዖት አምልኮ?

Please read in PDF

   ሕዝቅኤል እስራኤልን ሲመለከታት በኀጢአት የተጨማለቀች አመንዝራ ሴትን ትመስላለች፤ ታማኝነቷን ያጐደለች ፍቅረኛ ናት፣ ከሕፃንነት ጀምሮ ቢከታተላትም፣ ከተጣለችበት ቢያነሣትም፣ “በተወለድሽ ጊዜ በዚያው ቀን እትብትሽ አልተቈረጠም ንጹሕም ትሆኚ ዘንድ በውኃ አልታጠብሽም፥ በጨውም አልተቀባሽም በጨርቅም አልተጠቀለልሽም። በተወለድሽበት ቀን ከሰውነትሽ ጕስቍልና የተነሣ በሜዳ ላይ ተጣልሽ እንጂ ከዚህ አንዳች ይደረግልሽ ዘንድ ዓይን አልራራልሽም፥ ማንም አላዘነልሽም።” (ሕዝ. 16፥4-5) ከተጣለችበት አንሥቶ በብዙ ምሕረቱ ቢታደጋትም እርሷ ግን “ … አንቺም አደግሽ ታላቅም ሆንሽ፥ በእጅጉም አጌጥሽ፤ ጡቶችሽም አጐጠጐጡ ጠጕርሽም አደገ፥ ነገር ግን ዕርቃንሽን ሆንሽ፥ ተራቍተሽም ነበርሽ።” እንዲል ፈጽማ አመንዝራ መንገድን ተከተለች።

Monday 15 April 2019

ኒቆዲሞስ - ከዳግም መወለድ ይልቅ ኢየሱስ ይልቃል!

 Please read in PDF
 የሳምንቱ ስያሜ ኒቆዲሞስ ነው። የሚነበበው የወንጌል ንባብ ደግሞ ዮሐ. 3፥1-21 ነው። ክፍሉ በኢየሱስና በየአይሁድ መምህር በኾነው በኒቆዲሞስ ንግግር የደመቀ ኾኖ፣ የክፍሉ ዋና መልእክቱ ግን የኒቆዲሞስ መምህር መኾን ወይም የዳግም መወለድ ጉዳይ ብቻ አይደለም። እውነት ነው! በክፍሉ  የኒቆዲሞሰ ታሪክ ተመዝግቧል፤ የዳግም ልደት ትምህርትና ጥልቅ ማብራሪያም አለ፤ ዋናው የወንጌሉ መልእክት ግን ይህ አይደለም።

Friday 12 April 2019

ራሴን ያየሁበት ምስል

Please read in PDF
  

ይህን ምስል ስመለከት ኹለት የተቃረኑ ሃሳቦች ወደ ውስጤ መጡ፤ አንደኛው የካቶሊኩ ፖፕ ስለምን እንዲህ ራሳቸውን አዋረዱ? ምን ይኾን ልቡናቸውን የነካው? ከአራት መቶ ሺህ በላይ በጦርነት የተፈጁትና ያለቁት የኑብያ ልጆች [ሱዳናውያን]  አንጀታቸውን አድብነው፣ ጉበታቸውን አፍርሰው፣ በመሪር እንባ በፊታቸው ድቅን ብለውባቸው ይኾንን? የዓለም መገናኛ ብዙሃን እንኳን ሊዘግበው ሊመለከተው ያልወደደውን የኑብያን ልጆች [የሱዳናውያንን] ሰቆቃ በአካል ሄደው ተመልክተውት ራሳቸውን ስተው ይኾንን? እንዲህ በማድረጋቸውስ “የሱዳኑ መሪ” ልቡ ይሰበር ይኾንን? የመቶ ሺህዎቹ የኑብያ ልጆች ኅሊናውን አልገደለው፣ ልቡን አላደነደነው ይኾንን? የፖፕ ፍራንሲስ “ውርደት” የራሱ “ውርደት” እንደ ኾነው ይሰማው ይኾንን?! በመላ ዘመኑ የኑብያዋ የሱዳን መሪ የእኒህን ፖፕ ድርጊት መዘንጋት ይቻለው ይኾን? ስል ...

Sunday 7 April 2019

በጎና ክፉ ባሪያ (ሉቃ. 19፥11-27)

Please read in PDF

   የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ዋቢ ያደረገው ዓቢይ ጾም፣ የጾሙ ሳምንታት በየራሳቸው ስያሜ አላቸው፤ ስያሜዎቹን የሰየመው “የዜማ ደራሲው” ያሬድ ሲኾን፣ የጌታ ኢየሱስን ሕይወቱንና ትምህርቱን ከወንጌላት በመውሰድ የሰየማቸው ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኢ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የኾኑ ብዙ ትምህርቶች ያሉትን ያህል፣ ከጅማሬአቸው መልካም የነበሩና አኹንም ድረስ በመልካም ምሳሌነት የተያዙን አንጥሮ፣ በመጽሐፉ ቃል መዝኖ መቀበል ደግሞ ለእኛ ለአማንያን የተተወ ነው። ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተገኘውን ኹሉ እንድንቀበል ሳይኾን በመጽሐፍ መዝነን እንድንቀበል ቃሉም መንፈሱም ይመክሩናልና።
   የዚህኛው ሳምንት ስያሜ ገብር ኄር ይባላል፤ ትርጉሙም መልካም ወይም ትጉህ ባርያ ማለት ነው፤ ይህ ስያሜ ደግሞ የተወሰደው ከማቴ. 25፥14-30 ወይም ከሉቃ. 19፥12-27 ካለው የወንጌል ክፍል ነው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ክፍል የተናገረው ለሞቱ ወደ ኢየሩሳሌም እየወጣ በነበረበት ወራት ነው፤ በተናቁትና በተገፉት፣ በኢየሩሳሌማውያን ፈጽመው በማይወደዱት ገሊላውያንና መንደሮቿ መካከል የቆየውና የነበረው ጌታችን ኢየሱስ፣ አሁን ለሞቱ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቷል። በገሊላ የነበሩት እጅግ የተናቁ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ኃጢአተኞችና በኢኮኖሚም ደረጃ እጅግ ዝቅ ያሉ፣ ከፍተኛ የሥነ ልቡና ጫናም የነበረባቸው ሰዎች ጭምር፤ ኢየሩሳሌም ደግሞ በሕጉ የሚመኩና የሚመጻደቁ፣ አግላይና ናቂ፣ ትእቢተኞችና ራሳቸው ብቻ የመሲሑ ተቆርቋሪ እንደ ነበሩ አድርገው የሚያስቡ ፈሪሳውያንና ሰዱቃውን የበዙባት ከተማ ነበረች።