Monday 16 May 2022

ይድረስ ለየዋሁ ኦርቶዶክሳዊ ወገኔ በሙሉ!

 Please read in PDF

ያ ትሁት ልብ የነበረውና ጽድቅ ፍለጋ ወደ ኢየሩሳሌም የተጓዘው ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ፣ 'የምታነበው ይገባሃልን?' ተብሎ በወንጌላዊው ፊልጶስ ለቀረበለት ጥያቄ የሰጠው መልስ እጅግ ልቤን ይነካኛል። 'የሚያስረዳኝ ሳይኖር እንዴት ይገባኛል?' እኛ ከዚህ እውነተኛና ትሁት ሰው ደም ምንድነው የወረስነው? ከራሳችን ሰዎች እንዳንማር ተረግመን ይኾንን? ''በታሪካችን ውስጥ አንዳንድ ፋና ወጊ ወገኖቻችን ሃገርን የሚጠቅም እውነት ይዘው ብቅ ሲሉ ማጥፋቱን ተክነንበታል። (ምሳሌ፦ እነ ደቂቀ እስጢፋኖስን)። ለዚህ ነው በሥልጣኔ በር ላይ ቀድመን ደርሰን በመገተራችን፣ ሌሎች ከኋላ እየመጡ ቀድመውን የገቡት'' በማለት ፕሮፌሰር መስፍን በሕግ አምላክ ደቂቀ እስጢፋኖስ በሚለው የፕ/ር ጌታቸው መጽሐፍ ላይ የተናገሩት። 

Thursday 5 May 2022

መንትዮቹ፤ መስቀሉና ትንሣኤው!

 Please read in PDF

በሰሙነ ሕማማቱና በትንሣኤው ወቅት የነበረውን እውነት ካሰላሰለ በኋላ፣ ጴጥሮስ ክርስቶሎጎስ የተባለ አንድ አባት እንዲህ ብሎአል፤ “ሴቶቹ የክርስቶስን ትንሣኤ ለማክበር ቀዳሚዎች ናቸው፤ ደቀመዛሙርቱ ደግሞ ስለ ክርስቶስ መከራን ለመቀበል የመጀመሪያዎች ኾኑ። ሴቶቹ ሥጋውን ሽቱ ለመቀባት አዘጋጁ፤ ደቀ መዛሙርቱ ደግሞ ለቅጣት መሣሪያዎች ሰውነታቸው አዘጋጁ። ሴቶቹ ወደ መቃብር ገቡ፤ ደቀ መዛሙርቱም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ወደ እስር ቤት ሊገቡ ነው። ሴቶቹ ምስክርነታቸውን ለመግለጽ የተፋጠኑ ኾነዋል፤ ደቀ መዛሙርቱም ስለ እርሱ የሰንሰለት እስራትን ለመቀበል የማይፈሩ ኾነዋል።” ብሎአል።