Tuesday 31 March 2020

ቀጥ ያለ ኦርቶዶክስ!

መብራቴ እንደ በራ ጨዌ እንደ ሰማ
ውስጤ እንደ ፈለገ የክብርህን ግርማ
አጊኝቼ ልራብህ አይቼ ልናፍቅህ

Monday 30 March 2020

የገነነ ምሕረት!

በምድራችን ላይ እጅግ አያሌ ተላላፊ በሽታዎች ተነስተዋል፤ እስካሁን ግን ከ1918 እስከ 1919 ዓመተ እግዚእ፣ የዓለማችንን 50 ሚሊየን ሕዝብ ቅርጥፍ አድርጎ የበላ፤ እንደ ቅጠልም  ያረገፈ፤ በH1N1 Virus መነሻነት የተነሳውና “Spanish flu” በመባል እንደሚታወቀው መረርሽኝ ያህል የተነሣ የለም፡፡ በጊዜው የዓለማችን አንድ ሦስተኛው የሚያህለው ማለትም፣ 500 ሚሊየን ሕዝብ ገደማ በቫይረሱ ተጠቅቶ ነበር፤ ከዚህ ቁጥር ውስጥ ደግሞ 50 ሚሊየን ገደማ ሕዝብ ሞቶ ነበር፤ የዚያኔ በአሜሪካ ብቻ 675 ሺህ ሕዝብ ያህል አልቆባት ነበር፡፡

Saturday 28 March 2020

ስለ ኮሮና የእግዚአብሔር ልብ ምን ይላል?!


 
   እግዚአብሔር ይህችን ምድር በእሳት ትኩሳት ሊያሳልፋት ቀጠሮ የያዘላት እንጂ ዘላለማዊና ቋሚ፣ ደስታዋም የማይከስም ኾና የተሠራች አይደለችም፤ ምድርና ሥጋ በእርጅና ይያዛሉ፤ ያረጃሉ፣ ይጃጃሉ፣ ይገረጅፋሉ፣ እንደ ብራናም ተጠቅልለው ያልፋሉ፤ እንደ አበባ ይረግፋሉ፣ እንደ ቅጠል ይጠወልጋሉ፣ እንደ ሣር ደርቀው ይጠፋሉ (1ጴጥ. 124) የእግዚአብሔር ቃል ግን አይሻርም፤ ደግሞም ለዘላለም ጸንቶ ኗሪ ነው፤ (1ጴጥ. 125 ዮሐ. 1035) ከቅዱስ ቃሉ የሚመዘዙት ፍርዱ ደግሞ እውነትና ቅንነት የከበባቸው፣ እጅግም ጣፋጭ ናቸው፤ (መዝ. 199-10)



Friday 27 March 2020

በቫይረሱ ብንያዝስ?



በኮሮና ቫይረስ ከተያዙ ወይም ተይዣለው ብለው ከጠርጠሩ ምን ማድረግ ይችላሉ ?
ሳል፣ ትኩሳት፣ ትንፋሽ ማጠር እና ተያያዝ ምልክቶች በራስዎ ላይ ከተመለከቱና በኮቪድ-19 እንደተጠቃ ከሚጠረጥሩት ወይም ከተረጋገጠ ሰው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ከነበርዎት ወይም በኮቪድ19 ወደተጠቁ አገራት/አካባቢዎች ተጉዘው ከነበረ ምን ማድረግ አለብዎት?

Wednesday 25 March 2020

ለሚበልጠው ብልጥግና ትጉ!

Please read in PDF
   ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “ለጤናማ ብልጥግና ትጉ፣ ለጤናማ ብልጥግና መትጋት ይገባናል” የሚሉ አባባሎች፣ በመካከላችን አሰምተው ሲነገሩ እየሰማን ነው። አባባሉ ጤናማ ቢመስልም፣ በውስጡ ግን ስውር መደላድል የለውም ማለት፣ እጅግ ተላላነት ሊኾን ይችላል። “የብልጥግና ወንጌል” መምህራንና ደቀ መዛሙርት ዋና ቅኝታቸው፣ መጽሐፍ ቅዱስን በመታከክ ለብ ያሉ መልእክቶች ማቅረብና ማስተላለፍ እንደ ኾነ መዘንጋት አይገባንምና።  ለብ ያለ ነገር ደግሞ ለፍጥረታዊው ሰው እጅግ ከመለድለዱም ባሻገር፣ ቀላልና ሰፊ ኹሉም ለመጓዝ የሚያመቸው መንገድ ነው።

Monday 23 March 2020

ስለ ተላላፊ በሽታ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

Please read in PDF
መግቢያ
   ጌታችን ኢየሱስ መድኀኒት አስፈላጊነቱ ለበሽተኞች መኾኑን ተናገረ (ማቴ. 9፥12)፤ ስለዚህም ሰዎች ከበሽታ ለመዳን መድኀኒትን መጠቀማቸውን እናስተውላለን፤ “በጥንት ዘመን ሰዎች በመድኃኒት ሲያምኑ በነፍስ ሊበረቱ ይችላሉ። ጥቅሙ ከእምነት እንጂ ከመድኃኒት አልነበረም። ዛሬ ግን ብዙ ጊዜ በመድኃኒት ቢያምኑም ባያምኑም መድኃኒቱ ፍቱን ነውና ይሠራል”። ከፊት ዘመን ይልቅ በዛሬ ዘመን ሰዎች በመድኃኒት አብዝተው የሚታመኑ ይመስላል፤ ለዚህም ይመስላል በምድራችን ላይ እጅግ ዝቅተኛ ከሚባሉት እስከ ቅንጡ መታከሚያ ቤቶች የተበራከቱት። ነገር ግን ይህ ኹሌ ስሙርና የመጨረሻ መፍትሔ ኾኖ አይታይም።

Saturday 21 March 2020

ደብረ ዘይት - ይመጣል ኢየሱስ

Please read in PDF

ርኩሰት እንዳየለ ሞት እንደ በረታ
ዓመጽ ገደብ አልፎ ኹሉን እንደ ረታ
የደዌ ነጋሪት የሕመም ጉሰማ

Wednesday 18 March 2020

ተጽናኑ፤ አጽናኑም!

Please read in PDF

   አዲስ ኪዳን በአጭር ቃል፣ ከሥጋ ሕመምና ሞት፤ ከበሽታም ይልቅ ከእግዚአብሔር አባትነት መለየትና መነጠልን የዘላለም ሞትና ፍርድ እንደሚያስከትል ያስተምራል። የሥጋ ሕመምና ሞት በአዲስ ኪዳን ትምህርት፣ ጊዜያዊና ሰው የመኾናችን ውጤት መኾኑን ብቻ የሚያመለክትም ነው። ከዚህ ባሻገር ሰዎች ባለመታዘዝ በጸኑ ልክ፣ ለኀጢአት፣ ለዓመጻና ለማይረባ አእምሮ ተላልፈው ሊሰጡ ይችላሉ።


Sunday 15 March 2020

ልበ መጻጉዕ!

Please read in PDF

   የዓቢይ ጾም አራተኛው ሳምንት ስያሜው መጻጉዕ ነው፤ ትርጉሙ በ ቁሙ ጐባጣ ማለት ነው። የስያሜው ታሪክ በቀጥታ የተያያዘው በዮሐንስ ወንጌል ምዕ. 5 ላይ ያለውን ታማሚ ሰውን ማዕከል ያደረገ ነው። ታማሚው ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያህል ሕመምተኛ የነበረ ሰው ነው። ሕመሙ ምን እንደ ኾነ አልተጠቀሰም፤ ነገር ግን ጽኑ ሕመም መኾኑ አይካድም። በኢየሩሳሌም፣ በበጐች በር አጠገብ፣ አምስት ባለ መጠለያ መመላለሻዎች የነበሯት፣ በአራማይክ ቋንቋ ቤተ ሳይዳ ወይም ቤተዛታ ተብላ በምትጠራው የመጠመቂያ ስፍራ፣ ይህ መጻጉዕ ሰው ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያህል ፈውስን ሲጠብቅ ኖሮአል።


Thursday 12 March 2020

Monday 9 March 2020

ምኩራብ - ሦስተኛው ቤተ መቅደስ

Please read in PDF

  ያለንበት የዓቢይ ጾም ሳምንት በማኅሌታይ ያሬድ ስያሜ፣ “ምኩራብ” ተብሎአል፤ ምኩራብ አይሁድ በምርኮ ወደ ባቢሎን በተወሰዱ ወራት፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ለማንበብና የሕጉን ቃሎች ለማሰብ፣ በየጥቂት አባወራ በመሰባሰብ የጀመሩት ነው። ወደ አገራቸው ሲመለሱም ይኸንኑ በመቀጠል፣ ከዋናውና መሥዋዕት ከሚቀርብበት መቅደስ ባሻገር፣ በየመንደራቸው አቅራቢያ ምኩራብ በመሥራት፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማጥናትና ማንበብን በዚያ ጀመሩ። እንግዲህ ማኅሌታይ ያሬድ፣ ምኩራብን ለዓቢይ ጾም ሦስተኛው ሳምንት ሲሰይም፣ በሳምንቱ ውስጥ ከሚነበቡት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ደግሞ፣ ዮሐ. 2፥12-22ን በመመደብ ነው። ክፍሉም በቀጥታ በኢየሩሳሌም ከነበረው ቤተ መቅደስ ጋር በማያያዝ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረው ስለ መኾኑ የታመነ ነው።

Sunday 8 March 2020

በእኔ የተናገርክ … ተባረክ!

Please read in PDF

አገልግሎትን በክብር መጨረስ መታደል ነው። ያለ መንፈስ ቅዱስ ዕርዳታም፣ ማንም አገልግሎቱን በክብር መጨረስ አይቻለውም። ሩጫውን ስለ ጨረሱ ቅዱሳን ስናስብ፣ ልባችን ታላቅ ሐሴት ያደርጋል፤ በመደነቅም ይሞላል፤ ኹላችን እንዲህ ብንኾን፣ በሕይወት ዘመናችን እንደ እነርሱ ባለ ትጋት ጸንተን፣ እርግጠኞች ኾነን፣ “መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤” ማለት ብንችል እንዴት በታደልን?! … አዎን! ለዚህ ተጠርተናል!!!

Wednesday 4 March 2020

በማንቂያ ደወል አንቅተንስ … ?!

Please read in PDF

  ባለንበት ወር “የማንቂያ ደወል” የሚሉ ጉባኤያት፣ በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በተደጋጋሚ ከአድባራት እስከ ደብራት ሲደረጉ እያየን ነው። ከተለያዩ ጉባኤያት “መምህራን” አንደበት እንደ ሰማነው፣ የጉባኤያቱ መነሻ ዐሳብ፣ ሕዝቡን ስለ ሃይማኖቱ ማንቃት፣ በተለይ አኹን እየደረሰ ካለው ውጫዊና ውስጣዊ ተጽዕኖ በመከላከል፣ ሃይማኖቱን እንዲጠብቅና ከፍ ሲልም “ሰማዕት” እንዲኾን ማድረግ የሚሉና ሌሎችም ጽኑ አቋሞች አሉት። ነገር ግን ለጉባኤያቱ መደረግ እንደ ሥረ ምክንያት የተነሡትና እንደ ጭብጥ የተያዙት ዐሳቦች፣ ከክርስትና አስተምህሮ እጅግ የራቁና መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ ያላቸው አይመስሉም

Monday 2 March 2020

ቅድስት - ኢየሱስ ከሰንበት ይበልጣል!

Please read in PDF

  “ሰንበት” የሚለው ቃል፣ በዕብራይስጥ ትርጉሙ ማቆም ወይም መተው ማለት ነው።[1] “ሰንበት … የዕለት ስም ሰባት፣ ሰባተኛ ቀን፤ ሰባተኛ ዓመት ማረፊያ ዕረፍት…”[2] ማለት ነው። በቀደመው ኪዳን ትእዛዝ መሠረት፣ “ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፤ አንተ፥ ወንድ ልጅህም፥ ሴት ልጅህም፥ ሎሌህም፥ ገረድህም፥ ከብትህም፥ በደጆችህም ውስጥ ያለ እንግዳ በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ፤ …” (ዘጸ. 20፥10) እንዲል፣ ማናቸውም የኪዳኑ አማኝ፣ የዘወትር ሥራውን ትቶ ወይም በማረፍ በኹለንተናዊ መልኩ እግዚአብሔር አምላኩን በአምልኮ ለማክበር የሚጠቀምበት ቀን ነው፤ የሰንበት ቀን ለዕረፍትነት ወይም ለአምልኮ መሰጠቱ ከሕጉ በፊት መኾኑን አለመዘንጋት፣ ለኹሉ የሰው ዘር መሰጠቱን እንድናስተውል ያደርገናል