Wednesday 13 July 2022

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፲፰)

Please read in PDF

ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን የወንጌላውያን ትምህርት

ከምዕራባውያን መካከል ከካቶሊካውያን በ16ኛው ምዕተ ዓመት የተለዩት ወንጌላውያን፣ የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣንና ትውፊት በተመለከተ “Sola Scriptua - መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ” የሚል ጽኑ አቋምን ይዘዋል። መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ፣ “እንከን አልባ ለሰው ልጅ ብቸኛው መዳኛና የሕይወታችን መመሪያና የኹሉ ነገር ዳኛ” የሚል አቋምን በውስጡ የያዘና፣ ይህንም ብርቱ ሥልጣን ከመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት ያገኘ መኾኑን ሲናገሩ፣

Saturday 9 July 2022

“ራስህን ለካህን አሳይ”፣ ብሉያዊ ወይስ አዲሳዊ?

Please read in PDF

“ኀጢአትን ለካህን ለመናዘዝ ይገባል” ለማለት የሚከራከሩ ሰዎች፣ ከሚጠቅሷቸው ጥቅሶች መካከል ይህ ቀዳሚው ነው። ክፍሉ በቀጥታ እንዲህ ተብሎ በጌታችን ኢየሱስ ተነግሮአል፤ “… ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ፥ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ሙሴ ያዘዘውን መባ አቅርብ” ጌታችን ኢየሱስ ይህን የተናገረው፣ ከለምጽ ለነጻው ለምጻም ሰው ነው፤ (ማቴ. 8፥4፤ ማር. 1፥44፤ ሉቃ. 5፥14)። ጌታችን ይህን ለምጻም እንዲህ ብሎ ለምን እንዳዘዘው ከመናገር፣ አስቀድሞ አንድ ሰው ለምጽ ሲወጣበት ስለሚደረገው ብሉያዊ ሥርዓት በአግባቡ መረዳት ነገሩን ለማስተዋል እጅግ ይቀላል።

Friday 8 July 2022

መድሎተ ስሑት ወይስ “መድሎተ ጽድቅ”?! (ክፍል ፲፯)

 Please read in PDF

ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን የምሥራቃውያን ትምህርት

የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት የመጽሐፍ ቅዱስን ሥልጣን፣ ከትውፊት ነጥለው ብቻውን በማቆም ሥልጣኑን ይቀበላሉ። ከትውፊት የመነጠላቸውም ምክንያት፣ መጽሐፍ ቅዱስ የትውፊት የበላይና የቤተ ክርስቲያን መመሪያ፣ የኹሉ ነገር መመዘኛ፣ ልዩና የማይገረሰስ ሥልጣንም እንዳለው አምነው ይቀበላሉ።



ከካቶሊክና ከላቲን አብያተ ክርስቲያናት በተለየ መንገድ፣  የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት መጽሐፍ ቅዱስን ከቤተ ክርስቲያን ትውፊት መነጠላቸውና “ብቻውን በቂና አስተማማኝ” ማለታቸው የሚደንቅ ነው።

Saturday 2 July 2022

በአሜሪካ ለ50 ዓመታት የቆየው የውርጃ ሕግ መሻሩ!

 Please read in PDF

እግዚአብሔር በማናቸውም መንገድ የሰው ልጅ እንዲገደል አይፈልግም። ከታላላቆቹ ሕጎች መካከል አንዱ፣ “አትግደል” የሚለው ሕግ ነው። የሰው ልጆች ደግሞ በተቃራኒው፣ የሰውን ልጅ ለተለያዩ የገቢ ምንጭነትና የዓመጽ ሥራ በብርቱ ጭካኔ ከሚገድሉበት መንገድ አንዱና ዋነኛው፣ ውርጃ ከፊቶቹ ተርታ ይመደባል። ውርጃ በግልጽ በመጽሐፍ ቅዱስ ቢከለከልም፣ ተፈጥሮን የሚቃረን ቢኾንም እጅግ በሚዘገንን መልኩ አያሌ የውርጃ ተግባራት እንዲተገበሩ ብዙ ብሮች ይፈሱበታል፤ ሰዎች ተግባሩን እንዲፈጽሙ በሕግ ጭምር ከለላ ይደረግላቸዋል። ይህን በማድረግ ከሚታወቁት መካከል ግንባር ቀደሟ አሜሪካ አንዷ ናት። እናም ለ50 ዓመታት በሕግ ከለላ ሰጥታ ትፈጽም የነበረውን የውርጃ ሕግ፣ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች ሽረውታል።