Saturday 29 April 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል ስምንት)

3.  ታደር  ከሰይጣንና ከክፋት ኃይላት ጋር የምናደርገው ትግል ወታደር በጦርነት ሥፍራ ከሚያደርገው መጋደል ጋር ተመሳስሏል፡፡ እንዲያውም የተነገረን፣ “በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ” (ኤፌ.6፥10) በሚል ትእዛዛዊ ቃል ነው፡፡ መጋደላችንም ደምን እስከማፍሰስ ድረስ መቃወም ሊኖርበት ይችላል፤ (ዕብ.12፥4)፤ እንደበጎ ወታደርም የክርስቶስ ኢየሱስን መከራ መካፈል እንደሚገባም ጭምር፤ (2ጢሞ.2፥3)፡፡
    የብዙዎቻችን የክርስትና ሕይወት ሲታይ በክርስቶስ ለክርስቶስ መኖርን አያመልክትም፡፡ በሌላ ንግግር ትኩረታችን ጌታ ኢየሱስ ብቻ አይደለም፡፡ ከእርሱ[ከጌታ ኢየሱስ] የሚያንሱ ነገሮችንም ከእርሱ ጋር አስተካክለን ይዘን መጓዝ እንፈልጋለን፡፡ እንደሯጭ የሩጫውን ሥርዐት ወይም መማችንን[መስመራችንን] ብቻ፤ እንደባርያ ደግሞ ለገዛን ጌታ ፈቃድ ብቻ መኖርን አልተለማመድንም፤ አላሳደግነውምም፡፡ መንገዳችንን ለማቅናትና ትኩረታችንን ሁሉ በጸጋውና በ“ጸጋው ተቀባዮች” ላይ ከማድረግ ይልቅ፣ በእርሱ ላይ ብቻ እንድናደርግ፤ የወታደርን ጠባያት ከመጽሐፍ ቅዱስ አውጣጥተን እንማማርበታለን፤ ጌታ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይርዳን፤ አሜን፡፡
       ወታደር፦

Sunday 23 April 2017

ቶማስ - ከደቀ መዛሙርቱ የመጨረሻ አማኝ

 Please read in PDF

   አይሁድ በይሁዳ ምድር በቢታንያ መንደር ለግድያና ለወገራ ጌታ ኢየሱስን ይፈልጉ በነበረበት ወቅት፣ አልዓዛር በጠና መታመሙን ሰማ፡፡ ወዳጁ አልዓዛርን ስለእግዚአብሔር ክብር ሊያስነሣው ደቀ መዛሙርቱን “ወደይሁዳ ደግሞ እንሂድ” አላቸው፤ (ዮሐ.11፥8) ይህንን ሲል ሁሉም ፈርተው ነበር፤ ቶማስ ግን “ለባልንጀሮቹ ለደቀ መዛሙርት፦ ከእርሱ ጋር እንሞት ዘንድ እኛ ደግሞ እንሂድ” በማለት ደፋርና የማይፈራ ሰው መሆኑን አስመሰከረ፡፡
   በቤተ ክርስቲያን ቀኖና የዛሬው እሁድ ዳግማይ ትንሣኤ ወይም ዳግም ትንሣኤ ተብሎ ይጠራል፡፡ ከስምንት ቀን በፊት ለደቀ መዛሙርቱ በዝግ ቤት ውስጥ ሳሉ ተገለጠላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ልክ ጌታ ኢየሱስ ከሙታን መካከል እንደተነሣ አንድ ክስ በአይሁድ ሽማግሌዎች ቀርቦባቸዋል፡፡ “… ደቀ መዛሙርቱ በሌሊት መጥተው ሰረቁት” (ማቴ.28፥11) የሚል፡፡ ስለዚህ ከዚህ ክስ የተነሣ በጥብቅ ይፈለጉ እንደነበር መገመት አያዳግትም፡፡ እናም ይህን ክስና “አይሁድን ስለ ፈሩ ደጆቹን ዘግተው” (ዮሐ.20፥19) ተቀምጠው ነበር፡፡

Tuesday 18 April 2017

‘የሱስን ልበሱ

PLease read in PDF


ድሪት አትደርቱ፣ መጣፍያ አትለጥፉ፤
በአዲሱ ልብስ ላይ፣ ያረጀውን አትስፉ፤
አሮጌ አሮጌ ነው፣ መቦጨቁ ላይቀር፤

Friday 14 April 2017

ዳኞቹ

Please read in PDF    

    እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነው፤ (መዝ.7፥11)፡፡ በፍርዱም ጻድቅና የማይሳሳት፤ በቅንም ፈራጅ(ኤር.11፥20) ነው፡፡ ልብንና ኵላሊትን የሚመረምር አምላክ ነው፤ የሰውን ውስጣዊ ማንነት የሚፈትንና በፊቱም አንዳች የተሰወረ ነገር የሌለ አምላክ ነው፡፡ ደግሞም “ለሰው ሁሉ እንደ መንገዱ፥ እንደ ሥራው ፍሬ የሚሰጥ” አምላክ ነው፤ (ኤር.17፥10 ፤ ራእ.2፥23)፡፡ እግዚአብሔር የልብንና የውስጣችንን ነገር ሁሉ ስለሚያውቅና ስለሚመረምር በፊቱ የተሰወረ አንዳች ነገር የለም፡፡ ስለዚህም ጻድቅ በእግዚአብሔር ጽድቅ በእምነት ይመካል፤ እንጂ አልበደልኩም እያለ አይሞግትም፡፡
    ዳኝነት እውነትን በማጽደቅ፤ ሐሰትን በመጸየፍ የተከበበ ሥራ ነው፡፡ ስለዚህም ፈራጅ ከምንም በላይ በመልካምነቱ በተመሰከረለት “ትልቅ” ሥነ ምግባር የታነጸ ሊሆን ይገዋል፡፡ ጌታ እግዚአብሔር ለዚህ ነው፣ የእስራኤል ዳኞችን የሥነ ምግባር መመዘኛን ለቅዱስ ነቢይ ሙሴ፣ “አምላክህ እግዚአብሔር በሚሰጥህ በአገርህ ደጅ ሁሉ በየነገዶችህ ፈራጆችንና አለቆችን ሹም፤ ለሕዝቡም ቅን ፍርድ ይፍረዱ፡፡ ፍርድን አታጣምም፤ ፊት አይተህም አታድላ፤ ጉቦ የጥበበኞችን ዓይን ያሳውራልና፥ የጻድቃንንም ቃል ያጣምማልና ጉቦ አትቀበል፡፡ በሕይወት ትኖር ዘንድ፥ አምላክህ እግዚአብሔርም የሚሰጥህን ምድር ትወርስ ዘንድ እውነተኛውን ፍርድ ተከተል፤” (ዘዳግ.16፥18-20) በማለት የተናገረው፡፡

Wednesday 12 April 2017

ሰሙነ ሕማማት - “ … ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና” (1ቆሮ.11፥26)

 የጌታ ጾም መታሰቢያ የመጨረሻው ሳምንት ስያሜ ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ በዚህ ሳምንት ከምን ጊዜውም በላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአይሁድ “ወገኖቹ” የደረሰበት ጸዋተወ መከራ ከወንጌላት፣ ከግብረ ሕማማትና ከሌሎችም መጻሕፍት እየተውጣጡ ይነበባሉ፤ ሕማማቱንም ማዕከል ያደረጉ ሥርዓተ አምልኮዎች በጸሎት፣ በዝማሬ፣ በንባብና በቅዳሴ ይቀርባሉ፡፡
   ቅዱስ ጳውሎስ የጌታን ሕማም የጌታ እራት በቀረበበት ጊዜ መናገርና መመስከር እንዳለብን “ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፥ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና፤” (1ቆሮ.11፥26) በማለት ይናገራል፡፡ ጌታ ኢየሱስም ከሙታን መካከል ከተነሣ በኋላ ደቀ መዛሙርቱን፣ “እርሱም፦ ከእናንተ ጋር ሳለሁ በሙሴ ሕግና በነቢያት በመዝሙራትም ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው አላቸው፡፡ በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤ እንዲህም አላቸው፦ ክርስቶስ መከራ ይቀበላል በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል፥” (ሉቃ.24፥46) አላቸው፡፡

Saturday 8 April 2017

“Wanti kun ija kee duraa dhokatee jira” (Luqa.19:12)

Please read in pdf   

 Torbeen kun Moggaafama “Hosaa’inaa” jedhu qaba. Moggaasa kana Qulqulluun Yaareed torbeewwan sooma Kristoos hunda moggaaseen kan moggaafamee dha. Yaareed torbeewwan sooma guddaa kana keessa jiran hunda baruumsa Kristoos wajiin walsimsiidhaan moggaasa kenneefi jira. Kanaanis Kristoos bu’ura waan hundaa ta’u isaa agarsiisee jira.
    Hosaa’inaan seenaa mataa isaa danda’e qaba. Nuti garuu seenaa balla’a keessa kutaa seensaa qofa ilaala. Goftaan Yasuus “gaara Ejersaa” irraa bu’e gara magaalaa Yerusaalemitti gale. Gaara ejersaa irra taa’e magaala Yeruusaaleem gutumaan guututti arguu ni danda’a ture. Haata’uti gaara irraa bu’e gara magaalatitti seene. Lubootni, barsiisootni fi hoggantootni Ayihuud gara hammenyaan akka isa morman osoo beeku(Maar.15:12); dabalataaniis yeroo dhiyoo keessatti magaalatti fi ummata irratti naasuu fi badiin guddaan akka irratti qaqqabuu beekuu gara magaalaatti seene.

Sunday 2 April 2017

ኒቆዲሞስ - ለሕጉ እውነት የሚሟገት ጻድቅ! (ዮሐ.7፥51)

Please read in PDF

“ሕጋችን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን?”
    ነቢያት ለሕጉ ቀናተኞችና ሕጉ እንዲተገበር የሚተጉ ከእግዚአብሔር ለሕዝቡ የተላኩ ናቸው፡፡ ከእግዚአብሔር የተነገራቸውንና በተለያየ መንገድ የተቀበሉትን (ዕብ.1፥1)፤ በማናቸውም ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ሆነው የሚታዘዙትን (ኤር.1፥7) የትንቢት ቃል ሸክም ከእግዚአብሔር በተላኩ ጊዜ (ኤር.1፥4 ፤ ሉቃ.3፥2) ሳይሸራርፉ፤ ሳይቀንሱና ሳይጨምሩ እንዲናገሩ ይገደዳሉ፡፡ በዋናነት ነቢያት ራሳውና ሕዝቡ እንደሕጉ እንዲኖሩ ትልቅ ሥራን ይሠራሉ፡፡ ደጋግመውም የሕጉን መጽሐፍ ያውጃሉ፡፡ ከዚህ የበለጠ ትልቅና ዋና ሥራም የላቸውም፡፡

  ከዚህም ባሻገር፣ ጌታ እግዚአብሔርም ሕግ ሲላላ ሕዝብ ወደተላላነት እንደሚያደላ አስቀድሞ ስለሚያውቅ መሪዎችና አስተዳዳሪዎችን እንደወደደው ይሾማል፡፡ የአይሁድ መምህራንም የተጠሩበት ዋና ዓላማም ይህ ነበር፤ የሕዝቡ መሪና የሕግ መምህራን እንደመሆናቸው መጠን ሕጉን በመጠበቅ ለሕዝቡ ትልቅ ምሳሌ በመሆን፣ ሕዝቡን ያስተምራሉ፤ እንዲጠብቁም ያደርጋሉ፡፡ ዳሩ፣ በአንድ ወቅት በሕዝቡ መሪዎችና በሕጉ መምህራን መካከል ጌታ ኢየሱስን በተመለከተ ትልቅ ክርክር ሆነ፡፡ ለሕዝቡ ጥቂቱን እንጀራና ዓሳ ለብዙ ሺሆች በመመገቡ ምክንያት፣ ከመከበርና ከመደነቅ ይልቅ ለመገደል በቂ ምክንያት ሆነ፡፡