Wednesday 20 September 2023

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፪)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

2.4. እውነትን በመኖር ለማደግ

እውነተኛ ዕውቀት አእምሮን ጤናማ ያደርጋል። እውነተኛ ዕውቀትና ጤናማ ትምህርት የሌላቸው ሕይወታቸውና ልምዳቸውም ጤናማ ሊኾን አይችልም። በክርስትና ትምህርት ስናውቅ እናምናለን፤ ስናምነው ደግሞ የምናውቀው ብዙ አለን። የእምነት ዕድገት የሕይወት፣ የአምልኮና የመንፈሳዊ ዕድገት ለውጥ ነው።

ቅዱስ ጳውሎስ፣ “የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።” (ኤፌ. 1፥17) በማለት፣ እግዚአብሔርን በማወቅ እንዲያድጉ የጥበብና የመገለጥ መንፈስ እንዲሰጣቸው ልመና ያቀርባል። ይህም ዕውቀት ከራሱ ከእግዚአብሔር እንጂ ከሌላ ከማንም ሊመጣ እንደማይችልም ጭምር ይናገራል።

Saturday 16 September 2023

ጥንቆላና ሃይማኖተኝነት!

 Please read in PDF

ከሰሞኑ የስልጤ አከባቢ ጉዳይ አስደምሞኛል። አንድ ቤተ እምነት “በጥንቍልናና መተት፤ በድግምት አማኞቼን ወይም ተከታዮቼን አጥቅተውብኛል” በሚል አስባብ፣ በኦርቶዶክሳውያንና በወንጌላውያን አማኞች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን በምስልም፣ በድምጽም፣ በምስለ ወድምጽም ተመልክቻለሁ።

Monday 11 September 2023

“ንስሐ ግቡ” (ማቴ. 3፥2)

 

መጥምቁ ዮሐንስንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ከሚያመሳስላቸው የስብከት ርዕሶች ቀዳሚው፣ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” የሚለው መንግሥተ ሰማያዊ አዋጅ ነው። ቅዱስ ማቴዎስ ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ሲናገር፣ “በዚያም ወራት … በይሁዳ ምድረ በዳ እየሰበከ መጣ። የስብከቱም ማዕከል የእግዚአብሔር መንግሥትና ንስሐ ነበር። “ንስሐ” ድርጊታዊ ትርጒሙን ስንመለከት፣ “መመለስ” ማለት ነው። ይህም ከክፉ ድርጊቶች ኹሉ መመለስ፣ ክፉ ድርጊትን ኹሉ መተው፣ ከክፉ መንገድ ኹሉ ዘወር ማለትና ወደ ክርስቶስ መመለስ የሚል ትርጒምን የያዘ ነው።