Saturday 28 February 2015

የጠፉትን ለምን ነው የማንፈልገው?


           


    በኦሮምኛ አንድ የማስታውሰው ተረት አለ ፤ እንዲህ የሚል፦ “Loon bade loon jiruuf barbaadan”  ትርጉም “የጠፋ ከብት ላለው ከብት ሲባል ይፈለጋል” ፡፡ የተረቱ ጽንሰ ሐሳብ የጠፋውን ከብት የማይፈልግና ፈልጎም የማያገኝ ሰው በበረት ያለውንም ከብት ይነዱበታል ለማለት ነው፡፡ በእርግጥም የቤት እንሰሳን አጥብቆ አለመፈለግ በደህና በበረት ለሚኖረውም ምንም ዋስትና አንዳች ደኅንንት አይኖረውም፡፡

Tuesday 24 February 2015

ቅዱስ ሰንበት



ሰንበት ማለት ዕረፍት
ዕረፍት ማለት ሰንበት
ከሆነ ትርጓሜው       

Friday 20 February 2015

ይድረስ ለአይ ኤስ አይ ኤስና መሰል ባልንጀሮቻችሁ!




                                        
                                            Please read in PDF


   ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ በአንድ የቲያትር ድርሰታቸው ላይ እንዲህ ማለታቸው ይታወሰኛል፦ (በትክክል ካላልኩት ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡)
“አንቺ ወንጌል አጋዳይ
             እኔን ይዘሽ ወደሰማይ ወደሰማይ”
ብላቴን በቲያትር ድርሰታቸው ውስጥ “ወንጌል የምትባል ሚስት አግብተው የደረሰባቸውንና ያገኛቸውን መከራ በቅኔ” ሲያወጉ ይታያል፡፡ ወንጌል ከሥጋ ከደም ጋር ያይደለ፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊው ሥፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነውና የምትጋደለው (ኤፌ.6፥12) የክፋት ሠራዊት አጋንንት የሁል ጊዜ ጠላቶቿ ናቸው፡፡ ወንጌል ከአጋንንት ጋር ዘወትር ተጋዳይ ናት ማለት ነው፡፡

Saturday 14 February 2015

ለአዋጁ ጾም አዋጅ ይታወጅ!

                               
                       Please read in PDF

    ከፊታችን ሳምንት ጀምሮ ላሉት ተከታታይ ሳምንታት “ሁሉም ምዕመን የሚጾመውና” በቤተ ክርስቲያናችን ታላላቅ ከሚባሉ የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ የሆነው ጾም ፤ ጾመ ሁዳዴ ወይም ዓቢይ ጾም ወይም የጌታ ጾም የሚባለው ነው፡፡ ጌታ ጾምን በጾመበት ወራት ዲያብሎስ በስስት ፣ በትዕቢትና ገንዘብን በመውደድ ኃጢአት በግልጥ ፈትኖታል፡፡(ማቴ.4፥1-11) ንጹሐ ባህርይ መድኃኒት ክርስቶስ ደግሞ ዲያብሎስን ድል አድርጎታል፡፡ “ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነም ነውና ከዚህ የተነሳ በድካማችን ሊራራልን የሚችል ሊቀ ካህናት ሆኖልናል።” (ዕብ.4፥15)

Friday 6 February 2015

ጌታ የማያውቃቸው “የጌታ አገልጋዮች”


                                 Please Read in PDF

     ምስክርነት አንዱ የአምልኮ መገለጫ ነው፡፡ አንድ አማኝ “ክርስቶስ እርሱ ኢየሱስ ነው ወይም ክርስቶስ እርሱ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነው” (ማቴ.16፥16 ፤ ሐዋ.9፥20 ፤22)ብሎ ወደቤተ ክርስቲያን አካል ሲጨመር አንዱ የየዕለት ዋና ተግባሩ ምስክርነት ነው፡፡ ያመንነውን በመናገር ብቻ የምንመሰክር አይደለንም ፤ በሕይወትና በምግባር(በሥራ) እንጂ፡፡ “በጸጋ ድነናል”(ኤፌ.2፥5) ካልን ልክ እንደመዳናችን ማመናችንም ከእኛ የሆነ አይደለም፡፡ ጸጋው በእምነት ካዳነን “ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ” ከእኛ ሥራ የተነሳ አይደለም፡፡(ኤፌ.2፥8)
  እኛን ለማዳን አብ ልጁን ወደምድር ሲልክ ፤ እኛ ምንም የተገባን አልነበርንም፡፡ ስለዚህ “በእንዲሁ ፍቅር”(ዮሐ.3፥16) ወዶን በልጁ ሞት አዳነን፡፡ የልጁን ማዳንም እንድንቀበልም በልባችን የእምነትን አቅም ያኖረው እርሱ ነው፡፡ ነጻ ምርጫችንን ጠብቆ ፥ አምነን ወደእርሱ በመጣን ጊዜ ግን እንድናምነው ጉልበት የሆነን ያዳነን ያው ጌታ ነው፡፡ እንዲሁ “መልካሙን ሥራ ለማድረግም በክርስቶስ ኢየሱስ በሆነልን አዲስ ፍጥረት መወለድ(መፈጠር) ያስፈልገናል፡፡ (ኤፌ.2፥10)

Sunday 1 February 2015

ከነቢዩ የተሻሉት አህዛብና ግዕዛን


                                 PLease read in PDF

     ትንቢተ ዮናስን ስናጠና የእግዚአብሔር አስተማሪነትና ታጋሽነትን በእውነት ልብ የሚነካ ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚንቀው አንዳች ሥነ ፍጥረት እንደሌለ ስናይ ደግሞ የዮናስን መጽሐፍ ይበልጥ ደጋግመን ባለመሰልቸት በትኩረት እንድናየው ያደርገናል፡፡ ምንም እንኳ አህዛብ ቢሆኑም እግዚአብሔር የታላቂቱን ከተማ የነነዌን ክፋት ወደፊቱ መውጣቱ ባየ ጊዜ ከፍርድና ከቁጣ ይልቅ ይመለሱ እንደሁ በማለት የንስሐ ዕድል ሊሰጥ ነቢዩ ዮናስን ወደነነዌ “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ።” አለው፡፡(ዮና.1፥2)
   እግዚአብሔር ሳያስተምር ፣ ሳይመክር ፣ ሳይዘክር ፣ ሳይገስጽ ፣ ሳያስጠነቅቅ … ለፍርድ አይቸኩልም፡፡ እግዚአብሔር የኃጢአታችን ብዛት አያስጨንቀውም ፤ የትኛውም የኃጢአት ብዛት ትንሹን የእርሱን ምህረት እንደማይበልጥ ያውቀዋልና፡፡ ስለዚህ ነነዌን በፍርድ ከማስተማር በፍቅር ሊያስተምር ታላቁን ነቢይ ላከላት፡፡ ሥልጣን ከኃይል እንዲበልጥ በፍቅር ማስተማርም በፍርድና በተግሳጽ ከማስተማር እጅጉን ይበልጣል፡፡ ጌታ እግዚአብሔር ነነዌን ማስተማር የፈለገው በምህረትና በፍቅር ነው ፤ ዮናስ ግን እግዚአብሔር ከተማይቱን በፍርድና በቁጣ እንዲያስተምር እንጂ በፍቅር ከማስተማርና “ንስሐ ግቡ” ከሚለው ጀምር መባሉን አልወደደውም፡፡ ስለዚህም ከእግዚአብሔር ፊት መሸሽን እንደመፍትሔ በመቁጠር የዚያን ጊዜ የአለም ዳርቻ ናት ተብላ ወደምትታመነው ከነነዌ ማዶ ሊሄድ ተነሳ፡፡ ዳዊት “ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ? ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ? … ”(መዝ.138፥7) ያለውን ዘንግቶት ነበር፡፡