Tuesday 24 October 2023

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፬)

 Please read in PDF

ካለፈው ቀጠለ …

3.4. ከሰውም ኾነ ከሌላው ፍጥረት ጋር ያለንን ግንኙነት የተሻለ ያደርገዋል

ሰው ከእግዚአብሔር ጋር በኤደን ገነት በቅድስና ይመላለስ ሳለ፣ ግንኙነቱ ፍጹምና እንከን አልባ ነበር፤ (ዘፍ. 2፥8፡ 15፡ 25)። ነገር ግን ሰው በኀጢአት በወደቀ ጊዜ፣ ኀጢአት የሰውንና የእግዚአብሔርን ግንኙነት አበላሸ። ከዚህም የተነሣ ሰው፣ ወደ ወደቀውና ወደ ተሰበረው ዓለም መጣ፤ እግዚአብሔር ግን ለዘላለም ጸንቶ በሚኖረውና በማይለወጠው የቅድስናና የፍቅር ባሕርይው ጸንቶ አለ፤ (ዘጸ. 3፥14፤ ሚል. 3፥6፤ ኢሳ. 48፥12)።

Friday 6 October 2023

በአጭሩ፣ ኢሬቻ የዋቄፈታ አማኞች አምልኮአዊ በአል ነው!

Please read in PDF

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ የሮማ ቄሳራውያን ያህል፣ ለባህላዊ ሃይማኖት መስፋፋት ታላቅ አስተዋጽዖ ያደረገ አካልን መጥቀስ አይቻልም። በተለይም እኒህ ነገሥታት ክርስቲያኖችን ለማጥፋት ከተጠቀሙበት መንገድ አንዱ፣ ራሳቸውን እንዲመለኩ በማቅረብና ጣዖታትን እንዲመለኩ አዋጆችን በማውጣት ነው፤ የሚቃወሙአቸውን ኹሉ ደግሞ ያለ አንዳች ርኅራኄ በመፍጀት ተካካይ የላቸውም።[1] የኢየሱስን ጌትነት አውጀው፣ የቄሳራውያንን አል ጌትነት መቃወምና ጣዖታትን ፍጹም መጠየፋቸው ለክርስቲያን ወገኖች ብርቱ የስደትና የሰማዕትነት ዋና ምክንያት ነበር።[2] በተለይም በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ የቤተ ክርስቲያን የስደት ዘመን ወይም ዘመነ ሰማዕታት በመባል የተጠራበት አንዱ ምክንያት፣ የክርስቲያኖች ቄሳራዊ አምልኮን፣ ሮማዊና ሌሎችንም ባህላዊ ሃይማኖቶችን መጠየፋቸውና አለመቀበላቸው ነበር።[3]

Wednesday 4 October 2023

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፫)

 Please read in PDF

ካለፈው ቀጠለ …

3.3. የፍጥረት ዐላማን መረዳት

እግዚአብሔር፣ በማይቀየረውና ሊለወጥ በማይችለው (ሐ.ሥ. 2፥23)፣ በዘላለም ዕቅዱ (ኤፌ. 3፥10-11)፣ ፍጥረትን የፈጠረው ለራሱ ክብርና ዓላማ ነው። ለራሱ ዓላማ ስለ ፈጠረውም፣ ፍጥረት ክብሩን ያውጃል፤ (ኢሳ. 43፥6-7)። ለዚህም ነው፣ መጽሐፍ ቅዱስ፣ የእግዚአብሔርን ኅልውና ሲያስረዳ፣ “በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።” በማለት ስለ እግዚአብሔር ማብራሪያ ባለመስጠት፣ የፍጥረትን መፈጠር አስደናቂ ተግባር በመተረክ የሚጀምረው። ፍጥረትም የተፈጠረበትን ዓላማ ስለሚያውቅ፣ እግዚአብሔርን ገልጦ ያሳያል፤ ለፈቃዱም በግልጥ ይታዘዛል።