Wednesday 30 September 2020

እሬቻ አምልኮ አይደለምን?!

 please read in PDF

መግቢያ

   ስለ እሬቻ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከምንሰማቸው ልዝብ አሳቦች አንዱ፣ “የኦሮሞ ባህልን የምናንጸባርቀበት ብቻ እንጂ አንዳችም አምልኮአዊ መልክ የለውም” የሚለው ግንባር ቀደሙን ስፍራ ይይዛል። ይህን ለማለት ያስደፈረው እውነታ ደግሞ በክርስትና ጥላ የተጠለሉ አያሌ ኦርቶዶክሳውያንና የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት “አማኞች” እና ስለ እሬቻ ዘብ የቆሙ ሰዎች የሚያቀርቡት የተለሳለሰ ዐሳብ ነው። እሬቻን የሚያከብሩት ኦርቶዶክሳውያንና የወንጌላውን አብያተ ክርስቲያናት አማኞች፣ አምልኮአዊ መልክ እንዳለው ስለ ገባቸው ወይም ስለ ተጠራጠሩ፤ በሌላ መልኩ ደግሞ “ባህላችንን እንወዳለን” የሚል አባባይ ምክንያት በመጥቀስ ለማስረዳት ሲንገታገቱ አስተውያለሁ።



Saturday 26 September 2020

መስቀሉን የማያውቅ መስቀል

 Please read in PDF

መግቢያ

  በአገራችን በኢትዮጲያ ከሚከበሩት ሃይማኖታዊ በዓላት መካከል አንዱ ከደመራ ጋር ተያይዞ የሚከበረው በዓል  ነው፤ በዓሉ፣ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት እንጨቱ መስቀል፣ ለዓመታት ከተቀበረበት ቦታ መውጣቱን በማሰብ የሚከበር በዓል ነው። በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይኾን፣ ይህ የመስቀል በዓል በአያሌ የአገራችን ሕዝብ ባህሎች ውስጥ የተለያየ መልክና ቅርጽ ይዞ ሲከበር እንመለከታለን። ሃይማኖታዊው ትውፊት መስቀሉ ከተቀበረበት መውጣቱን በማሰብ ሲያከብር፣ አያሌ ባህሎች ደግሞ ከዘመን መለወጫ ጋር በማያያዝ በዓሉን ያከብሩታል።

Wednesday 23 September 2020

የአሸናፊ ገብረ ማርያም(ቀሲስ) “ጐስአ ልብየ ቃለ ሰናየ” ማርያም ናትን?

 Please read in PDF

መግቢያ

  አሸናፊ ገብረ ማርያም(ቀሲስ) ጥቂት የማይባሉ መዝሙሮችን “ሠርቶ”፣ ከሰንበት ትምህርት ቤት ጀምሮ ተጠቅመንባቸዋል፤ ታንጸንባቸዋል፤ አምልከንባቸዋል። ለጌታ የሚሠራቸው መዝሙሮች እጅግ መሳጭና ትኵረትን ቀንብበው የሚይዙና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያላቸው ናቸው። በዚህ ረገድ ከማከብራቸውና ከምወዳቸው ዘማሪዎች መካከል አንዱ ነው።

Saturday 19 September 2020

የልጁን መልክ መምሰል (ክፍል ፪)

Please read in PDF

እንዲህ ነበርን!

    አዳም “የመታዘዝን ፍሬ” ባለመብላት እንዲታዘዝ ቢነገረውም፣ እርሱ ግን የሰይጣንን ድምጽ ተከትሎ በመሄድና የተከለከለውን ወስዶ ከበላበት ቀን ጀምሮ ክርስቶስ እስኪመጣ ድረስ እርሱና ልጆቹ ሁሉ፣ እግዚአብሔር የተወን እየመሰለን አብዝተን ኃጢአትን ሠራን፤ ጨመርንም። ከዚህም የተነሣ፦

Thursday 10 September 2020

Tuesday 8 September 2020

ያለ ኢየሱስ ስርየት የለም!

 Please read in PDF

  ጳጉሜ 3 ብዙዎች ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የሚላተሙበትን ድርጊት የሚፈጽሙበት ቀን ነው፤ በሌላ ቋንቋ፣ “የእግዚአብሔርን ልጅ የረገጠ ያንንም የተቀደሰበትን የኪዳኑን ደም እንደ ርኵስ ነገር የቆጠረ የጸጋውንም መንፈስ ያክፋፋ፥ እንዴት ይልቅ የሚብስ ቅጣት የሚገባው ይመስላችኋል?” (ዕብ. 10፥29) የሚለውን ቃል በግልጥ የሚቃወሙበት ቀን ነው፤ “በመልአኩ ሩፋኤል” ስም መጠበል ወይም መጠመቅ ከኀጢአት ያነጻል የሚል ከንቱ ልፍለፋ።

Thursday 3 September 2020