Friday 12 April 2024

በብልጽግና ወንጌል የተለከፈ …

 Please read in PDF

በእግዚአብሔር ጸጋ ፍጹም አምናለሁ፤ ዳሩ ግን በ”ብልጽግና” ወንጌል አንዴ የተለከፉትን፤ እነርሱን በንስሐ ማደስ እጅግ ከባድ ነው፡፡ ምክንያቱም ትምህርቱ፣ የቀደሙትን ሰዎች አዳምና ሔዋንን እንዳሳተው አሳች፣ አንተን ከእግዚአብሔር ጋር የሚያስተካክል አጋንንታዊ ትምህርት ነውና፡፡ ለዚህ ነው ዶክተር ተካልኝ “የጸሎት-ንግድ ቤት” በሚለው መጽሐፉ እንዲህ በማለት የሚጠይቀውና የሚመልሰው፣

“… በእግዚአብሔር ማመንን ወደ “እንደ እግዚአብሔር ማመን” ቀይሮ ክርስትና የሚባል እምነት ይኖራልን? ፈጽሞ፤ … የትምህርቱ ኹሉ ነገር እምነት በሚባል አስገዳጅ ኃይል እግዚአብሔርን ጨምሮ ነገሮችን ኹሉ ለሰው ጥቅም ማስገዛት እና ማስገበር ነው፡፡” (ገጽ 60) ይላል፡፡



Monday 8 April 2024

Monday 1 April 2024

እባክህን ማረን !

 Please read in PDF

አገር ትድኻለች በረሃብ እንፉቅቅ

ትውልድ ይራኮታል በዋይታና በጭንቅ

Friday 29 March 2024

“በእግዚአብሔር ቤት መኖር” (መዝ. 27፥4)

 Please read in PDF

ንጉሥ ዳዊት የገዛ ቤተሰቡ ማለትም አቤሴሎም ልጁ ሳይቀር፣ ከሥልጣን ሊያወርዱት በክፋት አሲረውበታል፤ ፍጹም ካሴሩበት ሰዎች እግዚአብሔር እንዴት ባለ ታላቅ ትድግና እንደሚያድነው በመተማመን ያቀረበው የጸሎት ክፍል ነው። ጸሎቱ የኪዳኑን አምላክ በማሰብና በመታመን (2ሳሙ. 7) የቀረበ ሲኾን፣ በጌታ ላይ ያለውን ጽኑ እምነትም በይፋ የሚመሰክርና የሚያውጅ ጸሎት ነው። ጠላቶቹ የቱንም ያህል ጠንካራና ብርቱዎች ቢኾኑም፣ ለመዝሙረኛው ግን እግዚአብሔር ብርሃንና የኹሉ ነገር ምንጭ፤ ሰላምና መታመኛው ነው።

Tuesday 26 March 2024

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፲)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

  1. ስሞቹ አጠራርና አጠቃቀም ረገድ የሚያመጣው ተፋልሶ የለም።

የሥላሴን ትምህርት በትክክል የማይረዱ ሰዎች ከሚሠሯቸው ስህተቶች መካከል አንዱ፣ በስሞቻቸው አቀማመጥ መሠረት የሥልጣን ተዋረድና የማቀዳደም ሥራ መሥራታቸው ነው። በማቴዎስ ወንጌል አጠቃቀም ውስጥ፣ “አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ” ብሎ (ማቴ. 28፥19) መጥራት የተለመደና በብዙዎች ዘንድ “ተቀባይነት” ያለው አጠራር ነው።

Sunday 24 March 2024

ምኩራብ

 Please read in PDF

አይሁድ በምርኮ ዘመን መሥዋዕት የሚያቀርቡበት መቅደስ ስለ ፈረሰባቸውና፣ ወደ አገራቸውም ተመልሰው መሥራት ስላልተቻላቸው፣ በየጊዜው የሚገናኙበትንና ቃሉን በማንበብ፣ በመተርጐም የሚተጉበትን ምኵራብን መሥራት ጀመሩ። በምኩራብ ራቢ ወይም መንፈሳዊ መሪ ያለ ሲኾን፣ ሌሎች ደጋፊ ሰዎች ወይም ሠራተኞችን በተካተቱበት የሚመራ አነስተኛ ጉባኤ ነው።

Sunday 17 March 2024

የ“ነቢይ” ጥላሁን ነገረ ማርያም!

 Please read in PDF

የ“ነቢይ” ጥላሁንን የተወሰኑ ስብከቶችን የማድመጥ ዕድል አጊኝቼ አውቃለሁ፣ በኋላ ግን እርሱም “በግሉ” ወደ “ቸርች ከፈታ” ሲያዘነብል ተደንቄ ራቅኹት። ከሰሞኑ ደግሞ ስለ ማርያም የተናገረውን አይቼ፣ የነዶክተር ወዳጄነህንና የነፓስተር ቸሬን መንገድ ለመከተል ምን አደከመው? ብዬአለሁ። በስብከቱ መካከል ማርያምን (የጌታ ኢየሱስን እናት) “እየሰበከ” በመካከል እንዲህ ይላል፣

 " ... የወንጌላውያን ጸሐፊዎች [አራቱ ወንጌላትን ማለቱ ነው] የማርያምን ኹኔታ ስላላወቁና እርሷም ምናልባት አብራርታ ስላልነገረቻቸው እንጂ ... መለኮት ልትወልጂ ነው ሲላት …" ይላል፡፡


Tuesday 12 March 2024

እኔ ነኝ አድራሻው!

Please read in PDF

 ጌቶችና አለቆች  ገናና ክቡራን

በሰው ፊት ታላላቅ የኾኑ ኃያላን

ለምድር ለከበዱ ታዋቂ ምሑራን

ለግብዝ አስመሳይ ለሚወዱ ዓለምን …

Friday 8 March 2024

ኢየሱስ እስኪመጣ - ላለፉት አሥራ አንድ ዓመታት!

 

የማይዋሸውና (ቲቶ 1፥2) በምሕረቱ ባለጠጋ የኾነ እግዚአብሔር (ኤፌ. 2፥4)፣ ነፍሴም ሕያው ወደ አደረጋት ሕያው አምላክዋ ሳትመለስ (መክ.12፥7) ኢየሱስ እስኪመጣ ድረስ ዕንኾ፣ አሥራ አንድ ዓመታት በብሎግ(በጡመራ መድረክ) አገልግሎት በጌታ ፊት አለኹ! በዚህ አጭር ዘመኔ ከእርሱ በቀር የረዳኝ፣ ያጸናኝ፣ ከፍ ከፍ ያደረገኝ፣ ሞገስ የሰጠኝ፣ ብርሃኑን ያበራልኝ፣ ስጠወልግ ያለመለመኝ፣ ስደክም መንገድ አቋርጦና አሳብሮ መጥቶ ያበረታኝ፣ እጆቼን ይዞ “አይዞህ!” ያለኝ ከጌታ በቀር ማንም የለም፤ ክብር ይኹንለት!

Thursday 7 March 2024

መንፈሳዊውን ጾም እንጹም!

Please read in PDF

ጾም፣ በብሉይም ኾነ በአዲስ ኪዳን አማኞች ዘንድ፣ በጐላ መልኩ ሲተገበር የነበረ ደግሞም ያለ መንፈሳዊ ልምምድ ነው። ጾም በአማኞች ሕይወት እንደ መለኮታዊ ተግሳጽ የሚፈጸም መንፈሳዊ አምልኮም ነው። በብሉይ ኪዳን ንስሐ ሲገቡ (1ሳሙ. 7፥6)፣ ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ፣ ከእግዚአብሔር ዕርዳታ ለመፈለግ (ዘጸ. 34፥28፤ ዕዝ. 8፥21-23)፣ ራስን በመንፈሳዊ ተግሳጽ ለመገሰጽና የኀጢአት ኑዛዜ በእግዚአብሔር ለማቅረብ መንፈሳውያን ሰዎች በግል (2ሳሙ. 12፥22) ወይም በማኅበር (መሳ. 20፥26፤ ኢዩ. 1፥4) በእግዚአብሔር ፊት ይጾሙ ነበር!

Tuesday 5 March 2024

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፱)

Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

  • ንፈስ ቅዱስ፦ መንፈስ የኾነ (ዮሐ. 4፥24)፣ ፍጥረትን በመፍጠርና በውበት በማጌጥ (ዘፍ. 1፥2)፣ ከርሱ በመወለድና አዲስ ልደትን ለአማኞች የሚሰጥ (ቲቶ 3፥5)፣ ኃይልን በማልበስና የጸጋ ስጦታን ለቤተ ክርስቲያን በመስጠት ወይም በማከፋፈል (ዘካ. 4፥6፤ የሐ.ሥ. 1፥8፤ 1ቆሮ. 12፥7-11) በጽደቅ ፍሬዎች በመሙላትና በመቀደስ በአማኞች ሕይወት ውስጥ የሚኖር (ዮሐ. 14፥17፤ 1ቆሮ. 3፥16፤ 6፥19፤ ገላ. 5፥22-23፤ ኤፌ. 2፥22)፣ አብሮን በጸሎት የሚቃትት (ሮሜ 8፥26)፣ ቅድስት ድንግል ወልድን በተለየ አካሉ በሥጋ እንድትፀንስ በፈቃዱ ወድዶ የመጣ (ማቴ. 2፥11) የዘላለም እግዚአብሔር ነው፤ (ዕብ. 9፥14)።

Friday 1 March 2024

ድንግል ማርያም የአሚናዳብ ሠረገላ?

Please read in PDF

“የዛሬን አያድርገውና” ዲያቆን ትዝታው ሳሙኤል፣ ለድንግል ማርያም “ከዘመራቸው ዝማሬዎች” መካከል “የአሚናዳብ ሠረገላ” የሚል ይገኝበታል። ብዙ አገልጋዮች ከኦርቶዶክስ አገልጋይነታቸው ራሳቸውን አግልለው ወደ ወንጌል እውነት ሲመለሱ፣ አስቀድሞ “ለፍጡራን በግልጥ የዘመሩትን ዝማሬ” በትክክል ስህተት መኾኑን አምነው፣ ንስሐ ሲገቡ አላየኹም፤ ምናልባት የገቡ ካሉና መግባታቸውም እንደ ዝማሬያቸው አደባባያዊ ከኾነ እንዴት መልካም ነበር!

Monday 26 February 2024

እግዚአብሔር ለአሕዛብም ግድ ይለዋል!

Please read in PDF

እግዚአብሔር የሰማይና የምድር ፈጣሪ ነው፤ “እነሆ፥ ሰማይ ሰማየ ሰማያትም፥ ምድርም በእርስዋም ያለው ሁሉ የአምላክህ የእግዚአብሔር ነው።” (ዘዳግ. 10፥14) እንዲል፣ ከእግዚአብሔርና ለእግዚአብሔር ያልኾነ ፍጥረት ፈጽሞ የለም። በአዲስ ኪዳንም፣ “እርሱ[እግዚአብሔር] በክፎዎችና በበጐዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።” (ማቴ. 5፥44-45) በሚለው ንግግሩ እግዚአብሔር ለመላለሙ ግድ ይለዋል።