የ“ነቢይ” ጥላሁንን
የተወሰኑ ስብከቶችን የማድመጥ ዕድል አጊኝቼ አውቃለሁ፣ በኋላ ግን እርሱም “በግሉ” ወደ “ቸርች ከፈታ” ሲያዘነብል ተደንቄ
ራቅኹት። ከሰሞኑ ደግሞ ስለ ማርያም የተናገረውን አይቼ፣ የነዶክተር ወዳጄነህንና የነፓስተር ቸሬን መንገድ ለመከተል ምን
አደከመው? ብዬአለሁ። በስብከቱ መካከል ማርያምን (የጌታ ኢየሱስን እናት) “እየሰበከ” በመካከል እንዲህ ይላል፣
" ... የወንጌላውያን ጸሐፊዎች [አራቱ ወንጌላትን ማለቱ ነው]
የማርያምን ኹኔታ ስላላወቁና እርሷም ምናልባት አብራርታ ስላልነገረቻቸው እንጂ ... መለኮት ልትወልጂ ነው ሲላት …" ይላል፡፡