Sunday 17 March 2024

የ“ነቢይ” ጥላሁን ነገረ ማርያም!

 Please read in PDF

የ“ነቢይ” ጥላሁንን የተወሰኑ ስብከቶችን የማድመጥ ዕድል አጊኝቼ አውቃለሁ፣ በኋላ ግን እርሱም “በግሉ” ወደ “ቸርች ከፈታ” ሲያዘነብል ተደንቄ ራቅኹት። ከሰሞኑ ደግሞ ስለ ማርያም የተናገረውን አይቼ፣ የነዶክተር ወዳጄነህንና የነፓስተር ቸሬን መንገድ ለመከተል ምን አደከመው? ብዬአለሁ። በስብከቱ መካከል ማርያምን (የጌታ ኢየሱስን እናት) “እየሰበከ” በመካከል እንዲህ ይላል፣

 " ... የወንጌላውያን ጸሐፊዎች [አራቱ ወንጌላትን ማለቱ ነው] የማርያምን ኹኔታ ስላላወቁና እርሷም ምናልባት አብራርታ ስላልነገረቻቸው እንጂ ... መለኮት ልትወልጂ ነው ሲላት …" ይላል፡፡


Tuesday 12 March 2024

እኔ ነኝ አድራሻው!

Please read in PDF

 ጌቶችና አለቆች  ገናና ክቡራን

በሰው ፊት ታላላቅ የኾኑ ኃያላን

ለምድር ለከበዱ ታዋቂ ምሑራን

ለግብዝ አስመሳይ ለሚወዱ ዓለምን …

Friday 8 March 2024

ኢየሱስ እስኪመጣ - ላለፉት አሥራ አንድ ዓመታት!

 

የማይዋሸውና (ቲቶ 1፥2) በምሕረቱ ባለጠጋ የኾነ እግዚአብሔር (ኤፌ. 2፥4)፣ ነፍሴም ሕያው ወደ አደረጋት ሕያው አምላክዋ ሳትመለስ (መክ.12፥7) ኢየሱስ እስኪመጣ ድረስ ዕንኾ፣ አሥራ አንድ ዓመታት በብሎግ(በጡመራ መድረክ) አገልግሎት በጌታ ፊት አለኹ! በዚህ አጭር ዘመኔ ከእርሱ በቀር የረዳኝ፣ ያጸናኝ፣ ከፍ ከፍ ያደረገኝ፣ ሞገስ የሰጠኝ፣ ብርሃኑን ያበራልኝ፣ ስጠወልግ ያለመለመኝ፣ ስደክም መንገድ አቋርጦና አሳብሮ መጥቶ ያበረታኝ፣ እጆቼን ይዞ “አይዞህ!” ያለኝ ከጌታ በቀር ማንም የለም፤ ክብር ይኹንለት!

Thursday 7 March 2024

መንፈሳዊውን ጾም እንጹም!

Please read in PDF

ጾም፣ በብሉይም ኾነ በአዲስ ኪዳን አማኞች ዘንድ፣ በጐላ መልኩ ሲተገበር የነበረ ደግሞም ያለ መንፈሳዊ ልምምድ ነው። ጾም በአማኞች ሕይወት እንደ መለኮታዊ ተግሳጽ የሚፈጸም መንፈሳዊ አምልኮም ነው። በብሉይ ኪዳን ንስሐ ሲገቡ (1ሳሙ. 7፥6)፣ ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ፣ ከእግዚአብሔር ዕርዳታ ለመፈለግ (ዘጸ. 34፥28፤ ዕዝ. 8፥21-23)፣ ራስን በመንፈሳዊ ተግሳጽ ለመገሰጽና የኀጢአት ኑዛዜ በእግዚአብሔር ለማቅረብ መንፈሳውያን ሰዎች በግል (2ሳሙ. 12፥22) ወይም በማኅበር (መሳ. 20፥26፤ ኢዩ. 1፥4) በእግዚአብሔር ፊት ይጾሙ ነበር!

Tuesday 5 March 2024

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፱)

Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

  • ንፈስ ቅዱስ፦ መንፈስ የኾነ (ዮሐ. 4፥24)፣ ፍጥረትን በመፍጠርና በውበት በማጌጥ (ዘፍ. 1፥2)፣ ከርሱ በመወለድና አዲስ ልደትን ለአማኞች የሚሰጥ (ቲቶ 3፥5)፣ ኃይልን በማልበስና የጸጋ ስጦታን ለቤተ ክርስቲያን በመስጠት ወይም በማከፋፈል (ዘካ. 4፥6፤ የሐ.ሥ. 1፥8፤ 1ቆሮ. 12፥7-11) በጽደቅ ፍሬዎች በመሙላትና በመቀደስ በአማኞች ሕይወት ውስጥ የሚኖር (ዮሐ. 14፥17፤ 1ቆሮ. 3፥16፤ 6፥19፤ ገላ. 5፥22-23፤ ኤፌ. 2፥22)፣ አብሮን በጸሎት የሚቃትት (ሮሜ 8፥26)፣ ቅድስት ድንግል ወልድን በተለየ አካሉ በሥጋ እንድትፀንስ በፈቃዱ ወድዶ የመጣ (ማቴ. 2፥11) የዘላለም እግዚአብሔር ነው፤ (ዕብ. 9፥14)።

Friday 1 March 2024

ድንግል ማርያም የአሚናዳብ ሠረገላ?

Please read in PDF

“የዛሬን አያድርገውና” ዲያቆን ትዝታው ሳሙኤል፣ ለድንግል ማርያም “ከዘመራቸው ዝማሬዎች” መካከል “የአሚናዳብ ሠረገላ” የሚል ይገኝበታል። ብዙ አገልጋዮች ከኦርቶዶክስ አገልጋይነታቸው ራሳቸውን አግልለው ወደ ወንጌል እውነት ሲመለሱ፣ አስቀድሞ “ለፍጡራን በግልጥ የዘመሩትን ዝማሬ” በትክክል ስህተት መኾኑን አምነው፣ ንስሐ ሲገቡ አላየኹም፤ ምናልባት የገቡ ካሉና መግባታቸውም እንደ ዝማሬያቸው አደባባያዊ ከኾነ እንዴት መልካም ነበር!

Monday 26 February 2024

እግዚአብሔር ለአሕዛብም ግድ ይለዋል!

Please read in PDF

እግዚአብሔር የሰማይና የምድር ፈጣሪ ነው፤ “እነሆ፥ ሰማይ ሰማየ ሰማያትም፥ ምድርም በእርስዋም ያለው ሁሉ የአምላክህ የእግዚአብሔር ነው።” (ዘዳግ. 10፥14) እንዲል፣ ከእግዚአብሔርና ለእግዚአብሔር ያልኾነ ፍጥረት ፈጽሞ የለም። በአዲስ ኪዳንም፣ “እርሱ[እግዚአብሔር] በክፎዎችና በበጐዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።” (ማቴ. 5፥44-45) በሚለው ንግግሩ እግዚአብሔር ለመላለሙ ግድ ይለዋል።

Tuesday 13 February 2024

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፰)

Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

5.2. ሥላሴ ምግባራዊ ሦስትነት (Economic Trinity) አላቸው

በሌላ ንግግር አብ ከወልድ ወይም ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለውን ዐይነት ግንኙነት፣ ከፍጥረት ጋርም እንዲያ ያለ ግንኙነት የለውም። በሥላሴ መካከል ያለውን ኅብረትና አንድነት የሚያመለክተው ግንኙነት፣ ምግባራዊ ሦስትነት (Economic Trinity) ተብሎ ይጠራል። በዚህ ረገድ የሥላሴ እያንዳንዱ አካል በመለኮታዊ ማንነቱ ፍጥረትን በመፍጠር፣ በመመገብ፣ በልዕልና በመምራት፣ በሥልጣን፣ በአገዛዝ፣ በማዳን በሚሠሩት መለኮታዊ ሥራዎች ያላቸውን ፍጹም አንድነት የሚያመለክት ነው።

Friday 19 January 2024

“እያጠመቃችኋቸው፥ … እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤” (ማቴ. 28፥20)

 Please read in PDF

ለቤተ ክርስቲያን ከተሰጡ ሐዋርያዊ ተልእኮዎች ውስጥ፣ ቀዳሚውና የዘወትር ተግባር “አማኞችን ደቀ መዛሙርት ማድረግ” ነው። እንደ ጌታችን ትምህርት፣ አማኞች ደቀ መዛሙርት የሚኾኑት፣ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሲጠመቁ፣ ጌታ ያዘዘውን ኹሉ እንዲጠብቁ ሲማሩ፣ እንዲሁም በመታመን እርሱን ለመከተል ደቀ መዛሙርት በሕይወት ሲኾኑ ነው።

Thursday 18 January 2024

“ከእኛ ጋር ለምን አስተካከልሃቸው?” (ማቴ. 20፥11)

 Please read in PDF

ጌታችን ኢየሱስ መንግሥተ ሰማያት ምን እንደምትመስል በሰጠው ውብ ምሳሌ፣ እግዚአብሔርን የወይኑ እርሻ ባለቤት አድርጎ ያቀርበዋል። የእርሻው ባለቤት በአትክልቱ ስፍራ ሰውን ለመቅጠር ፈልጎ ጥሪ አቀረበ። በጥሪው መሠረት ሠራተኞቹ፣ አንድ ዲናር ሊከፈላቸው ተስማምተው ወደ እርሻው ቦታ መጡ። የሥራው ሰዓትም ከማለዳ 12 ሰዓት እስከ ምሽት 12 ሰዓት ነበር።

Wednesday 17 January 2024

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፯)

 Please read in PDF

ካለፈው ቀጠለ …

   5. የቅድስት ሥላሴ ትምህርት ምስጢር ነው!

ትምህርተ ሥላሴ ምስጢር ነው ስንል፣ ምን ማለታችን ነው? ብንል፣ ለሰው ያልተገለጠ ብዙ ትምህርት ወይም ብዙ ነገር አለ ማለታችን ነው። ኾኖም ግን በመጽሐፍ ቅዱስ ሦስቱን አካላት ለማጥናት ብዙ ትምህርት እንዳለ ልንዘነጋ አይገባም። በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ትምህርቶች ምስጢር ተብለዋል፤ ለምሳሌ፦ ጌታችን ኢየሱስ፣ ለደቀ መዛሙርቱ፣ “ለእናንተ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፥ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም።” ሲል (ማቴ. 13፥11)፣ ምሳሌዎቹ የተነገሩት በሕዝቡ ኹሉ ፊት ቢኾንም፣ ትርጕማቸው ወይም ምስጢሩ ግን የተነገረው ለደቀ መዛሙርት ብቻ ነው።



Thursday 11 January 2024

Sagantaa Addaa Ayyaana Yaadannoo Dhaloota Kiristoos!

" ... Ishiini ilma deetti; atis maqaa isaa Yesuus jettee moggaafta; inni saba isaa cubbuu isaanii irraa ni fayyisaatii." (Matt. 1:22)

 

Saturday 6 January 2024

ከባሪያዪቱ የተወለደ ንጉሥ!

 Please read in PDF

የክርስትና ትምህርት ከደመቀበትና ከተንቈጠቈጠበት ቀዳሚው እውነት አንዱ፣ የእግዚአብሔር ልጅ በእርሱ የሚያምኑትን ኹሉ በጸጋ የእግዚአብሔር ልጆች ያደርግ ዘንድ የሰው ልጅ መኾኑ ነው። እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ኾኖ፣ ዓለማትን የፈጠረና ደግፎም የያዘ ወይም ዓለሙ ተያይዞ የቆመው (ዮሐ. 1፥3፤ ቈላ. 1፥17፤ ዕብ. 1፥3) በእርሱ በታላቁ አምላክ ቢኾንም፣ በተለየ አካሉ  ከባሪያዪቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም (ማቴ. 1፥21፤ ዮሐ. 1፥14) ሥጋን ነሥቶ ተወለደ።