Sunday 30 August 2020

የልጁን መልክ መምሰል (ክፍል ፩)

Please read in PDF

    “ሁላችን በሃይማኖትና የእግዚአብሔርን ልጅ በማወቅ አንድ እስክንሆን ድረስ በክርስቶስ ፍጻሜ ልክ የአካል መጠን እንዲደርስ ፍጹም ሰው እንሁን” (ኤፌ.4፥13)

መግቢያ

    በዘመናችን ሰዎች ክርስቶስን በትክክል መኾን እንደሚቻላቸው አያሌ የስህተት ትምህርቶችን መስማት ከጀመርን ሰነባብተናል። አንዳንዴ ክርስቶስን የፍጥረቱ አካል በማድረግ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ እኛ ራሱ ክርስቶስን ልንኾን እንደምንችል በአደባባይ ታውጆአል፤ በተለያየ መንገድ ይህን ትምህርት ፊት ለፊት በመቃወም፣ የትምህርቱን ስሑትነትና ከመጽሐፍ ቅዱስ ያልተቀዳ መኾኑን ተናግረናል፤ አስተምረናል። ዛሬም ክርስቶስ የፍጥረት አካል እንዳይደለ፤ ቅዱሳት መጻሕፍት ያስተማሩንን፣ ፍጹም አምላክነቱና ፍጹም ሰውነቱን  ደፍረን እንናገራለን።

Tuesday 18 August 2020

የመጽሐፍ ቅዱሱ ክርስቶስ - ክብሩና ሞቱ (ሉቃ. 9፥28-36)

  Please read in PDF

  በግርማ መለኮት የተፈራውና ማንም ሊቀርበው የማይችለው ጌታ፣ በክበበ ትስብእት በናዝሬት ከምትኖር ከአንዲት ድኻ ሴት ከማርያም ተወልዶ፣ በተዋረደው ዓለም በውርደት ተመላለሰ። ከመሰቀሉ በፊት ሰውን ሥጋ በመልበሱ ብቻ ተዋረደ። በበረት ከመወለዱ በፊት፣ በናዝሬት መንደር ከአንዲት ሴት ማኅፀን በማደሩ እጅግ፤ እጅግ ዝቅ አለ። ከኀጢአተኞች ጋር በመቈጠሩና ከእነርሱም ጋር በመዋሉ ደግሞ ኢየሱስ፣ ስድባችንን ኹሉ በመሸከም መስቀሉን በመላ ዘመኑ ታገሠ።

Saturday 15 August 2020

ስለ ማርያም “ከሚሸቅጡ” ተጠበቁ!

Please read in PDF

   መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገረውን ብቻ መናገር አስተዋይነት፤ ያልተናገረውን ደግሞ አለመጨመር ፍጹም ታማኝነት ነው። እኛ ሰውን ደስ ለማሰኘት የተናገርነው “እውነት”፣ መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ ያልተናገረው ሐሰት ሊኾን የሚችልበት አንዳች ሚዛን የለም፤ የእውነት እውነተኛው ሚዛን መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ከኾነ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ያልተናገረውና ያላለው ኹሉ ሐሰት፣ እርሱ የተናገረውና በእርሱ ያለው ብቻ እውነት ነው። ሚዛንን ስቶ ሚዛናዊ መኾን ፈጽሞ አይቻልምና።

Thursday 13 August 2020

የመጽሐፍ ቅዱሱ - ለኢየሩሳሌም ያለቀሰው መሲሕ (ሉቃ. 19፥41-44)

Please read in PDF

   ጌታችን ኢየሱስ ስለ ማልቀሱ የተነገረው እጅግ በጣም ውሱን ቦታ ብቻ ነው፤ ካለቀሰባቸው ምክንያቶች አንዱ ደግሞ ስለ ኢየሩሳሌም ያለቀሰው ልቅሶ ነበር። ያለቀሰው በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ተቀምጦ፣ ከተማይቱን ፊት ለፊት በመመልከት ነበር። ሚስቱን አብዝቶ የሚወድድ ጐልማሳ፣ ሚስቱ በተወችው ጊዜ በስብራት እንደሚያለቅስ እንዲሁ፣ ኢየሱስም የከተማዋ ኹለንተና ከሚታይበት ከደብረ ዘይት ተራራ ፊት ለፊት ተቀምጦ ለኢየሩሳሌም አለቀሰላት።

Tuesday 4 August 2020

ክርስቲያኖች ወደ ቄሳር ሲጠጉ እፈራለሁ!

  ለምንኖረው ሕይወትና ለማናቸውም የክርስትናችን የኑሮ ዘይቤ፣ ማዕከሉ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። ያልተኖረ የሕይወት አብነት የለንም፤ የተኖረና በድል የተጠናቀቀ የሕይወት አብነት ግን አለን፤ እርሱም የክርስቶስ። ክርስቶስ ያልኖረውን ሕይወት ኑሩ አላለንም፤ “ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤” (ማቴ. 11፥28) ያለን ጌታ፣ “ፍለጋውን እንድንከተል ምሳሌ ትቶልናል” (1ጴጥ. 2፥21) ስለዚህ የማይጨበጥ፣ በንግግር ብቻ የሚተረክ፣ በተመስጦአዊ ስብከቶች የሚሰበክ ብቻ ያይደለ፤ የሚኖር፣ የሚሻተት፣ የሚቀመስ፣ የሚጣጣም ቅዱስ ሕይወትን ሰጥቶናል።

Saturday 1 August 2020

የአፍላህን ጊዜ

Please read in PDF

ወዲያ ገረገራ፣ ጥግ ላይ ያለኸው
ያለህ  የምትመስል፣  ሻግተህ  ያረጀኸው