Tuesday 30 September 2014

ሞት ደጅ ደጄን እያየ …


                          Please read in PDF              
                                     
ደምህ ነው ህይወቴ ፣ መከራህ ጉልበቴ፤
ህማምህ ድጋፌ ፣ መድከምህ ብቃቴ፤

Thursday 25 September 2014

የመስቀሉ ቃል


                                   

                                 
      የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉ አህዝብ ሞኝነት፤ ለአይሁድም ማሰናከያ ነው፡፡ ምክንያቱም አይሁድ የመስቀሉን ቃል  በእንጨት ላይ መዋልና መሰቀልን እንደተረገመ ስለሚቆጥሩት ነው፡፡(ዘዳግ.21፥23 ፤ ገላ.3፥13) ነገር ግን ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀል ላይ በመሰቀሉ “እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ … ” እንደኃጢአተኛ የተቆጠረ ሆነ፡፡(2ቆሮ.5፥21) ለግሪክ ሰዎች ደግሞ በእንጨት ላይ መሰቀል የአማልክትን ክብርና ልዕልና ዝቅ የሚያደርግና እንደድኩም የሚያስቆጥር ስለሆነ ፈጽሞ አይቀበሉትም፡፡
      ቀድሞ የጥንት ፋርሶች በኋላም ሮማውያን አንድን ወንጀለኛ በመስቀል ላይ በመስቀል የሚቀጡት “ኦርዝሙድ” የተባለ የመሬት አምላካቸው እንዳይረክስባቸው በመጠንቀቅና ለአማልክታቸው ክብርን ለመስጠት በማሰብ ነበር፡፡(አባ ጐርጐርዮስ(ሊቀ ጳጳስ)፤ የኢትዮጲያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ 3ኛ ዕትም፤ 1991፤ አዲስ አበባ፤ ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ድርጅት፤ ገጽ.104)

Monday 22 September 2014

ሦስቱ ባህታውያን(የመጨረሻ ክፍል)


                                            Please read in PDF
      
     ነገር ግን ሁለተኛው ባህታዊ ቃላቶቹን አቀላቅለው አሳስተው ተናገሩ፡፡ ራቁታቸውን ያሉት ረዥሙ ባህታዊም አጣርተው አልደገሙትም፡፡ ጢማቸው አፋቸውን ሸፍኖት ስለነበር የተጣራ ድምፅ ሊያወጡ አልቻሉም፡፡ ጥንታዊው ደግሞ ጥርሶቻቸው ስለረገፉ በግልጽ የማይሰማ ነገር ነው ያጉተመተሙት፡፡
   አቡኑ እንደገና ደገሙላቸው፡፡ ባህታውያኑም እንደገና ደገሙት፡፡ አቡኑ በትንሽ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ባህታውያኑም በአጠገባቸው ቆመው አፍ አፋቸውን አፍጠው እየተመለከቱ የሚሏቸውን ይደግሙላቸው ነበር፡፡ ቀኑን ሙሉ እስከአመሻሽ ድረስ ሊያስተምሯቸው ደከሙ፡፡ አንዲቷን ቃል አስር፣ ሃያ፣ መቶ ጊዜ እየመላለሱ አስጠኗቸው፡፡ ቃላት እየተቀለቀሉባቸው ሲቸገሩ ያርሟቸውና እንደገና ከመነሻው ያስጀምሯቸዋል፡፡
     የጌታን ጸሎት ሙሉ ለሙሉ እስከሚያስተምሯቸው ድረስ አቡኑ ከባህታውያኑ ዘንድ ቆዩ፡፡ በመጨረሻም ያለ አቡኑ ድጋፍ እያንዳንዳቸው በራሳቸው ሙሉ ጸሎቱን ወረዱት፡፡
    አቡኑ ወደ መርከቡ ሊመለሱ ሲነሱ ጨለማው እየከበደ ከባህሩም ጨረቃ እየወጣች ነበር፡፡ ባህታውያኑን ሲሰናበቱ ሁሉም እስከመሬት አጐንብሰው ሸኟቸው፡፡ እሳቸውም እያንዳንዳቸውን ካጐነበሱበት ቀና እያደረጉና እያቀፏቸው ባስተማሯቸው መሠረት እንዲጸልዩ ካዘዟቸው በኋላ ወደ ጀልባዋ ገቡ፡፡

Friday 19 September 2014

ሦስቱ ባህታውያን (ክፍል - ሁለት)

    
        Please read in PDF

       አቡኑ ከመርከቢቷ የፊት ጫፍ ላይ ወንበር ቀርቦላቸው ሲቀመጡ ሌሎቹም ሁሉ መጥተው ወደ ትንሿ ደሴት መመልከታቸውን ቀጠሉ፡፡ ጥሩ የማየት ችሎታ ያላቸው ሰዎች በደሴቷ ላይ የሚገኙትን አለቶችና የጭቃ ጎጆዋንም ማየት ችለው ነበር፡፡ ከመሃላቸው አንዱ ሦስቱን ባህታውያን ጭምር መለየት ችሎ ነበር፡፡ ካፒቴኑ አጉሊ መነጽር አምጥቶ ከተመለከተ በኋላ ለአቡኑ እየሰጣቸው፦
   “ትክክል ነው፡፡ ከባህሩ ጠረፍ ላይ ከትልቁ አለት እንዲህ ወደ ቀኝ ሲሉ ሦስቱ ባህታውያን ቆመው ይታያሉ፡፡” አለ፡፡
    አቡኑ በመነጽር ተመለከቱ፡፡ ወደትክክለኛው አቅጣጫም አዞሩት፡፡ የተባለው እውነት ነው፡፡ ሦስቱም እዚያው ቆመዋል፡፡ አንደኛው ረዥም ሌላኛው ትንሽ አጠር የሚሉና ሦስተኛው ደቃቃ ትንሽ፡፡ ሦስቱም ከባህሩ ጠረፍ ላይ እጅ ለእጅ ተያይዘው ቆመው ነበር፡፡

Monday 15 September 2014

ሦስቱ ባህታውያን (ክፍል አንድ)



አጭር ልብወለድ
(ምንጭ ብሪቱ መጽሔት ጥር - የካቲት 1991)
(ደራሲ፦ ሊዎ ቶልስቶይ)
(ተርጓሚ፦ ሁነኛው ጥላሁን)

“አሕዛብም በመናገራቸው ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና ስትጸልዩ እንደ እነርሱ በከንቱ አትድገሙ።ስለዚህ አትምሰሉአቸው፤ ሳትለምኑት አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ያውቃልና።” (ማቴ.6፥7-8)

     አቡኑ ከአርካንጌልስክ ከተማ ወደ ሶሎቬትስኪ ደሴት በመርከብ እየተጓዙ ነበር፡፡ ቅዱሱን ሥፍራ ለመሳለም የሚሄዱ ምዕመናንም አብረዋቸው ነበሩ፡፡ የነፋሱ አቅጣጫ አመቺ፣ አየሩም ማለፊያ ነበረ፡፡ ባህሩም ጸጥ ብሏል፡፡ ምእመናኑ ገሚሱ ጋደም ብለው ከፊሉም ከያዙት ስንቅ እየቀማመሱ የተቀሩትም በቡድን በቡድን ተቀምጠው እርስ በእርስ ያወራሉ፡፡ አቡኑ ከነበሩበት ተነስተው ወደ መርከቡ መተላለፊያ መራመድ  ጀመሩና ወደጫፉ ሲቃረቡ ሰብሰብ ያሉትን ሰዎች አዩዋቸው፡፡ አንድ ባላገር ወደባህሩ እያመለከተ አንድ ነገር እያሳያቸው ሲናገር ሰዎቹ ያዳምጡት ነበር፡፡ አቡኑ ቆም ብለው ባላገሩ ወደሚያመለክትበት በኩል ተመለከቱ፡፡ በፀሐይ ከሚያብረቀርቀው ባህር በስተቀር ምንም የሚታይ ነገር አልነበረም፡፡ ወደሰዎቹም ጠጋ ብለው ባላገሩ የሚለውን ማዳመጥ ጀመሩ፡፡ ባላገሩ አቡኑን እንዳየ ባርኔጣውን በማውለቅ ንግግሩን አቋርጦ ፀጥ አለ፡፡ የሚያዳምጡትም ሰዎች ባርኔጣዎቻቸውን በማንሳት በአክብሮት ተቀበሏቸው፡፡
    “በመምጣቴ አትጨነቁ ወዳጆቼ” አሉ አቡኑ፡፡ ወደባላገሩም ፊታቸውን አዙረው “የመጣሁት አንተ የምትነግራቸውን ለመስማት ብዬ ነው” አሉት፡፡

Tuesday 9 September 2014

የተወደደችው የጌታ አመት (ሉቃ.4፥19)



እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ በሰላም በፍቅር አሸጋገራችሁ!!!

    ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ያለማቋረጥ ከብዙ ህዝብ ጋር ለአምልኰ በመገኘት ለተከታዮቹ ደቀ መዛሙርት የሚደነቅ ምሳሌ የሚሆን ልምድ አለው፡፡(ማቴ.13፥54፤ ማር.1፥21፤ ሉቃ.4፥16፤ ዮሐ.7፥14) ጌታ ለጸሎትና ቃሉን ለማስተማር ዘወትር “መሰብሰብን ባለመተው” ለደቀ መዛሙርቱ አብነት ሆኗል፡፡(ዕብ.10፥24) ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት ለጸሎት፤ ቃሉን ለመመርመርና ለማስተማር መሆንን ጌታ በእውነት እኛንም አስተምሮናል፡፡ ናዝሬት ጌታን ለመቀበል ፈቃደኛ ባትሆንም እርሱ ግን ወዳደገባትና ወደሚያውቃት ከተማ ምኩራብ መጥቶ አስተማረ፡፡ ዕድገታችንን፣ ማንነታችንን፣ ገመናችንን፣ ልጅነታችንንና፣ ውድቀታችንን … ምናልባትም “ልካችንን” በሚያውቁን ሰዎች ፊት ማገልገል ከባድ ህመም ይኖርበት ይሆናል፤ ጌታ ግን አድርጎታልና ልጆቹ በህይወቱ ልንታዘዝ፤ ህይወቱም ሊያስተምረን ይገባል፡፡
    ጌታ  ወደምኩራብ በገባ ጊዜ የኢሳይያስን ትንቢት ጥቅልል አንስተው ሰጡት፡፡ እርሱም ተነስቶ መጽሐፉን በመተርተር ማንበብ ጀመረ፡፡ አይሁድ ምንም እንኳ ወደ ተስፋው ፍጻሜ ባይደርሱም፤ የእግዚአብሔርን ቃል የማንበብ ብቻ ሳይሆን መጻህፍትን በመቅደሱና በየምኩራቦቻቸው በአግባቡ የማስቀመጥ ልማድ ነበራቸው፡፡ በምኩራባቸው የእግዚአብሔር ቃል ጥቅልል ትልቁንና የመጨረሻውን ሥፍራ በክብር ይይዛል፡፡ ትልቅና የመጨረሻው አምልኰ ለእግዚአብሔር ቃልና ላስተማረን ትምህርቱ ልዩ ክብርን በመስጠት መታዘዝ ነው፡፡ የብዙዎቻችን ቤት “መጻህፍት መደርደርያ” የተመሉት በልቦለድና በፍልስፍና “ጥቅልል ጽሁፎች” ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ቃል ቸል በማለት ለሌሎች “ፍጡራን ጥቅልሎች” ትልቅ ክብርና ሥፍራ የሰጠ ትውልድ ይህ የእኛ ዘመን ትውልድ ነው ብል ያልተጋነነ እውነት ነው፡፡

Tuesday 2 September 2014

ማስተስረያውን ክዶ


                               Please Read in PDF 


ሳይጐድል ደምግባቱ፣ አምሮ እንደደመቀ፤
ትኩስ ሥጋነቱ፣ ግሎ እንደሞቀ፤
ሸጋ ቆንጆነቱ፣ ጉድ አጀብ አስብሎ፤
ከደሙ ቤዛነት፣ ከ‘ርሱ ተነጥሎ፤